Get Mystery Box with random crypto!

Habib Kedir

የቴሌግራም ቻናል አርማ habib_kedir — Habib Kedir H
የቴሌግራም ቻናል አርማ habib_kedir — Habib Kedir
የሰርጥ አድራሻ: @habib_kedir
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 3.93K

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2023-03-15 22:27:53
711 viewsHabib Kedir, 19:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-15 22:27:46 የቀቤና ብሔረሰብ ህልውና እንዲጠፋና እንዲቀጭጭ የማድረግ ጥረት…
#ይበቃል_3
***
በኢትዮጵያ ህገ መንግስት አንቀፅ 39 ንኡስ አንቀጽ 5 ላይ አንድን ብሔረሰብ ከሚኖርበት አከባቢና መልከዓ ምድር ለይቶ ማየት እንደማይቻል ይደነግጋል፡፡ በዚሁ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ 3 እና አንቀፅ 98 ንዑስ አንቀፅ 1፣ በቂ የሆነ የአካባቢው አስተዳደር በየደረጃው በሚዋቀርና በሚደራጅ እንዲሁም በህዝብ ቀጥተኛ ተሳትፎ እና አካባቢውን በማልማት ለሀገር ልማት የበኩሉን አስተዋፅኦ ያበረክት ዘንድ መብት ይሰጣል፡፡
**
ይሁን እንጂ እነዚህ መብቶች በቀቤና ብሔረሰብ ላይ በጉራጌ ዞንና በወልቂጤ ከተማ አስተዳደር በኩል ተግባራዊ አይደረጉም፡፡ ለነዚህም በቂ መገለጫዎችንና ማብራሪያዎችን ማቅረብ ይቻላል፡፡ ከብዙ በጥቂቱ ዋና ዋና የሆኑትን ለማንሳት የምሞክር ሲሆን የማቀርባቸው ጉዳዩች በሃቅ ላይ የተመሰረቱና ማንኛውም ንፁህ አዕምሮ ያለው ሰው ሊያረጋግጣቸው የሚችላቸው ጉዳዮች መሆናቸውን አበክሬ ለማሳሰብ እወዳለሁ፡፡
***
የመጀመሪያው የብሔረሰቡን ህልውና የማጥፋት ዘመቻ የተጀመረው በ1994 ዓ.ም ሲሆን በወቅቱ ቀድሞ የነበረው ጎሮ ወረዳ ለሁለት ተከፍሎ ቀቤና ወረዳ እና አበሽጌ ወረዳ ተብሎ እንዲደራጅ ተወስነ:: ከውሳኔው ማግስት ጀምሮ ብሄረሰቡ ራሱን በራሱ ለማስተዳደር ያገኘውን ህገ-መንግስታዊ መብት ለማሳጣት በነ መኩርያ ሃይሌ ይመራ የነበረው የጉራጌ ዞን አመራር ቀቤና ወረዳ የሚባል ስያሜ እንዳይኖር ከፍተኛ ጥረትና ጫና ቢያሳድርም ከወረዳው ህዝብ ጋር በተደረገ ውይይትና ህዝበ ውሳኔ ቀቤና ወረዳ ሆኖ እንዲቀጥል ተደረገ::
***
ቀቤና የሚል መጠርያ እንዲኖር የማይፈልጉ የጉራጌ ዞን አመራሮች ቀቤናን ከካርታ ለመፋቅ የሚያደርጉትን ጥረት በማጠናከር የቀቤና ባህልና ታሪክን በማቀጨጭ ህልውናው እንዲጠፋ ማድረጋቸውን በመቀጠል በ1999 ዓ.ም የቀቤና ህዝብ ሳያውቀውና ሳይወያይበት በቀቤና ወረዳ የሚገኘውን ቆላካ ባዳ የሚባለውን ቀበሌ ሙሉ በሙሉ በመዝለል ቸሀ ወረዳ ካለ ጉብሬ ከሚባል የገጠር ማዕከል ጋር ወልቂጤን በአንድ ማስተር ፕላን ለማስተሳሰር እቅድ ወጠኑ፥ ይህ የሚያሳየው እራሳቸውን ችለው መልማት ያለባቸውንና በ15 ኪሎ ሜትር ርቀት ያሉ ሁለት ከተሞችን በማስተሳሰር ስም ሉዓላዊ የሆነን ወረዳ መብት በመርገጥ ቋንቋውን ለማቀጨጭና ባህሉን ለማጥፋት የሚደረገውን ጥረት ነው፡፡
***
ቀቤና የወልቂጤ ከተማ በዕቅድና በፕላን እንድትመራ የሚፈልግና የሚመኝ ቢሆንም ይህንን ብሔረሰብ ለማጥፋት በማቀድ አንድ የገጠር ቀበሌ በመካከል እያለ እሱን አልፎ ሌላ መንደሮችን በማስተር ፕላን እንዲካተቱ መደረጉና ህዝብ ሳያውቅና ሳይወያይ እጅግ በጣም ስፋት ያለውን ቀበሌ ለማካለል መሞከር የጉራጌ ዞንን አምባገነንነት ቁልጭ አድርጎ ያሳያል፡፡
