Get Mystery Box with random crypto!

Habib Kedir

የቴሌግራም ቻናል አርማ habib_kedir — Habib Kedir H
የቴሌግራም ቻናል አርማ habib_kedir — Habib Kedir
የሰርጥ አድራሻ: @habib_kedir
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 3.93K

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2023-03-27 09:32:24
የዶክተር አብይ የወልቂጤ መድረክ ሙሉ ውይይት
911 viewsAdu Emru, 06:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-27 04:20:16
905 viewsHabib Kedir, 01:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-27 02:08:32 የወደቀን እናንሳ፣ ኸይር ስራ እንስራ
የረመዳን ሰደቃችንን መንቀሳቀስ ለማይችለው፣ ለታመመው ወንድማችን፣ ለታላቁ ባለውለታችን እናድርግ
መሀመድ ሸመድያን(መሀምድ ቡሌ)
***
ዛሬ የቀቤና ብሔረሰብ የምንለው መጠርያ በብዙ ታላላቆቻችን ትግልና መስዋዕትነት ጸንቶ የቆየ ነው።
በ1976 የህዝባችን ጉዳይና መጻኢ እጣ ፈንታ አሳስቧቸው ከተንቀሳቀሱ ታላላቆቻችን አንዱ ነው መሀመድ ቡሌ። በወቁቱ በቀቤና የመጀመርያ የትግል ችቦ የሆነውን የምክክር ኮንፈረንስ እና የወጣቶች ግንኙነት በግንባር ቀደምትነት መርቷል። በውይይቱ ጥናታዊ ጹሁፍ በማቅረብ ህዝባችን ለነጻነቱ በሚታገልበት ሁኔታ ላይ አቅጣጫ ሰጥቷል
በደርግ አገዛዝ ወቅት በየአመቱ በሚከበረው የመስከረም 2 ክብረ በዓል የቀቤና ኪነት ቡድንን በመድገፍና በመምራት የቀቤና ብሔረሰብ ባህሉ፣ ቋንቋው፣ ታሪኩና ወጉ እንዳይጠፋ ከአዲስ አበባ እየተመላለስ ትልቅ መስዋዕትነት ከፍሏል
ከደርግ ውድቀት በኋላ የቀቤና ህዝብ የነጻነት ትግሉን ያቀጣጠለው ድርጅት ቀብዴድ ሲመሰረት ከብርቱ አባቶቻን ጋር በመሆን በሀሳብና በአካል ተንቀሳቅሶ ደግፏል
የቀቤና የምንግዜም ታላላቅ አባቶቻችን እነ ሀጅ ፈትሁዲንና ሀጅ አህመደል ሀዲ በ1985 አዲስ አበባ ድረስ መጥተው የቀብዴድ ቅርንጫፍ ሲያቋቁሙ ኮሚቴ በመሆን ተመርጦ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ዋና ሰብሳቢ በመሆን በትጋት ህዝቡን አገልግሏል።
መሀመድ ቡሌ በኢትዮጵያ ሬድዮ የቀቤንኛ ቋንቋ አዘጋጅ የነበረው ጀግናው ጋዜጠኛ ሙባሪክ ሙደሲር ለስልጠና ሲሄድ እሱን ተክቶ ከ1986 እስከ 1987 በኢትዮጵያ ሬድዮ የቀቤንኛ ቋንቋ አዘጋጅና አቅራቢ በመሆን የቀቤና ብሔረሰብ ቋንቋ እንዲጎለብትና ተደራሽ እንዲሆን ለፍቷል።
በ1987 የቀቤና ህዝብ በጉራጌ ዞንና በጎሮ ወረዳ መደራጅቱን በመቃወም በ28 ቀበሌ የሚገኘው ቀቤና ግብር አልገብርም ብሎ ትግሉን ሲያቀጣጥል ከአዲስ አበባ ድረስ በመሄድ የህዝቡን እንቅስቃሴ መስመር በማስያዝ በታሪክ ለመጀመርያ ግዜ የቀቤና ተወካዮች በመዋቅሩ ተካተው ምክር ቤት እንዲገቡና ትግሉ ህጋዊ መስመር እንዲይዝ ትልቅ መስዋዕትነት ከፍሏል።
