Get Mystery Box with random crypto!

ሰማያዊ ስጦታ ቤተክርስቲያን//Heaven Gift Church//

የቴሌግራም ቻናል አርማ http_gcgm — ሰማያዊ ስጦታ ቤተክርስቲያን//Heaven Gift Church//
የቴሌግራም ቻናል አርማ http_gcgm — ሰማያዊ ስጦታ ቤተክርስቲያን//Heaven Gift Church//
የሰርጥ አድራሻ: @http_gcgm
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 16.34K
የሰርጥ መግለጫ

👉መልካሙ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን
👉ማቴ 14፥30
👉ሚኒስትሪያችንን በተለያዩ ስጦታዎች
ስለምታግዙን እናመሰግናለን።
ለማንኛውም ጥያቄ እና እገዛ👇
ለፀሎት አገልግሎት ከስር ያለውን ስልክ ይጠቀሙ።
https://www.facebook.com/gcgm.gctv?mibextid=sCpJLy
👉YouTube-https://youtube.com/@melkamqine?si=vBbrpgENQkfcJ

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2023-02-10 06:02:21 ሰላም ቅዱሳን ክፍል 5.
እንግዲ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፡ይህ አዲስ ተደርጎ የተፈጠረው ሰው የመንፈስ ፍሬ ደግሞ አልፎም በስጋ ህይወት ላይ የሚገለጥ ህይወት አለው ብለናል።
መነሻ ጥቅስ ፥- ገላ 5፥22
ገላትያ 5 (Galatians)
22፤ የመንፈስ ፍሬ ግን ፍቅር፥ ደስታ፥ ሰላም፥ ትዕግሥት፥ ቸርነት፥ በጎነት፥ እምነት፥ የውሃት፥ ራስን መግዛት ነው።

አዲሱ ሰው እና የመንፈስ ፍሬ
4.ቸርነት
Greek translation.... chrestotes
English Translation...Kindness/gentlness
አማርኛ ፍቺ.....ቸርነት
# Kindness....Civil behaviour, favourable treatment, or a constant and habitual practice of friendly offices and benevolent actions.
ስለዚህም ምክኒያት ማንም በክርስቶስ ይሁን ስንል ወይንም ከሆነ (ቸርነት)የምንለው የመንፈስ ፍሬ ተካፋይ እንድትሆኑ ነው ።
በዚህ ማንነት የትም ስፍራ ላይ የሚገለጠው የታደሰ አይምሮ ያለው ነው።
ይህም ማለት አዲሱ ሰው በመንግስት አመራር ላይ ይሁን ፥በትምህርት ተቋማት ይሁን ፡በቤተ/ክ አመራር ይሁን ፡ በንግድ ዘርፍ ይሰማራ ብቻ ቸርነት በሙሉ ማንነቱ ተላብሶ ይታያል ፡ይህን እንድታደርጉ የአእምሮ ብቃት ሳይሆን የሚረዳችሁ ከማንነት ለውጥ ጋር ተያየዞ የሚገለጥ የመንፈስ ፍሬ ነው።
እንግዲ እግዚአብሔር ራሱ በማንነት ደረጃ ቸር ነው።
መንገዶቹ ሁሉ የቸርነት ናቸው ብሎ መጽሃፍ ይነግረናል
መዝሙር 25 (Psalms)
10፤ የእግዚአብሔር መንገድ ሁሉ ቸርነትና እውነት ነው።
ሁሉን አድራጎቱን አይታችሁ እንደሆን በቸርነት እና በምህረት የተሞላ ነው።
ቸርነትን የሚያደርገው አስቦ አቅዶ ሳይሆን የመተንፈስ ያክል ቸርነት ማንነቱ ስለሆነ ነው።
ቸርነት የሚገለጠው ቸር ለሆነላችሁ አካል ወይም ሰው ሳይሆን ለማታውቁት ሁሉ ነው መሆን ያለበት ለዚያ ነው ቸርነት ማንነት ነው የምንለው።
የገላትያ ጸሃፊም ለዛ ነው የመንፈስ ፍሬ ነው ያለው።
ቸር ስትሆኑ አእምሮአችሁ እና ልባችሁ ተግባበተው ከመንፈሳችሁ ጋር እየተጉ ታገኙታላችሁ ።
ቸርነት ሁሉን በእኩል አይን ማየት ነው።
ይህን እውነት አውቃችሁ አዲስ ፍጥረት የሆናችሁ በዚህ ህይወት ልትገለጡ፡ይህ ማንነት ላልተካፈላችሁ ደግሞ ፡ከዚህ ማንነት ተካፋይ ሆናችሁ ፡በዚህ ፍሬ መገለጥ እንድትችሉ ይሆናል
ስለዚህ በክርስቶስ ኢየሱስ መሆን ይጠቅማል የምንለው ለዚህ ነው።ይህን ለማግኘት ደግሞ በክርስቶስ ሆኖ አዲስ ማንነት መያዝ ያስፈልጋል።