***
ይህን 7300 ሄክታር ስፋት ያለውና እንደ አዳማና ሀዋሳ ካሉ የሃገራችን ትልልቅ ከተሞች የሚስተካከል ስፋት ያለው መሬት በዕቅዳቸው ውስጥ እንዲካተት ማድረጋቸው የረዥም ጊዜና ሁሉን አካታች ፕላን ለማዘጋጀት ካላቸው ቅን አመለካከት ሳይሆን የብሔረሰቡን ቋንቋና ባህል በማቀጨጭ በሂደት ብሔረሰቡን የማጥፋት ከረዥም ጊዜ ዕቅድ የመነጨ ለመሆኑ ህብረተሰቡ ሳይሳተፍ በዕቅድ ያዘጋጁት ፕላን ማሳያ ነው፡፡
***
ይበቃል_4 ቻሌንጅ ይቀጥላል…
ሁላችሁም ፁሁፉን ሼር በማድረግና ምስሉን ፕሮፋይል በማድረግ ዘመቻውን ተቀላቀሉ።
የቀቤና ህዝብ የልዩ ወረዳ ጥያቄ ለምን እንዳቀረበና አስፈላጊነቱን ለሁሉም ግንዛቤ እንፈጥራለን

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል
#ቀቤና_ልዩ_ወረዳ
740 viewsHabib Kedir, 19:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-15 15:22:00
ይህን ድልድይ ተጋግዞ ማሰራትና ህዝባችን በገዛ አቅሙ ማልማት እንደሚችል ማሳየት ይገባል
***
የቀቤና ወረዳን ከሙህር አክሊል ወረዳ ጋር የሚያገናኝ የ2 ኪሎ ሜትር የጠጠር መንገድ እየተስራ ይገኛል። የቀቤና ወረዳ አሰተዳደር እና የመንገድ ልማትና ትራንስፖርት ጽ/ቤት ከደቡብ መንገዶች ባለስልጣን ጋር በመተባበር ይህን የጥርጊያ መንገድ እያሰሩት ነው፣ 2 ኪሜ ትንሽ ቢመስልም ከህዝቡ ችግርና ከአከባቢው አስቸጋሪነት አንጻር ጥሩ ነው።
***
መንገዱ አገልግሎት እንዲስጥና ሁለቱን ወረዳዎች እንዲያገናኝ በመሀል ያለው ድልድይም መሰራት አለበት ለዛ ደግሞ የሁሉም ርብርብ ያሻል፣ ባለሀብቶችና የእናቶችን ችግር የምንረዳ ሁሉ እገዛ ማድረግ አለብን።
ይህ መንገድ ከደቀንሺ-ሞላ ቀበሌ ወደ ዘናበነር፣ ሴባ፣ ዳኛሴ፣ ወራፉና፣ አጉስቄ እና ጭሬት ቀበሌዎችን የሚያገናኝ መንገድ ነው ድልድዩም ከጎሮቤት ወረዳ ያገናኛል።
***
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል
#ቀቤና_ልዩ_ወረዳ
847 viewsHabib Kedir, 12:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-14 21:17:41
859 viewsHabib Kedir, 18:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-11 20:05:51
የቀቤና ህዝብ ታላቅ ህዝብ ነው
***
ያከበረውን ያከብራል
የሚወደውን እጥፍ ይወዳል
ያነገሰውን ያነግሳል
በጣም የሚገርመው ነገር ህዝባችን የሚጠላውን አይጠላም። የሚንቀውን አይንቅም። ይልቁንስ ወደ ቀልቡ እንዲመለስ ዱኣ ያደርግልታል፣ ይታገሳል።
***
ይህ ህዝብ ነፃነት ይገባዋል
ለዛ ደግሞ አስፈላጊውን መስዋዕትነት እንከፍላለን
ከፍ ማለትን የሚሻ ዝቅ ብሎ መስራት ግዴታው ነው
ህዝቤን ያለ ምክንያት በፍቅር እወደዋለሁ
ከቀቤና በመፈጠሬ እድለኛም ደስተኛም ነኝ
በጣም ደስተኛ ነኝ፣ ለምን ብሎ ማንም እንዳይጠይቀኝ።
521 viewsHabib Kedir, 17:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-10 22:32:40
እውነት ተናጋሪዎችን ያብዛልን
