Get Mystery Box with random crypto!

Habib Kedir

የቴሌግራም ቻናል አርማ habib_kedir — Habib Kedir H
የቴሌግራም ቻናል አርማ habib_kedir — Habib Kedir
የሰርጥ አድራሻ: @habib_kedir
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 3.93K

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 8

2023-03-20 20:00:46
ጠቅላዩ ቅዳሜ ወልቂጤ ይመጣል
***
ዶ/ር አብይ ወልቂጤ የሚመጣው፣ አጎቶቼ ክልልነት በተናጠል እንደማይሰጥና የእስካሁን አካሄዳቸው ስህተት እንደነበር ከጠቅላይ ሚኒስትሩ አፍ እንዲሰሙ ነው።
***
ነገር ግን በጉራጌ ዞን ቀቤና፣ ማረቆ፣ ወለኔ፣ ሶዶ፣ መስቃን፣ ዶቢ ክስታኔ ሁሉም ሰላም ናቸው። ለጥቂት አከባቢ ግርግር የዶክተር አብይ መምጣት አስፈላጊነቱ አልታየኝም። ነገ ከነገ ወድያ ስልጤ፣ ሀድያ፣ ሀላባ፣ ከምባታ፣ ጋሞና ጌድኦ ክልል ለየብቻ እንደማይቻል "እራሱ መጥቶ ይንገረን" ማለታቸው አይቀርም።
***
ይህን መሰል ጉዳይ ለማስተካከል በክልሉ ድርጅቱን እንዲመሩ የተሾሙ ሰዎች በቂ ነበሩ። በየ ዞኑ መመላለስና መዓት የህዝብ ችግር ባለበት ሀገር በጀቱን በድግስ ማመንመን ተገቢ አይመስለኝም።
**
የእለቱ ስብሰባ እንዲህ ነው ሚሆነው…
ዌሄም አደርሁም ጨብጨብጨብ
ጉራጌ ሁሉም ሀገሩ ነው ጨብጨብጨብ
ለጉራጌ ከሀድያ በላይ ዘመድ የለውም ጨብጨብ
ጉራጌ ከስልጤ ተነጥሎ ህይወት የለውም ጨብጨብ
ጉራጌ ሁኑ ጨብጨብጨብ
በወሄ ዋሮ ጨብጨብጨብ
አለቀ!!
****
639 viewsHabib Kedir, 17:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-18 22:02:21
ባለ ውለታዎችን ማመስገን ተገቢ ነው
***
የቀድሞ አምባሳደር ተስፋዬ ሀቢሶን ለማመስገን በሚደረገው እንቅስቃሴ ከቀቤና ወጣቶችና ከኦገቶች የተገኘን 30 ሺ ብር ገቢ አድርገናል።
አንጋፋዎችን የሚያመሰግን ሁሉ ጀግና ነው።
ጋሽ ተስፋዬ ሀቢሶ ለቀቤና ህዝብ ነፃነት፣ የከፈልከውን ዋጋ እናውቃለን ለማለት ያህል ነው። እናመሰግናለን ረዥም እድሜ ከጤና ጋር እንመኛልካለን
***
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል
#ቀቤና_ልዩ_ወረዳ
300 viewsHabib Kedir, 19:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-18 12:30:39
ዛሬ የፀሎት ቀን ነው በተባለው መሰረት
እኛም እንዲህ ብለን ዱኣ አድርገናል