ለተጨማሪ ጥያቄዎች- 0966222852
Powered by እዮብ አበራ


ክፍል 6.አዲሱና የመንፈስ ፍሬ
ክፍል 6.በጎነት
ሳምንት ይቀጥላል........


#የመንፈስፍሬ #ፍቅር #ሰላም #ደስታ #ትዕግስት#ቸርነት#....
325 viewsEjob @ JS, 03:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-10 06:02:18
342 viewsEjob @ JS, 03:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-07 08:24:55
ከሰሎሞን እና ከዮናስ የሚበልጠው ከእናንተ ጋር ነው።
ሰላም ለእናንተ ቅዱሳን አንድ መልክት አለኝ ዛሬ የምነግራችሁ እውነት ከፍታን የሚያሰጨምር፥አገልግሎታችሁን ከፍ የሚያደርግ፥የሕልውና ልሕቀት ውስጥ የሚያስገባችሁ፥ሕብረታችሁን የሚስጨምር ይሁን ።
መጽሐፍ ቅዱስ ሲናገር
Luke 11 (አማ) - ሉቃስ
31: ንግሥተ አዜብ በፍርድ ከዚህ ትውልድ ሰዎች ጋር ተነሥታ ትፈርድባቸዋለች፤ የሰሎሞንን ጥበብ ለመስማት ከምድር ዳር መጥታለችና፥ እነሆም፥ ከሰሎሞን የሚበልጥ ከዚህ አለ።
Luke 11 (አማ) - ሉቃስ
32: የነነዌ ሰዎች በፍርድ ከዚህ ትውልድ ጋር ተነሥተው ይፈርዱበታል፤ በዮናስ ስብከት ንስሐ ገብተዋልና፥ እነሆም፥ ከዮናስ የሚበልጥ ከዚህ አለ።

እነዚህ ሰዎች በዘመናቸው ብዙ ያገለገሉ እንደኛው ሰው የነበሩ እግዚአብሔርን አግልግለው ያለፉ እንጂ ሌላ ድብቅ የለውም ሰው ሆኖ የመጣው አምላክ የሆነው ከሁሉ የሚበልጠው ግን በተቸገራችሁበት ነገር ላይ ከፍታ በሚያስፈልጋችሁ ነገር ላይ ይዟችሁ ይወጣል።የሰማዩን ካልከለከላችሁ ፥የምድሩን አይነሳችሁም።
ከዮናስ ይሁን ከሰሎሞን የሚበልጥ በእናንተ ውስጥ ነው።
የሚበልጥ የሚለው ቃል Pleion የሚል ቃል ሲይዝ ትርጓሜውም በብዛት አንድ ብቻ የሆነ ታላቅ የሆነ እንደሱ አይነት ሌላ የሌለ፤በጥራት አንድ የሆነ እንደሱም ሌላ የሌለ ማለት ነው ።ይህ አምላክ ደግሞ በእኛ ውስጥ አድሯል።
ስለዚህ የመንፈስ ቅዱስ ሕብረት ልሕቀት፥የመከናወን ልሕቀት፥ከፍ የማለት ልሕቀት ለሁላችን ተሰቶናል።
በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ስትንበረከኩ በመንፈስ ቅዱስ ልሕቀት ውስጥ ግቡ
በኢየሱስ ስም የቃል የመገለጥ ልሕቀት ውስጥ ግቡ፥በመንፈስ ቅዱስ የመመራት ልሕቀት ውስጥ ፥ወንጌልን የምትሰሩበት የብርሃን ልሕቀት ያግኛችሁ።