የኢትዮጵያ ህገ መንግስት በቀቤንኛ ቋንቋ እንዲተረጎም የብሔረሰቦች ምክር ቤት በጠየቀው መሰረት በመተርጎምና በማስተባበር ከጀግና ወንድሞቹ ከዘይኑ አክመልና ሙዜ ጋር በመሆን 44 ገጽ ለህትመት እንዲቀርብ በማድረግ ለፌደሬሽን ምክር ቤት(አልማዝ መኮ) አድርሷል።
የደቡብ ብሔረሰቦች አጠቃለይ እንቅስቃሴ ወደ ሀዋሳ ከዞረ በኋላ ብዙ ግዜ የቀቤና ህዝብን መብት በሚመለከቱ ጉዳዮች ላይ በመሳተፍ ሀዋሳ ድረስ በመመላለስ መርቷል፣ አስፈጽሟል።
በ1991 ወደ ሳውዲ አረቢያ ከሄደም በኋላ የቀቤና ብሔረሰብ እድር ጠንካራ እንዲሆን በመደገፍ ከፍተኛ እንቅስቃሴ አድርጓል።
ታላቁ የቀቤና ልማት ማህበር በሳውዲ ሲመሰረት መድረክ የመራው ይህ ጀግና ወንድማችን ነው። ልማት ማህበሩ ተቋቁሞ በሁለት እግሩ እንዲቆምና እውን እንዲሆን ትልቅ መስዋትነት ከከፈሉ ወንድሞች ውስጥ ቀዳሚው ነው።
በአጠቃላይ በሳውዲ ቆይታው የቀቤና ህዝብ በሚገጥሙት ኩነቶች ሁሉ መድረኮችን በመምራት፣ በኢቲቪና በተለያዩ ሚድያዎች እንዲቀረጹና እንዲተላለፉ በማድረግ በቆንጽላና በኤንባሲዎች በመገኘት፣ የተቸገሩትን በመርዳትና በማስተባበር፣ የተጣሉትን በማስታረቅ ለህዝቡ ያለውን ፍቅር በተግባር የገለጸና ከፍተኛ ዋጋ የከፈለ ጀግና ነው።
በአጠቃላይ ታላቃችን መሀመድ ቡሌ አንድም ቀን ለራሱ ያልኖረ፣ ሁል ግዜም ስለ ህዝቡ ከፍታና ነጻነት የሚጨነቅ፣ አርቆ አሳቢና ባለ ብሩህ አዕምሮ ጀግናና ደፋር ነበር።
አሁንስ?
አሁንማ ያ ጀግናና ታታሪ ለሰው አዛኝና ሩሁሩህ ሰው ታሞ ቤት ከዋለ አመታት ተቆጥረዋል፣ መንቀሳቀስ አይችልም ውሎ አዳሩ ዊልቸር ላይ ሆኗል። እራሱን ችሎ መጸዳዳት አይችልም። ህመሙ ከባድ በመሆኑ በየወሩ መድሀኒት ያስፈልገዋል በዊልቸር መጸዳጃ እንኳን ለመድረስ የተስተካክለ ቤትና ግቢ የለውም።
የልጆች አባት ነው፣ በማረፍያ እድሜው በሰው እጅ ወድቋል
መድሀኒቱ ውድ ከመሆኑም ባሻገር በየግዜው ጥቁር አንበሳ መመላለሱም ወጪው ከፍተኛ ነው
***
ይህን ለህዝቡ ታላቅ ውለታ የዋለ ዋርካ ሰው የመጨረሻ ዘመኑን በደስታ ያሳልፍ ዘንድ ማድረግ የሚገባን ሁለት ነገር አለ
1ኛ የሚኖርበትን ጠባብ አንድ ክፍል ቤት ማሻሻል። ተሸክማ መጸዳጅ የምትወስደው የልጆቹ እናት ባለቤቱ ናት፣ ይህን ለማስቀረት ደህና ዊልቸር ኖሮት በተስተካከለ ግቢ እንዲንቀሳቀስና መጽዳጃ በዊልቸር እንዲሄድ በማድረግ ባልቤቱ ተሸክማ እንዳትወስደው ማድረግ
2ኛ የህክምና ወጪውን በመሸፈን ጥሩ ህክምና እንዲያገኝና ቤተሰቦቹ እንዳይራቡ ድጋፍ ማድረግ
ለዚህ የሀገር ባለውለታና ታላቅ ሰው ይህን ማድረግ አያቅተንም ግዜው ረመዳን ነው መሀመድ ቡሌ ደጅ ጠንቶ የሰው እጅ አይቷል፣ እርዱኝ ብሏል። የዘንድሮ ሰደቃችንን ለሱ እናውል እንደ ህዝብ ከወደቅንበት ለማንሳት የታገለን ብርቱ ሰው እኛ ከወደቀበት እናንሳው
በየ ሀገሩ የምትገኙ የቀቤና ተወላጆች አስተባብሩ
#ሼር በማድረግ ለደጋግ ኢትዮጵያዊያን አድርሱ
***
አስተባባሪ ኮሚቴ ተዋቅሯል
በጣም በምትወዷቸውና በምታምኗቸው ታላላቅ ሰዎች፣ አካውንት ተከፍቷል።
1 ኢማም ሸምሱ አስፋ
2 ሀጅ ረውነቅ ሰማን
3 ኑረዲን አህመዲን(አሊ)
ንግድ ባንክ 1000532001524
Iklas ዳሽን 2943842990911
***
የኮሚቴዎች ስልክ
1 አሊ(ኑረዲን) 0900830529
2 ኢማም ሸምሱ 0955328641