ያ ረቢ
ያ አላህ

እኛ ብቻ ነን የበላይ የሚሉ ጨቋኞችን

ከኛ በቀር አዋቂ የለም የሚሉ አባዮችን

ከሌላ ብሔረሰብ አንቀራረብም ብለው ሲያበቁ፣ ቀቤናን ግን አቅም እንበልጠዋለንና እንደፈለግን አናደርገዋለን የሚሉ በዳዮችን

አንተው ቀልብ ስጣቸው

አይ #ካላጠፋናቸው ብለው በእብሪታቸው ከቀጠሉ በራሳቸው ሀጃ ይጠመዱ

#አሜን
561 viewsHabib Kedir, edited  09:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-17 23:18:20 #ይበቃል_4
***
የቀቤና ብሔረሰብን እጣ ፈንታ ጉራጌ መወሰን የለበትም
የቀቤና ብሔረሰብ ሕዝብ የራሱ ቋንቋ ባህል ማንነትና ታሪክ ያለው ብሔረሰብ ቢሆንም ይሄን ለመቀበል በማይሹ የጉራጌ አመራሮች ሴራ ከተፈጸመበት ትልቅ ደባ ውስጥ የራሱ የሆነ መዋቅራዊ አደረጃጀት እንዳይኖረው ማድረጉ ግንባር ቀደሙ ነው።
***
ህዝቡ ይሄንን አደገኛ ሴራ በመረዳት የራሱ መጠሪያ ያለው እና እንደማንኛውም ብሔር ብሔረሰብ ሕዝብ በነጻነት የሚያስተዳድርበት መዋቀር ለመፍጠር ባደረገው ሰፊና እልህ አስጨራሽ ትግል በ1994 ዓ.ም በጉራጌ ዞን ውስጥ ሆኖ በስሙ የሚጠራ ነገር ግን በራሱ ጉዳይ የተሟላ ውሳኔ ሊወስን የማይችልበት ወረዳ የተፈቀደለት። ቢሆንም በወቅቱ ይሄ መዋቅር ከስም ለውጥ ውጪ ሕገ መንግስታዊ መብታችንን ሊያስከብር አይችልም በራሳችን ጉዳይ እራሳችን መወሰን የምንችለው በልዩ ወረዳ ስንደራጅ ነው የሚል ጥያቄ ቢያነሳም በቀጣይ ይታያል በሚል ኢ-ፍትሐዊና ኢ-ሕገ መንግስታዊ በሆነ አደረጃጀት እንዲዋቀር ተፈርዶበት እነሆ እስከዛሬ ሰሚ ሳያገኝ በተዕግስት ጠብቋል።
***
የቀድሞ ደቡብ ክልል በሴራ ፓለቲካ በተካኑ የጉራጌ አመራሮች ጫና ውስጥ ሆኖ የቀቤና ጥያቄ መከልከል የማይቻል መብት በመሆኑ አልፈቀድክም ላለመባል አልሸሹም ዞር አሉ የሚመስል ምላሽ በመስጠቱ መዋቅር በተበጀለት ጉራጌ ቀቤና ወረዳ በተሰኘ #እስር_ቤት እንዲተዳደር በማድረጉ ከአስተዳደራዊ በደሎች በተጨማሪ በተፈቀደ መዋቅር በርካታ መብቶቹን እያጣ ከርሟል
**
ለአብነትም
1.የብሔረሰቡ መብት በዞን ምክር ቤት አብላጫ ድምጽ ይደፈጠጣል ለአብነት የክላስተር ጉዳይ
2.የወልቂጤ ከተማ የቀቤና ሕዝብ በማያውቀውና ፍቃደኝነቱ ባልተጠየቀበት ሁኔታ ዴሞግራፊውን ለመቀየር ከቸሃ ወረዳ የተወሰኑ ቀበሌዎች ወደ ወልቂጤ ማካለል
3.በራሱ መልከአ ምድር ባሉ የወልቂጤ ከተማ ዙርያ ቀበሌ በማዘጋጃ የሚመራ ከተማ ለመመስረት የጉራጌ ፍቃደኝነት ያስፈልጋል በሚል መከልከሉ
4.በከተማ ዙርያ ያሉ ቀበሌዎች ቀቤና ፈቀደም አልፈቀደ ወደ ወልቂጤ ስለሚካለል ለአርሶ አደሩ ደብተር የሚሰጠው ጉራጌ ዞን ደብዳቤ ከጻፈ ነው የሚል ምላሽ ከክልል መሰጠቱ
***
በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ውስጥ በየትኛውም ጫፍ አንዱ ብሔረሰብ በሌላው ጉዳይ በማይወስንበት ሁኔታ በቀቤና ጉዳይ ጉራጌ እንዲወስን ያደረገ መዋቅር የተደራጀበት ሁኔታ ተስተካክሎ ቀቤና በራሱ ጉዳይ እራሱ የመወሰን ሕገ መንግስታዊ መብቱ የሚከበርለት በልዩ ወረዳ ሲደራጅ ብቻ መሆኑ መታወቅ አለበት።
