2023-03-07 20:27:46
ይህን አይቶ ማለፍ ይከብዳል
ሼር አድርጉት፣ አስተባብሩ፣ ለደጋጎች አድርሱ
***
በየቤቱ ያለውን ችግር ዞር ዞር ብላችሁ ብታዩ በጣም ብዙ አሰቃቂ ጉዳዮች አሉ። በስልክና በውስጥ መስመር በርካታ የተቸገሩ ሰዎችን አገኛለሁ።
የአንዳንዶቹ ችግር እጅግ ልብ ይሰብራል
አዕምሮን ይረብሻል
***
በሀኪሞች ካልታከምክ ትሞታለህ የተባለ ሰው፣ "ገንዘብ አጥቼ ቀኔን እየጠበቅኩ ነው" ቢላችሁ ምን እንደሚሰማችሁ አላውቅም።
መሬማ አብዲ ትባላለች
የሁለት ልጆች እናት ስትሆን፣ በልብ ህመም ቤት ከዋለች አመት ሆኗታል።
***
የጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ለልብ ቀዶ ጥገና ወረፋ ቢያሲዛትም ከሷ የቀደሙ በርካታ የልብ ህሙማን በመኖራቸው፣ በህይወት ለመትረፍ የግል አማራጭ እንድትወስድ ተነግሯታል።
መሬማ እንኳን በግል ልትታከም እንደ አባትና እናት ሆና የምታሳድጋቸውን ልጆች ይዛ የምትቀምሰው የላትም። በሰው እጅ ወድቃለች፣
የልብ ህመሙ ከግዜ ወደ ግዜ እየባሰባት መንቀሳቀስና መተንፈስ አትችልም። ሁለቱን ጨቅላ ልጆች ከጎና አስቀምጣ አላህን ከመለመን ውጭ አማራጭ የላትም
የልጅን አይን አይን እያዩ ሞትን መጠባበቅ፣ ከባድ ሀዘን ነው
***
ከጎኗ ያሉ ቤተሰቦችና ሌላ ሰዎች አመት ሙሉ የቻሉትን ሁሉ አድርገዋል። አሁን ግን አቃታቸው። በመንግስት በኩል እድል ከገጠማት እስከ 200 ሺ በግል ከሆነ እስከ 700 ሺ ብር ለህክምና ያስፈልጋታል።
***
አሳክመን ሰበብ ሆነን እናድናት ወይስ ህክምና አጥቷ ሞቷን ትጠብቅ? ሞትን የተጋፈጠችው እሷ ብቻ ሳትሆን ልጆቹም ጭምር ናቸው፣ በጨቅላ እድሜ እናታቸውን አጥተው ምንስ፣ ማንስ መጠጊያ አላቸው?
ሰው ሞልቶ በፈሰሰበት ሀገር እናታቸው ማታከሚያ አጥታ ብትሞትስ ምን ተብሎ ይነገራቸዋል?
***
እናንተ ደጋግ ሰዎች ከኔ የሚጠበቀው የገጠመኝን ፈተና ለናንተ ማጋራት ነው፣ ልባችሁ የራራ በምታመልኩት ፈጣሪ ይሁንባችሁ የተቸገሩትን እርዱ።
ከራሳችሁ ከፍ ያለውን ሳይሆን ከናንተ በታች ያሉትን፣ ተመልከቱ። በትንሽ ህክምና መዳን የሚችሉ ብዙ ተጎጂዎች አሉ
መሬማን ለመርዳት በሶስት ሰው አካውንት ተከፍቷል
1 አብዲ አሊያ
2 ካፉ አስፋው
3 ሀያት ጀማል
አካውንት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000528120214
የኮሚቴዎች ስልክ: 0913680407/0910849303
ቀጥታ እሷን ማናገር ወይም መጠየቅ የምትፈልጉ
ስልክ 0926537099
አሁን ያለችው አአ አጃምባ(ትውልዷ ቀቤና ወረዳ ቢሸዋ ሸፋቲ ቀዬ)
****
ነብሳያችንን እናሸንፍ
ለማንኛውም ድጋፎቾ ማስተባበርያ ቴሌግራም ቻናል ተቀላቀሉ https://t.me/Yosisi_Charity
ደግ ደጉን እናስብ
በጎ በጎውን እንስራ
#መልካምነት_መልሶ_ይከፍለናልና
***
910 viewsHabib Kedir, edited 17:27