ብሩካን መልካም ቀን
1.0K viewsEjob1 Ejob, 05:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-04 16:16:00 Follow our face book page stay blessed all


https://www.facebook.com/gcgm.gctv?mibextid=LQQJ4d
350 viewsEjob @ JS, edited  13:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-04 15:59:20 You are blessed


406 viewsEjob @ JS, edited  12:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-03 06:00:08 ሰላም ቅዱሳን ክፍል አራት....
እንግዲ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፡ይህ አዱስ ተደርጎ የተፈጠረው ሰው የመንፈስ ፍሬ ደግሞ አልፎም በስጋ ህይወት ላይ የሚገለጥ ህይወት አለው ብለናል።
መነሻ ጥቅስ ፥- ገላ 5፥22
ገላትያ 5 (Galatians)
22፤ የመንፈስ ፍሬ ግን ፍቅር፥ ደስታ፥ ሰላም፥ ትዕግሥት፥ ቸርነት፥ በጎነት፥ እምነት፥ የውሃት፥ ራስን መግዛት ነው።

አዲሱ ሰው እና የመንፈስ ፍሬ
4.ትዕግስት
Greek translation....Makrothymia
English Translation...pacience
አማርኛ ፍቺ.....መታገስ


በክርስትያን ህይወት ውስጥ ባህሪ በጣም ወሳኝ ነገር ነው፡፡ ባህሪያችን በተሰራ መጠን በእግዚአብሄር መንግስት ውስጥ ጠቃሚነታችን ይጨምራል ለብዙዎችም በረከት እንሆናለን፡፡

ባህሪያችንን ባሳደግን መጠን ደግሞ በእግዚአብሀሔር መንግስት ውስጥ ያለን ተፅእኖ ይጨምራል እግዚአብሄርም ለተጨማሪ ሃላፊነት ያምነናል፡፡ እግዚብሄር ክብሩን ሊገልጥብን በህይወታችን በትጋት ይሰራል፡፡

አንዳንዴ የእግዚአብሔር አሰራርና የኛ አስተሳሰብ አንድ ላይሆን ይችላል፡፡ መታገስ እና እግዚአብሔርን መጠበቅ የሚያስፈልገው የእግዚአብሔር አሰራርና የእኛ ፍላጎት ሁልጊዜ አብሮ ላይሄድ ስለሚችል ነው፡፡

የእግዚአብሔርን እውነተኛውን ነገር ማግኘት ከፈለግን እግዚአብሔርን መከተል አለብን ሌላ መንገድ የለውም፡፡ እግዚአብሔር የራሱ እርምጃ አለው፡፡ እግዚአብሔር በእኛ ፍጥነት አይገባም፡፡ ስለዚህ ነው ከእግዚአብሔር ጋር በትህትና ለመኖርና ለማፍራት ትእግስት ወሳኝ የሚሆነው፡፡

የእግዚአብሔርን እርምጃ ሳንጠብቅ የምናደርገው ነገር የእኛ እንጂ የእርሱ አይሆንም፡፡

በህይወታችን እግዚአብሔርን ብቻ ሳይሆን ሰውንም መታገስ ይገባናል፡፡ እያንዳንዱ ሰው የራሱ ደረጃ እና አመለካከት አለው፡፡ ከሰው ጋር አብሮ ለመኖርና ለማገልገል በዚያም ፍሬያማ ለመሆን ትግስት ይጠይቃል፡፡ ሰው ሁሉ እኛን ይምሰል ማለት ትእቢት ነው፡፡ ሰውን መታገስ ግን ትህትና ነው፡፡

ማንኛውም ሃይል ካለመቆጣጠሪያ መሳሪያው አደገኛ እንደሆነ ሁሉ ባህሪው ያልተሰራ ሰው አደገኛ ነው፡፡ ባህሪው ያላደገ ሰው  ራሱን ተቆጣጥሮ ሃይሉን በምን ላይ ማፍሰስ እንዳለበት አያውቅም፡፡ ለዚህ ነው ከሃይል ይልቅ ባህሪ ይበልጣል የሚባለው፡፡