በጉራጌ ዞን የቀቤና ህዝብ ስቆቃ ይበቃል
***
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል
#ቀቤና_ልዩ_ወረዳ
666 viewsAdu Emru, 20:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-17 20:12:47
704 viewsAdu Emru, 17:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-17 20:12:42 ጠቅላይ ሚንስትር አብይ ወልቂጤ ይመጣሉ
****
የጉራጌ አመራሮችና አጠቃላይ ህዝቡ ገዢውን ፓርቲና ጠቅላይ ሚንስትሩን በግልፅ ይቅርታ ሊጠይቁ እንደሆነ ሰምተናል።
ቢዘገይም፣ ብዙ ኪሳራ ቢያስተናግድም ጥሩ ነው
***
የጉራጌ አመራሮች ቃለ መሀል የፈፀሙበትን የድርጅቱን መርህ በመጣስ በሁለት ቢላ እየበሉ ዞኑን ሲያሸብሩና ህዝቡን ሲያወኩ ከርመዋል።
በመጨረሻ የመንግስትን ቁርጠኛ አቋም የተረዱት ክልል አስመላሽ ኮሚቴዎች፣ በጠቅላይ ሚንስትሩ ፊት ለፈጠሩት ግርግር ይቅርታ ጠይቀው፣ እንደማይደገምም ቃል ይገባሉ ተብሏል። ከጠቅላዩ ጋር ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ ባለስልጣናት ይመጣሉ።
****
በመድረኩ የቀቤና፣ የማረቆና የወለኔ ብሔረሰቦች ከጉራጌው እኩል ውክልናና ተሳትፎ ማግኘት አለባቸው።
ምንም እንኳን ጠቅላይ ሚንስትሩ ስለቀቤና ብሔረሰብ ታሪክና የመብት ጥያቄው በቂ ግንዛቤ ቢኖራቸውም፣ አንዳንዴ መድረክ ለማሞቅ የሚጠቀሟቸውና አብዛኛውን ሰው ለማስደሰት(ለማስጨብጨብ) የሚወረውሯቸውን ቃላት ተከታትሎ የሚያርም ያስፈልጋል።
***
ሁሉም ማወቅ ያለበትና መድረክም ከተገኘ መነገር ያለበት የቀቤና ህዝብ ሀቅ…
1 የቀቤና ብሔረሰብ ቀጥታ ከመንግስት መገናኘት ይፈልጋል። በጉራጌ በኩል አልፎ መንግስትን ማግኘት ማክተም አለበት
2 ቀቤና በምስለኔ የጉራጌ ካድሬዎች መመራት የለበትም፣ እራሱን በራሱ ማስተዳደር አለበት።
ለምን የሚባል ነገር የለም፣ መብት ስለሆነ ብቻና ብቻ።
***
የቀቤና ህዝብ የልዩ ወረዳ ጥያቄ የጠየቀው በጉራጌ ስለተጨቆነ ብቻ ሳይሆን በጉራጌ ስር መተዳደር ስለሌለበት ነው።
አንድ ብሔረሰብ በሌላ ብሔረሰብ የሚመራበት ምንም ምክንያት የለም። ቀቤና እራሱን እራሱ ለመምራት ብቁ ነው። ውሀ መብራት መንገድ ሆስፒታል መሬት ንጥቂያ ጭቆና ምናምን ብለን ጉንጫችንን ማልፋት የለብንም።
***
የቀቤና ህዝብ በጉራጌ ዞን ምክር ቤት በ3 ሰው ተወክሎ ለህዝቡ የሚበጅ ውሳኔ እንደማያገኝ ማንም ያውቃል። የኛ ጥያቄ የመጨቆን ያለመጨቆን ጉዳይ ሳይሆን የመዋቅርና የህገ መንግስት ትግበራ ጉዳይ ነው። በ21ኛው ክ/ዘ የቀቤናን ጉዳይ ጉራጌ እንዲወስንለት መፍቀድና ይህንንም አምኖ መቀበል ዘመናዊ ባርነት ነው
***
የማይገናኙ ነገሮችን የሚያገናኙና መጋባት መዋለድ አብሮነት ጉርብትና የሚባሉ ዲስኩሮች ከመብት ጋር የሚገናኙ አይደሉም። የቀቤና ህዝብ እራስን በራስ ማስተዳደር ከጉራጌ ጋር መጋባት፣ መዋለድ፣ አብሮ መኖርና መተሳሰብን የሚጨምር እንጂ የሚከለክል አይደለም። ቀቤና 70% ከኦሮሞ ጋር ድንበር ነው። ሁለቱ ህዝቦች በማዋቅር ሌላ ሌላ ክልል ናቸው ነገር ግን ፍቅራቸውና አብሮነታቸው መጋባቱ መዋለዱ ጨመረ እንጂ አልቀነሰም።
