Get Mystery Box with random crypto!

Arat Kilo Media - አራት ኪሎ ሚዲያ

የቴሌግራም ቻናል አርማ horn_african_news — Arat Kilo Media - አራት ኪሎ ሚዲያ A
የቴሌግራም ቻናል አርማ horn_african_news — Arat Kilo Media - አራት ኪሎ ሚዲያ
የሰርጥ አድራሻ: @horn_african_news
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 4.70K

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 18

2022-07-22 14:38:02 የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ወደ ትግራይ የሚጓጓዝ ስድስት ሺ ቶን ማዳበሪያ ለFAO ማስረከቡን አስታወቀ

የኢትዮጵያ ግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በትግራይ ክልል ላሉ አርሶ አደሮች የሚላክ ከስድስት ሺ ቶን በላይ የአፈር ማዳበሪያ ለዓለም የምግብና የእርሻ ድርጅት (FAO) ማስረከቡን አስታወቀ፡፡
በኢትዮጵያ በብቸኝነት ማዳበሪያን ወደ አገር ውስጥ የሚያስገባው ኮርፖሬሽኑ፣ ማዳበሪያውን ለፋኦ፣ ያስረከበው ከአንድ ወር በፊት የግብርና ሚኒስቴር፣ ፋኦ ከኮርፖሬሽኑ ማዳበሪያ እንዲገዛ የሰጠውን ፈቃድ ተከትሎ ነው፡፡
ኮርፖሬሽኑ በየዓመቱ ‹‹ከአቅም በላይ የሆነ አጥረት እንዳይፈጠር›› በሚል ከሚይዘው መጠባበቂያ ላይ በመቀነስ ይኼንን የማዳበሪያ መጠን ለፋኦ ማስረከቡን የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ክፍሌ ወልደማሪያም ተናግረዋል፡፡
ኮርፖሬሽኑ ለፋኦ ካስረከበው የአፈር ማዳበሪያ ግማሽ ያህሉ ኤንፒኤስ (NPS) ማዳበሪያ ሲሆን ቀሪው ዩሪያ ነው፡፡ ፋኦ ኤንፒኤስ ማዳበሪያን ከኮርፖሬሽኑ ወስዶ መጨረሱንና ዩሪያ ማዳበሪያን እያጓጓዘ መሆኑን ዋና ሥራ አስፈጻሚው አስረድተዋል፡፡
ፋኦ ወደ ትግራይ የሚያጓጉዘውን ተጨማሪ ስድስት ሺ ቶን የአፈር ማዳበሪያ ለመረከብ፣ ጥያቄ ማቅረቡን የተናገሩት አቶ ክፍሌ፣ ድርጅቱ ተጨማሪውን ለመግዛት አስፈላጊ ሒደቶችን በማጠናቀቅ ላይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ዋና ሥራ አስፈጻሚው እንደሚያስረዱት ኮርፖሬሽኑ አሁን ያስረከበውንም ሆነ በቀጣይ ለድርጅቱ የሚሸጠውን የማዳበሪያ ሽያጭ ክፍያ ተረክቦ የሸጠውን ያህል ማዳበሪያ ወደ መጠባበቂያው ይተካል፡፡ የመጀመሪያውን ስድስት ሺ ቶን ሽያጭ ክፍያ ለመቀበል በሒደት ላይ ሲሆን፣ ፋኦ ሁለተኛውን ስድስት ሺ ቶን የአፈር ማዳበሪያ እንደሚገዛ የመጨረሻ ማረጋገጫ ሲሰጥ ለመተኪያው የግዢ ሒደት እንደሚጀመር አስታውቀዋል፡፡
ለመተኪያ የሚሆነው ማዳበሪያ ግዢ የሚፈጸመው ከተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስ መሆኑንና በአምስት ቀናት የመርከብ ጉዞ ጅቡቲ ወደብ መድረስ እንደሚችል አቶ ክፍሌ ተናግረዋል፡፡
የተባበሩት መንግሥታት የምግብና የእርሻ ድርጅት (FAO) ከቀናት በፊት ባወጣው መግለጫ፣ የመጀመሪያ ዙር የሆነውን 262 ቶን የአፈር ማዳበሪያ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር በመተባበር ወደ ትግራይ ክልል ማስገባቱን አስታውቋል፡፡ ፋኦ በመግለጫው በመጀመሪያው ዙር ወደ ትግራይ ክልል ያስገባው ማዳበሪያ፣ በክልሉ ያለውን የምግብ ዋስትና ዕጦት አደጋ ለመግታት ከአጋር አካላት ጋር በመሆን ማግኘት የቻለው 19,300 ቶን ማዳበሪያ አካል መሆኑን ገልጿል፡፡
በመጪዎቹ ሳምንታት ከአጋር አካላት ጋር በመሆን 60,000 ቶን ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ ማቀዱን በመግለጫው ላይ ጠቅሷል፡፡ ድርጅቱ በክልሉ ያለውን የማዳበሪያ አቅርቦትና ፍላጎት ለማሟላት የ53 ሚሊዮን ዶላር ጉድለት እንዳለበት አስታውቋል፡፡