3 ሼህ ረውነቅ 0938959926
የራሱ የመሀመድ ቡሌ 0910650822
እኔንም በውስጥ አናግሩኝ
ደግ ደጉን እናስብ
በጎ በጎውን እንስራ
መልካምነት መልሶ ይከፍለናልና
ሰውን ለመርዳት ደግሞ ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው
***
የበጎ ተግባር ማስተባበርያ የቴሌግራም ግሩፕ ተቀላቀሉ
https://t.me/Yosisi_Charity
ለማስተባበር ተብሎ የተከፈተውን የዋትስ አፕ ግሩፕ በሚቀጥለው ሊንክ ተቀላቀሉ https://chat.whatsapp.com/JyQbadxGkEoDFRpITDKjsT
927 viewsHabib Kedir, 23:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-26 17:59:01
የአምባሳደር ተስፋዬ ሀቢሶ የእውቅናና የሽልማት ፕሮግራም አዲስ አበባ በብሉ ስካይ ሆቴል ተካሂዷል
አምባሳደር ተስፋዬ ዘመናዊ መኪና እና የ1,000,000 ብር ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
***
አምባሳደርን በመሸለሙ ሂደት አስተዋፅዖ በማድረጋችን ቀቤና ተመስግኗል።
እኔም በፕሮግራሙ  ህዝቤን ወክዬ ተገኝቼ ከትላልቅና ግምቱ ሰዎች ልምድ ቀስሜአለሁ፣ አምባሳደሩ ስለ ህዝባችን ደግነት አውርተው አይጠግቡም።
ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስን ጨምሮ ትላልቅ ሰዎችና ባለስልጣናት እንዲሁም ሚድያዎች ፕሮግራሙን ታድመዋል።
አምባሳደር ተስፋዬ ሃቢሶ ለአገር ላበረከቱት ዘርፈ ብዙ አስተዋፅኦ ነው እውቅና የተሰጣቸው
***
በዕለቱ በመርሀ ግብሩ ላይ የተገኙት የአከባቢው ተወላጆች እና የዕዉቅናና ሽልማት አስተባባሪ ኮሚቴዎች እንደተናገሩት አምባሳደር ተስፋዬ ሃቢሶ በሽግግር መንግሥት ኮንፈረንስ የከምባታ ጠምባሮን ህዝብ ወክለው ማንም ደፍሮ ባልቀረበበት ሁኔታ እንደሌሎቹ ሳይሸማቀቁ የተገኙና ቀጥሎም የሽግግር መንግሥት የተወካዮች ምክር ቤት ዋና ፀሃፊና አባል ለመሆን የበቁ ብቸኛ ከምባታ በመሆንና ሰላማዊ የፖለቲካ ትግል በማካሄድ በሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ መንገድ ለውጥ እንዲመጣ ካደረጉ ሰዎች አንዱ በመሆናቸው እውቅናና ሽልማት ለመስጠት መነሳሳታቸውን ገልፀዋል።
***
ሽልማቱን  የተረከቡት አምባሳደር ተስፋዬ ሃቢሶ በበኩላቸው በተሰጣቸዉ ዕዉቅናና ሽልማት መደሰታቸውን ገልፀዉ የተሰጠቸው እውቅናና ሽልማት በቀጣይ ለሌሎች መልካም ትምህርት እንደሚሆን ገልጸዋል።
በፕሮግራሙ ላይ የታደሙት የዕለቱ የክብር እንግዳ ክቡር አቶ መለሰ አጭሶ ተወካይ እንደተናገሩት  አምባሳደር ተስፋዬ ሃቢሶ "እንደ አገር በተለያየ ዘርፍ ካበረከቱት አስተዋጽኦ አንጻር እውቅናና ሽልማቱ ይገባቸዋል" ብለዋል።
***
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል
#ቀቤና_ልዩ_ወረዳ
1.0K viewsHabib Kedir, 14:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-26 13:54:08
ምንኛ ያማረ አገላለፅ