ትዕግሥተኛ ሰው ከኃያል ሰው ይሻላል፥ በመንፈሱም ላይ የሚገዛ ከተማ ከሚወስድ ይበልጣል። "ምሳሌ 16፡32"

በህይወታችን ልናሳድገው የሚገባን ባህሪ ትግስት ነው፡፡ እግዚአብሔር በህይወታችን በትጋት እየሰራ ያለው ትእግስትን ነው፡፡

ይህም ብቻ አይደለም፥ ነገር ግን መከራ ትዕግሥትን እንዲያደርግ፥ ትዕግሥትም ፈተናን ፈተናም ተስፋን እንዲያደርግ እያወቅን፥ በመከራችን ደግሞ እንመካለን፤ "ሮሜ 5፡3-4"

ካለ ትእግስት ግን ምንም ነገር ቢኖረን ከንቱ ነው፡፡ ትእግስት ሙሉ እና ፍፁም ለበጎ ስራ ሁሉ የተዘጋጀን ፍፁም ሰዎች ያደርገናል፡፡

ወንድሞቼ ሆይ፥ የእምነታችሁ መፈተን ትዕግሥትን እንዲያደርግላችሁ አውቃችሁ፥  ልዩ ልዩ ፈተና ሲደርስባችሁ እንደ ሙሉ ደስታ 
ቍጠሩት ትዕግሥትም ምንም የሚጎድላችሁ
ሳይኖር ፍጹማንና ምሉዓን ትሆኑ ዘንድ ሥራውን 
ይፈጽም። "ያዕቆብ 1፡2-3"

አዲሱ ሰው በዚ ማንነት ውስጥ የተፈጠረ ደግሞ ያደገ ነው።ስለዚህ በክርስቶስ ኢየሱስ መሆን ይጠቅማል የምንለው ለዚህ ነው።

ሃገር የምታረፈው ታጋሽ መሪ ሲኖር ነው፡ቤተሰብ የሚያርፈው ታጋሽ ሰው መሆን ስንችል ነው፡ሁሉ በዚህ መንፈስ ሲሆን ብዙ ሰላም ይበዛል።ይህን ለማግኘት ደግሞ በክርስቶስ ሆኖ አዲስ ማንነት መያዝ ያስፈልጋል ።
===============================
በቀጣይ ሳምንት
አዲሱ ሰው እና የመንፈስ ፍሬ
ክፍል 5.ቸርነት (Kindness)
===============================
ብሩካን ናችሁ
Goodness of Christ Gospel Ministry

Powered by እዮብ አበራ

#የመንፈስፍሬ #ፍቅር #ሰላም #ደስታ #ትዕግስት#....
900 viewsEjob @ JS, edited  03:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-03 06:00:02
908 viewsEjob @ JS, 03:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-27 06:00:12 ሰላም ቅዱሳን ክፍል ሶስት. ..
እንግዲ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፡ይህ አዲስ ተደርጎ የተፈጠረው ሰው የመንፈስ ፍሬ ደግሞ አልፎም በስጋ ህይወት ላይ የሚገለጥ ህይወት አለው ብለናል።
መነሻ ጥቅስ ፥- ገላ 5፥22
ገላትያ 5 (Galatians)
22፤ የመንፈስ ፍሬ ግን ፍቅር፥ ደስታ፥ ሰላም፥ ትዕግሥት፥ ቸርነት፥ በጎነት፥ እምነት፥ የውሃት፥ ራስን መግዛት ነው።

አዲሱ ሰው እና የመንፈስ ፍሬ
3.ሰላም
Greek translation....eirene
English Translation...peace
አማርኛ ፍቺ.....ሰላም(ረፍት)

እንግዲ ሃዋርያው ጳውሎስ ይሄን eirene or peace የተጠቀመው:-
ጥንታዊ ግሪኮች ጣኦቶቻቸውን የሚጠሩበት ስም እናም የንጉሰ ነገስት ስምም ሆኖ ይታወቃል ቢሆንም በጥንት ጊዜ ይኖሩ የነበሩ ክርስቲያኖች ከጣኦቱ ይልቅ የሚያሳዩት ሰላም ስለነበር ከግሪኮች የተሻለ የመንፈስ ፍሬ ሰላም (eirene) የሚባለው የሚገኘው በክርስቶስ በመሆን ነው የሚል መልክት የያዘ ነው::
የጥንት ክርስቲያኖችን ጠቋሚ ነው።ስለሆነም በዚህ የሰላም ፍሬ የሚመላለስ ሁሉ በክርስቶስ ነው::

