2023-03-23 17:44:39
አጎቶቼ ክልል "#አይጠቅማችሁም" ተብለዋል
***
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ከጉራጌ ባለሀብቶች ጋር በአአ ተወያይቷል፣ ስብሰባውም በተናጥል የሚሰጥ ክልል የለም በሚል ተቋጭቷል።
ዶክተር አብይ "#አይጠቅማችሁም" ብሏል።
"የሚጠቅማችሁ ቢሆን ጉራጌን ክልል ማድረግ ቀላል ነበር። ጉራጌ ክልል የማይሆነው ህጉ ስለማይፈቅደው ሳይሆን ስለ ማይጠቅመው ብቻ ነው።" ብለዋል ጠቅላዩ። እንግዲህ እኛ ለአመታት ስንለው ካልሰማችሁ እንኳንም ከጠቅላዩ አንደበት ሰማችሁት።
***
ስብሰባው ምንም እንኳን የጉራጌ ዞን ባለሀብቶች ቢባልም የቀቤና፣ የማረቆና የወለኔ ተወካዮች አልተጠሩም።
በውይይቱ…
ከሌሎች ብሔረሰቦች በተለየ ሁኔታ ጉራጌ ክልል የሚሆንበትን ምክንያት አስረዱ ተብለው አንድም አሳማኝ ሀሳብ ሳያነሱ ቀርተዋል ባለሀብቶቹ። ይልቁንስ ለጉራጌ ህዝብ አብሮነትና አንድነቱን መጠበቁ አስፈላጊው እንደሆነ ሀሳብ ሰጪዎች ጠቁመዋል።
***
የምስራቅ ጉራጌ ባለሀብቶች ምዕራቦችን "ህዝባችንን አዋርዳችኋል" ያሉ ሲሆን እንደ ተለመደው ኮከብ ሆነው ውለዋል። ጉራጌ በማይታወቅበት ሁኔታ በመጥፎ ስም እንዲጠራ ያደረጉት ጥቂት አጀንዲስቶች እንደሆኑ ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲገነዘቡ ጠይቀዋል።
***
ጠቅላይ ሚኒስትሩም ለጉራጌ ጠቃሚው አብሮነት እንደሆነ ደጋግመው የተናገሩ ሲሆን "ጉራጌን በስራው በቅርበት የማውቀው ህዝብ ነው" በማለት በማይረቡ የተልዕኮ አጀንዳዎች ግዜውን ሀብቱንና ክብሩን እንዳያጣ አጥብቀው ተናግረዋል። በተለይም ክልልነትን ምክንያት ተደርገው የተካሄዱ እንቅስቃሴዎች እንድምታቸው የክልልነት አጀንዳ እንዳልነበሩ የመረጃና የደህንነት ጥቆማ እንደሚያሳይ ገልፀዋል።
***
ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ በበኩላቸው የብሔር ፖለቲካና የተናጠል ክልልነት ለጉራጌ ህዝብ አስፈላጊው እንዳልሆነ በመረጃ አስደግፈው ትንተና ያቀረቡ ሲሆን ሁሉም ባለሀብት በሚባል መልኩ በሀሳቡ ተስማምተዋል። ባለሀብቶቹ ጠቅላይ ሚኒስትሩን በተለየ ክብርና ሙገሳ ሲያንበሸብሿቸው ውለዋል በተለይ አቶ ጠንክር የተባለ ሰው የጠቅላዩ ምክትል ነበር የሚመስለው።
***
በመጨረሻም የጉራጌ ባለሀብቶች መሪው ድርጅት ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ከመንግስት ጎን በመሆንና ከጎሮቤት ብሔረሰቦች ጋር በህብረት ሀገራቸውን እንደሚያለሙ ቃል የገቡ ሲሆን ጠቅላዩም በዚህ ሁኔታ መቀጠሉ "አይጠቅማችሁም" ከዚህ በኋላ "ይህ አጀንዳ ተዘግቷል" ብለው ባለሀብቱ ከመንግስት ጎን ቆሞ ልማቱን እንዲያፋጥን ጥሪ አቅርበዋል።
***
ሲጠቃለል፡-የሶሻል ሚድያ የነ ዘሀበሻ ዘመቻና መሬት ላይ ያለው ሀቅ የተለያየ ነው። እንደ ዛሬው የባለሀብቱ ሁኔታ ጉራጌ ነገ ክልል ይሁን ተቀበሉ ቢባሉም እምቢ ክላስተር ይሻለናል የሚሉ ይመስለኛል፣ እውነቴን ነው
**
መረጃውን የሰጡኝን የምስራቅ ኮከቦችን አመሰግናለሁ
ለልማት እንዲመች…
ምስራቅ ጉራጌ ዞን ነው
ምዕራብ ጉራጌም ዞን ነው
ቀቤና ልዩ ወረዳ ነው
ማረቆ ልዩ ወረዳ ነው
ወለኔ ብሔረሰብ ነው
605 viewsHabib Kedir, 14:44