የትናንቱ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የወልቂጤ መድረክ ማሳረግያ ነው። ለአጎቶቼ #እንደ_ህዳር_አህያ_አትሁኑ የሚለው መልዕክት። ዶክተር አብይ የሚገርም አገላለፅ ነው የተጠቀመው
ምን ማለት ነው? ለሚለው ይህን አጭር ቪድዮ ተመልከቱ የህዳር አ * ያ
****
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል
#ቀቤና_ልዩ_ወረዳ
1.1K viewsHabib Kedir, 10:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-26 12:23:08
ከፊል ፅንፈኞች ቢያሳፍሩንም ጥሩ የሰሩም አሉ
በትናንትናው የጠቅላይ ሚኒስትሩ የወልቂጤ አቀባበል
የቀቤናው ጎላ ብሎ ታየ እንጂ የአበሽጌ ወረዳም አቀባበል አድርጓል።
ክብር ለሚገባው ክብር እንሰጥ
1.1K viewsHabib Kedir, 09:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-26 01:15:27
ዛሬ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ
"ሰብሩ ውሀ እየጠየቃችሁ ቧንቧ አትስበሩ" ብሏል።
ካላመናችሁ ቪድዮውን አድምጡ
548 viewsHabib Kedir, 22:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-25 22:06:08
792 viewsAdu Emru, 19:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-25 22:05:02 የዛሬ የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ
የወልቂጤ መድረክ አጭር መረጃ
***
ወደ ወልቂጤ አመጣጣቸው በጉራጌ ዞን ከአደረጃጀት ጋር በተያያዘ በነበረው ችግር ዙርያ ውይይት ለማድረግና መፍትሄ ለመሻት ነበር
በአጭሩ ወደ ዞኑ የሄዱት ህዝቡን በማክበር ነው
ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር የክልል ፕሬዝደንቶች አቶ ሙስጠፌ ከሶማሌ፣ አቶ አወል ከአፋር፣ አቶ ሽመልስ ከኦሮሚያ ሲሆኑ የተከበሩ አደም ፋራህ የፓርቲው ም/ፕሬዝደንትና የት/ሚንስትሩ ፕ/ር ብርሀኑ ነጋም አብረዋቸው ነበሩ።
***
እነዚህ የሀገር መሪዎችና ከፍተኛ ባለስልጣናት አክብረውት የመጡት ከፊል የወልቂጤ ህዝብ በሩን ዘግቶ እንግዶቹን ለማሳፈር የሞከር ቢሆንም በከተማውና በዙርያው የሚገኘው አርቆ አሳቢ የቀቤና ህዝብ አደባባይ ወጥቶ በመቀበል እንደ ተለመደው ከተማውንና ዞኑን ከሀፍረት ታድጓል።
በሀገራችን፣ በባህላችን በርካታ በደል ያደረሰብህ ሰው እንኳን ቤትህ ቢመጣ በታላቅ አክብሮት ተቀብለህ ትሸኛለህ።
እንደ ግሌ በቀቤና ህዝብ እጅግ ኮሬቻለሁ። በአንፃሩ በአጎቶቼ አፍሬአለሁ፣ የምሬን ነው።
ነውር ተግባር ነው የፈፀሙት
***
ጠቅላይ ሚኒስትሩና እንግዶቹ ወልቂጤ ሲደርሱ በርካታ የቀቤና ተወላጅ ባነር ይዞ አቀባበል በማድረግ አሜተኤሳ እንኳን ደህና መጣህ ያለው ሲሆን፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የመኪና #መስታወታቸውን ዝቅ አድርገው ሰላምታ በማቅረብ ህዝባችንን አመስግነዋል። ከጎናቸው ላለ ሰው "ይህ ህዝብ የማውቀው ጨዋ ህዝብ ነው" ሲሉ ተደምጠዋል።