[ዘገባው የ‹‹ሪፖርተር›› ጋዜጣ ነው]
467 views11:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-21 17:37:53
የአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ም/ቤት በ20 ሚሊዮን ብር ወጪ በአዲስ አበባ ከተማ ያሉ ረዳት ያጡ ዜጎችንና ዝቅተኛ ደመወዝ ያላቸውን የኩባንያ ሰራተኞችን የሚደግፍ ፕሮጀክት ይፋ አደረገ

‹‹የግሉ ዘርፍ ጥምረት በኑሮ ውድነት ላይ›› የተሰኘው የም/ቤቱ ፕሮጀክት፤ ከ15 ሺ እስከ 20 ሺ ለሚሆኑ የዕለት ጉርሳቸውን መሸፈን ለማይችሉ ዜጎች ያልበሰሉ ምግቦችን ለሁለት ወራት ማከፋፈልን፣ ከ16 ሺ እስከ 24 ሺ ግለሰቦችን ምሳ ማብላትን እንዲሁም በ100 ድርጅቶች ውስጥ በዝቅተኛ ክፍያ ለሚሰሩ የኩባንያ ሰራተኞች ቀለብ ማቅረብን የሚያካትት መርሃ ግብር ነው፡፡

ከዚህ በተጨማሪም ምክር ቤቱ በቅርቡ ረዳት የሌላቸውን ዜጎች ለማገዝ 6.2 ሚሊዮን ብር የሚገመት ድጋፍ ማድረጉን የም/ቤቱ ፕሬዝደንት ወ/ሮ መሰንበት ሸንቁጤ ተናግረዋል፡፡
684 views14:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-21 11:28:33
ከ9 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት የእንቦጭ ማጨጃ ማሽን ወደ ኢትዮጵያ ሊገባ ነው

ከ9 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የሆነበት የእንቦጭ ማጨጃ ማሽን ወደ ሀገር ውስጥ ሊገባ እንደሆነ የዓለም አቀፍ ትብብር ለጣና ደህንነት ማኅበር (Global Coalition for Lake Tana Restoration) አስታወቀ።

ማሽኑ ወደ ጅቡቲ የመርከብ ጉዞ የጀመረ ሲሆን በአምስት ሳምንታት ውስጥ ኢትዮጵያ እንደሚገባ ተገልጿል። ከዚህ ቀደም ሁለት የእንቦጭ ማጨጃ ማሽኖች ወደ ኢትዮጵያ የገቡ ሲሆን፤ በኮሮና ቫይረስ ወረርሺኝ ሳቢያ ፋብሪካዎች በመዘጋታቸው የዘገየው የሶስተኛው ማሽን መገጣጠም ሂደት ተጠናቆ ማሽኑ ወደ ኢትዮጵያ መጫኑ ተነግሯል።