***
ሰሞኑን በወልቂጤ ሁሉም ክፍለ ከተሞችና አጠቃላይ በጉራጌ ዞን ህዝባዊ መድረኮች እየተካሄዱ ነው።
ዘግይቶም ቢሆን ህዝብ እውነታው ገብቶታል።
አብዛኛዎቹ መድረኮች ላይ ህዝቡ ይበቃል ብሏል። ከመንግስት ጋር እልህ መጋባትና ከዚህ በላይ መስዋዕትነት መክፈል አስፈላጊ እንዳልሆነ በመድረኮቹ ሀሳብ ተነስቷል። ጉራጌ ከሌሎች አጎራባች ህዝቦች ጋር አብሮ ለመደራጀት የሚከብደው እንዳልሆነና ክልልነትን አሳበው ሌሎች አጀንዳዎችን የሚያራምዱ እንዳሉም ህዝቡ ተረድቶ አስተያየት ሰጥቷል
***
በተለይ በወልቂጤ አዲስ ክፍለ ከተማ በነበረው መድረክ የቀድሞ የጎሮ ወረዳ አስተዳዳሪ የነበሩት እና በህዝቡ ዘንድ ተወዳጅ የነበሩት #ጋሽ_ናስር _ጀማል(አቡ ዋዝ) በሳል ንግግር ያደረጉ ሲሆን ቀልቤን ስለሳበው ላካፍላችሁ
***
ጀመሩ ጋሽ ናስር
"ጉራጌ ክልል ለመሆን ብዙ የሚቀረው ነገር አለ፣ ማንን አወያይታችሁ ነው ክልል የጀመራችሁት? ክልል እኮ ኮሚቴ በማዋቀርና በአንድ ሰሞን የምክር ቤት ወከባ የሚፈጠር አይደለም። ህዝባዊ ውይይቶች አልተደረጉም። ቀቤና ባላመነበትና ባልተወያየበት ሁኔታ ጉራጌ ክልል ሊፈጥር አይችልም። ወለኔ ባልተወያየበትና በማያውቀው ሁኔታ ጉራጌ ክልል ሊሆን አይችልም። ማረቆ፣ መስቃን፣ ሶዶ ያላመነበት፣ ያልተወያየበትና ያልተስማማበት አጀንዳ ጉራጌን ክልል ሊያደርግ አይችልም። ለምንድነው ሚቀለደው? እኛ ልማትና ሰላም ናፍቆናል። ብዙ የሚቀሩ የቤት ስራዎች እያሉ አታደንቁሩን ከመንግስት ጎን ቆመን በስራችን እንቀጥል።"
ይህ ንግግር እጅግ መሳጭ ነው። እኔም የምስማማበትና ትክክልም ነው።
ጋሽ ናስር ጀማል ከወለኔ ብሔረሰብ የተገኙ በህዝብ ልብ ውስጥ ሁሌም ያሉ፣ ዛሬም ድረስ በአርሶአደሩ የሚደነቁ ምርጥ የቀድሞ የጎሮ ወረዳ አስተዳዳሪ ነበሩ
ረዥም ሀያት ከጤና ጋር
***
731 viewsAdu Emru, 19:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-10 15:50:47
ጥያቄያችን በሀቅ ላይ የቆመ ነው
በእርግጠኝነት እናሸንፋለን
***
ሁሉንም ነገር ከልብ ከፈለግነው ያደክመናል እንጂ አናጣውም። ከልቡ የፈለገ ሰው የልቡን አያጣም።

ሽንፈቶቻችን ሁሉ በጥረቶቻችን ይሸነፋሉ። ድክመቶቻችንም በጥንካሬአችን ይደመሰሳሉ። በማይቆም ጥረት ውስጥ ስንኖር ለማይቀር ድል እንታጫለን።
***
የምንኖረው መሆን እና አለመሆን በሚፈራረቁባት ምድር ላይ በመሆኑ ለደቂቃም ቢሆን ጥሮና ግሮ ከመኖር አንታቀብ። ብዙ ነገር ሊያጥረን ይችላል ነገር ግን የሁሉም እጥረቶች ማጥፊያ ራሱ #ጥረት ብቻ መሆኑን አንርሳ።
***
ከተጋን እየፈካን እንኖራለን። ትጋታችን ምኞታችንን ከተረትነት ይታደገዋል። ሳንሰለች ከታገልን የፈለግነው ሁሉ እኛን ይፈልገናል።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል
#ቀቤና_ልዩ_ወረዳ ነው
837 viewsHabib Kedir, 12:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-09 20:53:51
ድሮና ዘንድሮ
***
በዚህ አለም ስንኖር ብዙ ውጣ ውረድ ሊገጥመን ይችላል
ዛሬ ያለን ሀብት፣ ስልጣን፣ ዝና፣ ውበት ሊጠፋ ይችላል
የሰራነው በጎ ተግባር የክፉ ቀናችን ስንቅ ነው።
እህታችንን ድሮና ዘንድሮ፣ተመልከቷት።
ለዝህች አጭር እድሜ ፣ መረዳዳትና መደጋገፍን አንርሳ
እንረዳዳ!