***
ወደ መድረኩ ስመለስ በእለቱ የመጀመርያው እድል ወሳጅና ተናጋሪ የቀቤናው ጀግና ወንድማቾን እድሪስ ሲሆን ቀቤና ከምርጫው ግዜ ጀምሮ ከመንግስት ጎን ቆሞ ሀገር ሰላም እንዲሆን መስዋዕትነት መክፈሉን ገልፆ ከክልልነት ጥያቄ ጋር ተያይዞ በጉራጌ ዞን ያለውን ጫፍ የወጣ ፅንፈኝነት በዝርዝር በመጥቀስ መንግስት ህግ እንዲያስከብር ጠይቋል፣ በተጨማሪም የቀቤና ህዝብ የመንግስት አቅጣጫ የሆነውን ክላስተርን በመደገፉ የሚደርሱ ትንኮሳዎች እንዲቆሙና የቀቤና ህዝብ የጠየቀው እራስን በራስ የማስተዳደር ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጠይቋል።
***
በመድረኩ የማረቆ ጀግና እህታችን የጉራጌ ዞን ከምስረታውና ከስያሜው ጀምሮ ችግሮች እንዳሉበትና እጅግ ጨቋኝ ዞን እንደሆነ በመጥቀስ በዞኑ የማረቆ ህዝብን ስቃይ በሚያምር ሁኔታ አቅርባለች። የማረቆ ሞትና መፈናቀል፣ የልዩ ወረዳ ጥያቄ፣ የ9 ቀበሌዎች የወሰን ጉዳይ መፍትሄ እንዲሰጥና ከጨቋኙ ዞን ማረቆ፣ ቀቤናና ወለኔ ነፃ እንዲወጡ ጠይቃለች
***
ከጉራጌ ተወካዮች እንደ ተለመደው የወልቂጤ ማካለል ጉዳይ፣ የታሰሩ ሰዎች ጉዳይ፣ የመሰረተ ልማትና የኢንዱስትሪ ፓርክ ጥያቄ እንዲሁም ክልል አሁን ካልተሰጠ መች እንደሚሰጥ ይነገረን የሚሉ ጥያቄዎችን አንስተዋል።
***
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የጉራጌ ህዝብ የሚገባቸውን ክብር ቢነፍጋቸውም መድረክ አያያዛቸውና አመለካከታቸው እጅግ የተለየ ነበር። በንግግራቸው ለጉራጌ ህዝብ ክብር ስላላቸው መምጣታቸውን ገልፀው፣ ወቅቱ በሙስሊሙም በክርስትያኑም የፆም በመሆኑ ሰላም ማውረድና አንድነት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል። ከክልልነት ጋር በተያያዘ አሁን የሚመለስ የተናጠል ክልል እንደሌለና ህዝቡ አብሮነትና አንድነት ላይ እንዲሰራ ጥሪ አድርገዋል። በውይይቱ ከዶ/ር አብይ በተጨማሪ አቶ ሽመልስና አቶ ሙስጠፌ ለጉራጌ ዞን ህዝቦች ያላቸውን ፍቅርና ክብር ገልፀዋል።
***
እኔ በመጨረሻም እላለሁ የቀቤና ህዝብ ሆይ በልጆችህ ልትኮራ ይገባል። ቀቤና እንግዳ በመቀበልና የአላዋቂዎችን አይብ በመሸፈን አይደለም ወልቂጤና አከባቢው አጠቃላይ ጉራጌን ከሀፍረት ጠብቀሀል። በአባቶችህ ምክር፣ በሙሁራን ምክክር፣ በአመራሮች ቁርጠኝነትና በህዝባችን ታዛዥነት ቀቤና ዛሬም ከፍ ብሎ ውሏል። የመጡ ከባድ እንግዶችንም ያለ ምንም ቅሬታ በክብር ሸኝተሃል ቀቤና።
እንግዲህ ከእንደዚህ አይነት መሰሪ ሴረኞች ጋር ለዘመናት በትዕግስት አብሮ መኖር ምን ያክል ጥበብ እንደሆነ የኢትዮጵያ ህዝብና መሪዎች ይረዳሉ።
በቅርቡ ቀቤና ነፃ ይወጣል
***
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል
#የቀቤና_ልዩ_ወረዳ
801 viewsAdu Emru, 19:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-25 14:37:07
982 viewsAdu Emru, 11:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