ስለዚህ ዛሬም መናገር የምንሻው በሁሉ ስፍራ ያላችሁ በክርስቶስ ያልሆናችሁ; በክርስቶስ የሆናችሁ በዋናነት ይህ ህይወት ይኑራችሁ ስንል በዚህ ህይወት እንድትመላለሱ ነው እንጂ በምድር ባለው ጊዜያዊ የሰው ሰላም፡ የቁሳቁስ ሰላም፡ የመጠጥ ሰላም ውስጥ ግቡ እያልን አደለም።
በመጽሃፍ
ኤፌሶን 2 (Ephesians)
14-15፤ እርሱ ሰላማችን ነውና፤ ...
እንደሚል ክርስቶስ ኢየሱስ ሰላማችን ነው።

በዘመነ አገልግሎቱ ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱ
ዮሐንስ 14 (John)
27፤ ሰላምን እተውላችኋለሁ፥ ሰላሜን እሰጣችኋለሁ፤ እኔ የምሰጣችሁ ዓለም እንደሚሰጥ አይደለም። ልባችሁ አይታወክ አይፍራም።
ይህም እውነት በGreek ፍቺው Eriene የሚል ተመሳሳይ ፍቺ ነው ያለው።
ስለዚህ ወዳጆች ዛሬም የምንላችሁ እውነተኛ የሆነ ሰላምን ለማግንኘት የምንደክም ከመሆን ተቆጥበን ከእምነት በሚሆን ማንነት እውነተኛ ሰላም ማግኘት እንይዛለን።
ይህም ማለት
ለምሳሌ ፡ ነፍሰ ጡር በመውለጇ ሰአት የምታገኘው ሰላም አስቡ
ከእሱ ይበልጥ ከመንፈስ የሆነ ሰላም በስጋ የሚገለጥ ሰላም በሙላት አለው።

መዝሙር 29 (Psalms)
11፤ እግዚአብሔር ለሕዝቡ ኃይልን ይሰጣል፤ እግዚአብሔር ሕዝቡን በሰላም ይባርካል።
ከዚህ ክፍል እንደምናየው ሰው እውነተኛ ሰላምን ማግኘት ይችላል ግን በክርስቶስ በኩል በሚሆን የጌታ ሰላም ነው ።ማንም ይሄን ሰላም መስጠት አይችልም ከእግዚአብሔር ውጪ
ታዲያ ከጌታ ይህን ሰላም ለማግኘት ፡በክርስቶስ ሆኖ አዲስ ፍጥረት መሆን ያስፈልጋል።
በቀጥታ የሚገኝ እግዚአብሔር የለንም ፡በክርስቶስ የሚገኝ እግዚአብሔር ነው ያለን።
ምንም ነገሮቻችሁ
(የግል ህይወታችሁ፥ ስራችሁ ቢሆን፥እጮኝነታችሁ፥ትዳራችሁ፥አመራራችሁ)
በሰላም የተሞላ እንዲሆን በክርስቶስ መሆን ያስፈልጋል።ስለዚህ

ወዳጆቼ አንድ ሰው አዲስ ፍጥረት እንዲሆን ያስፈለገው ከሁኔታ የሚገኝ ደስታን ትቶ ቋሚ ሰላም ውስጥ ለመግባት በክርስቶስ መሆን ያስፈልጋል።

አዲሱ ሰው እና የመንፈስ ፍሬ
ክፍል 4-ትዕግሥት

በቀጣይ ሳምንት ይጠብቁን
ብሩካን ናችሁ።
1.7K viewsEjob @ JS, 03:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-27 06:00:08
1.6K viewsEjob @ JS, 03:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-25 07:01:35
ሁሉ ነገር በክርስቶስ ተፈጠረዋል!
epoiesen(Greek)
እብ 1፡2
ክብር ለኢየሱስ ይሁን
2.4K viewsEjob @ JS, 04:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