***
ማካለል በሚል አጀንዳ ዞኑ ደብዳቤ ካልፃፈ ተብሎ የመሬት የይዞታ ማረጋገጫ ያላገኙ መዓት የቀቤና ገበሬዎች አሉ። በቀቤና ህዝብ አንጡራ መሬት ወሳኙ ጉራጌው ነው ማለት ነው። ይህ ለአንዴና ለመጨረሻ ግዜ መቋጫ ማግኘት አለበት።
ዋናው ጥያቄያችን ቀቤና የራሱን ጉዳይ እራሱ የሚወስንበት አደረጃጀት እንዲፈጠር ነው፣ ያ ደግሞ ለግዜው ልዩ ወረዳ ነው።
***
በመጨረሻም ወረዳውና ወጣቶች እንደ ተለመደው ጠቅላዩ ወልቂጤ ሲመጣ ከመግብያው ጀምሮ በደማቅ ዝግጅት አሜተ ኤሳ ብለን መቀበላችንን እንዳንረሳ።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል
#ቀቤና_ልዩ_ወረዳ
721 viewsAdu Emru, edited  17:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-17 14:23:18
718 viewsAdu Emru, 11:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-17 14:23:14 ስንጣላ መታረቅም እንዳለ እናስብ
***
ሰሞኑን በሀላባ አንዲት እህታችን መታሰሯና መለቀቋ ይታወቃል
ጉዳዩን በሶሻል ሚድያ ማራገብ ያልፈለኩት፣ ያው እኛ በቀደድነው ቀዳዳ ሴረኞች እንዳይገቡበት በሚል ነው። ከቅን ሰዎች ጋር በአካልና በስልክ አውርተንበታል።
***
ሀድያና ሀላባ የታላቁ የሀድያ ሱልጣኔት የአንድነት ቀንዲል ናቸው። ሁለቱ ህዝቦች የትብብር ፋናወጊዎች፣ የአንድ አብራክ ክፋዮች፣ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች ናቸው።
የጥንቱን የአባቶቻችንን ልዕቅና በማወቅ ከብሽሽቅ ወጥተን ችግሩን በእርጋታ መፍታት ተገቢ ነው።
ስንጣላ መታረቅ እንዳለ እያሰብን ይሁን።
***
ሀድያና ሀላባ፣ በዚህ ትውልድ አላዋቂነት የማይፈራርስ ታሪካዊ አንድነት አላቸው። በጥቃቅን ጉዳዮች የሚሻክር ዝምድና አይደለም ያላቸው። ስለ ልጅቷ በሶሻል ሚድያ ሳይሆን በአካል ከሚመልከተው አካል ጋር መነጋገር በመጀመሩና ብልህና አርቆ አሳቢ፣ ሀቀኛ ሽማግሌዎች በሁለቱም በኩል ስላሉ፣ ያጠፋ ይገሰጻል፣ ችግሩም ይፈታል።
***
በለሊት ተነስታችሁ "ፈጣሪ ሆይ የሚጻፍ ርዕስ አታሳጣኝ" ብላችሁ የምትጸልዩ ሰዎች ርዕስ ስለተገኘ ብቻ አይጻፍም፣ ዙርያ ገባችሁን መርምሩ። ለህዝባችን አንድነት ጠቃሚውን መምረጥና የሚተወውን መተው ተገቢ ነው። በሀድያም ይሁን በሀላባ ምንም ችግር ቢከሰት ወደ ሚድያ የማናወጣውና ተመካክረን ነገሮችን በተቻለ መጠን በውስጥ ለማስተካከል የምንሞክረው፣ ዊዝደም ያላቸው፣ የህዝባቸውን ስሜት የሚረዱ፣ ችግርን የመፍታት ጥበብ የሚያውቁ ብልህ ሽማግሌዎች ስላሉን ነው።
***
በእውነት ስለ ሊድያ የተጨነቁ በጣም ትንሽ ናቸው፣ አንድ ነን ስንል የማይወዱ፣ በትብብራችን የሚቀኑ፣ ሊበታትኑን የሚፈልጉ አዕላፍ ሰዎች አሉ።
ለሁሉም መልሳችን አንድ ነው
ሀድያና ሀላባ ወንድማማች ህዝብ ነው
አሉ የተባሉ ችግሮች በመመካከርና በሰላም ይፈታሉ