ማሽኑ ለዐማራ ክልል መንግስት የውሃ አካላት ጥበቃና ልማት ኤጀንሲ በነፃ የተበረከተ እንደሆነም ማኅበሩ አስታውቋል። የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርት እና ሎጄስቲክስ አገልግሎት ድርጅት ያለክፍያ በነጻ ማሽኑን ከአሜሪካ እስከ ጂቡቲ የወሰደ ሲሆን የዐማራ ክልል መንግስት ደግሞ ከጂቡቲ እስከ ባህርዳር ከተማ ያለውን የየብስ ትራንስፖርት ወጪ ለመሸፈን ቃል መግባቱም በመግለጫው ተጠቅሷል።
380 viewsedited  08:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-21 11:07:56
የጣሊያኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ማሪዮ ድራጊ ከስልጣን መልቀቃቸውን አስታወቁ

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከስልጣን ለመልቀቅ ቀደም ብለው ያቀረቡት ጥያቄ ውድቅ ሆኖ ነበር። ይሁንና አሁን የጥምር መንግስቱ እንደገና ማንሰራራት ባለመቻሉ ስልጣን መልቀቃቸው ተገልጿል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ማሪዮ ድራጊ፤ ስልጣናቸውን መልቀቃቸውን ለፓርላማው ተናግረዋል ተብሏል።

ከሰሞኑ የብሪታኒያ ጠቅላይ ሚኒስትር ስልጣን መልቀቃቸው የተሰማ ሲሆን የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትርምበተመሳሳይ ከሃላፊነት መልቀቃቸው ይታወሳል።
420 views08:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-19 18:40:20
ሳማንታ ፓወር በዚህ ሳምንት ኢትዮጵያን፣ ኬንያን እና ሶማሊያን ይጎበኛሉ

የአሜሪካ ዓለም አቀፍ የልማትና ተራድኦ ድርጅት (USAID) አስተዳዳሪ ሳማንታ ፓወር በተያዘው ሳምንት ወደ ኢትዮጵያ፣ ኬኒያ እና ሶማሊያ እንደሚያቀኑ ገልፀዋል፡፡
ኃላፊዋ በአገራቱ በሚኖራቸው ጉብኝት ድርቅን ተከትሎ እየተከሰተ ባለው ሰብአዊ ቀውስ ምክንያት የተጎዱ ዜጎችን እንደሚጎበኙ አስታወቀዋል፡፡
ሳማንታ ስለጉብኝታቸው የተናገሩት፣ USAID ለአፍሪካ ቀንድ አገራት 1 ነጥብ 2 ቢሊየን ዶላር ገደማ ድጋፍ መስጠቱን ይፋ ባደረጉበት ወቅት ነው፡፡
ድጋፉ በኢትዮጵያ፣ ኬንያ እና ሶማሊያ ለሚገኙ ዜጎች አስቸኳይ የሰብዓዊ እርዳታ የሚውል መሆኑን ገልጸዋል፡፡
547 views15:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-18 21:38:32 የኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን አስተዳደር ከሰሞኑ በተፈጠረው ግጭት ውስጥ ተሳትፎ ነበራቸው ያላቸውን የስራ ኃላፊዎች ላይ እርምጃ መውሰዱን አስታውቋል።በእርምጃው የተካተቱት የዞኑ ፖሊስ አዛዥ እና የጅሌ ጥሙጋ አመራሮች ናቸው ተብሏል።
Wasu
628 views18:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-17 18:28:54
446 views15:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-11 18:34:27 በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ እና ኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን አዋሳኝ ስፍራዎች ላይ ዳግም ግጭጥ አገረሸ

በአማራ ክልል በሰሜን ሸዋ ዞን ስራ ባለው ኤፍራታ እና ግድም ወረዳ አርሶ አምባ ቀበሌ እና በኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን ጅሌ ጥሙጋ ወረዳ ስራ ባለችው በጤ ቀበሌ ከትናንት ረፋድ ጀምሮ ግጭት መከሰቱን ኢትዮ ነጋሪ ከአካባቢው ነዋሪዎች ሰምታለች፡፡