ለእህታችን በዚህ በተወደደ ምሽት ሰደቃ እናበርክት
***
አካውንት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000528120214
የኮሚቴዎች ስልክ: 0913680407/0910849303
ቀጥታ እሷን ማናገር ወይም መጠየቅ የምትፈልጉ
ስልክ 0926537099
ቴሌግራም ቻናል ተቀላቀሉ https://t.me/Yosisi_Charity
ደግ ደጉን እናስብ
በጎ በጎውን እንስራ
#መልካምነት_መልሶ_ይከፍለናልና
495 viewsHabib Kedir, 17:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-09 10:22:26
የጉራጌ ዞንን ለማረጋጋት የቀቤና ወረዳን የፖለቲካ ሜዳ ማድረግ ተገቢ አይደለም
***
"በማዕከላዊ ኢ/ያ ክልል ቀቤና ልዩ ወረዳ ሆኗል" ብለው በየመድረኩ የሚነዘንዙትን "አይ ቀቤና ወረዳ አሁንም በጉራጌ ዞን ስር ነው" ብሎ ለማሳመን ወይም የፖለቲካ ቁማር ለመጫወት ነው አቶ ላጫ ወረዳችን የገባው።
የራሱን ዞን መምራት ያቃተው፣ ወደ ራሱ ቸሀ ወረዳ እንኳን መግባት የተከለከለ ሰው ምን አግኝቶ ነው ወደ ወረዳችን የሚገባው?
***
አቶ ላጫ ለቀቤና ህዝብ ከፍተኛ ጥላቻና ንቀት እንዳለው ከበፊት ጀምሮ በየመድረኩ ያሳየ መሰሪ ሰው ነው።
አቶ ላጫ በእውነት ለቀቤና ተጎጂዎችና ለህዝባችን የሚያስብ ከሆነ የቀቤና ወረዳ ምክር ቤት ያፀደቀውን የህዝባችንን የልዩ ወረዳ ጥያቄ በዞኑ ምክር ቤት እንዲፀድቅ ያድርግ።
ልክ የከምባታ ጠምባሮ ዞን ም/ቤት የጠምባሮ ልዩ ወረዳን እንዳፀደቀው።
***
በመድረክ ህዝባችንን እያዋረደ አዛኝ መስሎ ቆርቆሮ ይዞ ቢመጣም ለፖለቲካ ፍጆታና ፅንፈኛ ጉራጌዎችን ለማረጋጋት መሆኑ አይጠፋንም።
የፈለገ ይሁን ይህ በጥላቻ የሰከረ ሰው ወደ ወረዳችን ባይገባ ደስተኛ ነኝ።
መጀመርያ የራሱን ወረዳዎች በትክክል ይምራ፣ ስርዓትም ያሲዝ። የበጋ በጎ ፍቃድ ደግሞ ከየት የመጣ ፈሊጥ ነው።
***
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል
#ቀቤና_ልዩ_ወረዳ
750 viewsAdu Emru, 07:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-08 21:51:22
ዶክተር ዳውድ አላህ ሰደቃህን ይቀበል
763 viewsHabib Kedir, 18:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