የአካባቢው ነዋሪዎች እንዳሉት ከትናንት ረፋድ ጀምሮ በሁለቱ ቀበሌዎች አዋሳኝ አካባቢዎች ከፍተኛ የተኩስ ልውውጥ እንዳለ፣ በዚህም ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ ሰዎች መገደላቸውን ተናግረዋል፡፡

የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ስልጠና ሳይቀር በይፋ ሲወስዱ ለአካባቢው ዓመራሮች ብንናገርም የሚሰማን አጥተናል ያሉት ነዋሪዎቹ አሁን ላይ ጦርነት መክፈታቸውን ተከትሎ ነዋሪዎች መኖሪያ ቤታቸውን ለቀው ወደ አጎራባች ወረዳዎች እና ቀበሌዎች በመሰደድ ላያ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

የባሰ ጉዳት ሳይደርስ መንግስት ተጨማሪ ጸጥታ አስከባሪ ሀይል እንዲልክላቸውም ነዋሪዎቹ ጠይቀዋል፡፡

በአካባቢው የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች በስፋት እና በግልጽ እንደሚንቀሳቀሱ የነገሩን ነዋሪዎቹ አሁን ላይ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የሸኔ ታጣቂዎች ወደ መኖሪያ መንደሮች ዘልቀው በመግባት ጥቃት በማድረስ ላይ መሆናቸውንም ተናግረዋል፡፡

ከትናንት ምሽት ጀምሮ የአማራ ልዩ ሃይል ወደ ቦታው የገባ ቢሆንም የሸኔ ታጣቂዎች ብዛት ከፍተኛ መሆኑን ተከትሎ ግጭቱን ማስቆም እንዳልተቻለም ከነዋሪዎቹ ሰምተናል፡፡

የሰሜን ሸዋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታደሰ ገብረፃዲቅ በበኩላቸው በተጠቀሱት ቦታዎች ግጭት መቀስቀሱን ተናግረው ግጭቱ ሳይባባስ ለማስቆም ተጨማሪ ሀይል ወደ ስፍራው መላኩን ተናግረዋል፡፡

በአማራ ክልል በሁለቱ ዞኖች ባለፉት ዓመታት ተደጋጋሚ ጦርነቶች የተካሄዱ ሲሆን አጣዩ ከተማ ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ መውደሟ ይታወሳል፡፡

ከሁለት ወራት በፊት በዚሁ አካባቢ በተፈጠረ ተመሳሳይ ጥቃት በኤፍራታ እና ግድም ስራ ያለችው ሞላሌ መንደር ሙሉ ለሙሉ በኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች መውደሟ አይዘነጋም፡፡
Ethio negari
666 views15:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-11 18:33:39
የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝ ነገ ፍርድ ቤት እንደቀርቡ ቀጠሮ ተይዟል።

ባሳለፍነው ሳምንት በነበረ የችሎት ቀጠሮ አቶ ሀይለማርያም በማንኛውም ሰዓት ወደ ኢትዮጲያ ሲመጡ ተወካያቸው ወይም የሜ/ጀ ክንፈ ዳኘው ጠበቃ ከ48 ሰዓት በፊት ለፍርድ ቤቱ እንዲያሳውቁ እና ምስክርነታቸው እንዲሰማ መታዘዙ ይታወሳል።

በዚህም መሰረት ተወካያቸው ዛሬ ቀርቦ ወደ ኢትዮጳያ መምጣታቸውን ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ሪፖርት አድርጓል።

ፍርድ ቤቱም በነገው ቀጠሮ አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝ በአካል ቀርበው ሜጀር ጀነራል ክንፈ ዳኘው በተከሰሱበት በመርከብ ግዢና በእርሻ መሳሪያ ግዢ ጉዳይ ላይ በተቆጠሩበት የመከላከያ ምስክርነት ቃላቸውን እንዲሰጡ ቀጠሮ ይዟል።

በዚህ ቀጠሮ መሰረት አቶ ሀይለማርያም ነገ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ተብሎ ይታሰባል።
641 views15:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