የሀላባ ሙስሊሞችና የሀድያ ወንጌላዊያን በፍቅር ተከባብረው ለዘለዓለም ይኖራሉ
ሴይጣን አይኑ እያየ፣ ጆሮውም እየሰማ ሁሉም ነገር ሰላም ይሆናል
#ሀላባ_ቁሊቶ ሰላም
#ዋቻሞ_ሀድያ ሰላም
***
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል
#ቀቤና_ልዩ_ወረዳ
746 viewsAdu Emru, edited  11:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-16 21:09:08
"#እንደ_አገር"
ሳውዲ ሪያድ ኢትዮጵያ ኤንባሲ ነገ አይቀርም
አንዳንድ ሰዎች በጣም ይለያሉ
ፍጹም ሚዛናዊ ናቸው
***
በጣም የምንወደው ወንድማችን ሸምሱ ሱልጣን የስልጤ ብሔረሰብ ተወላጅ መሆኑ ስለቀቤና ባህል ታሪክና ቋንቋ ከማወቅ አላገደውም።
በሳውዲ የቀቤና ብሔረሰብ ዝግጅት ባለበት ሁሉ ተገኝቶ ስለ ቀቤና ልዕቅናና ታሪክ በግጥም ያቀርባል፣ ሌተ ቀን አውርቶም አይጠግብም።
የሱን አይነት ቅን ሰዎች ያብዛልን
ስለ ታላቅ ህዝብ ታሪክ የሚያውቁ ታላቆች ብቻ ናቸው
ሪያድ የምትገኙ የምንግዜም የህዝባችን መከታዎች ወንድማችን ቀቤናን እንዳከበር በፕሮግራሙ በመገኘትና መጽሀፉን በመግዛት አክብሩት።
***
ወንድሜ ሸምሱ "#እንደ_አገር" የተሰኘ መጽሀፍ ጽፎ በሳውዲ ሪያድ ነገ ያስመርቃል።
መጽሀፉ በቀን 17/03/2023 በኢትዮጵያ ኢምባሲ በድምቀት ይመረቃል።
በመጽሀፉ ስለ ቀቤና ህዝብ ባህላዊ ሽምግልና ቀንጨብ አድርጎ አቅርቧል
ጓደኛዬ Shemsu She Sultan Gerbashot እንኳን ደስ አለህ
አንተ ገና ምትደርስበት አለህ!
***
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል
#ቀቤና_ልዩ_ወረዳ
475 viewsAdu Emru, 18:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-16 16:21:15
ትምህርት ቤቶች የሁሉም ነገር መሰረት ናቸው
#ሼር አድርጉት
***
አንድ ህዝብ ባህልና ታሪኩን እንዲሁም የመረዳዳት እሴቶቹንና ግብረገብነትን ታች ካሉ ትምህርት ቤቶችና ከህፃናት ቢጀምር ውጤታማ ይሆናል።
አሁን ያሉ ጅማሮዎች ከጎለበቱ ቀጣይ የቀቤና ትውልድ በእርግጠኝነት ገናና ታሪኩን የሚመልስ ይሆናል
***
በቀቤና ልዩ ወረዳ ወሸርቤ ጣጤሳ #ኡንጀሞ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የህዝባችንን ባህል፣ ታሪክና ቋንቋ ለማሳደግ ብሎም የመረዳዳት ባህሉን ለማዳበር በታዳጊ ተማሪዎች ላይ እያደረገ ያለው እንቅስቃሴ እሰይ የሚያስብል ነው።
***
ባለፈው ህዳር በብሔረሰቦች በዓል ወቅት ተማሪዎቹ በጨቅላ አዕምሯቸው የቀቤና የባህል አልባሳት፣ የባህል ቁሳቁስ እንዲሁም ባህላዊ የአመጋገብ ስርዓትን አቅርበዋል።
የዛው ትምህርት ቤት ህፃናት አሁን ደጎሞ እገዛ ለሚያስፈልጋቸው ሰዎች ሰብል በመሰብሰብ አግዘዋል።
***
ህዝባችን ታዳጊዎች ላይ መልካም ዘር ከዘራ ቀጣዩ ግዜ ብሩህ ይሆንለታል።
በየትምህርት ቤቱ የባህል አብዮት በመፍጠር፣ ብሔረሰቡን የሚወድ፣ ባህሉን የሚያከብር፣ በማንነቱ የሚኮራ ትውልድ እንፍጠር።
በዚህ ረገድ የኡንጀሞን ትምህርት ቤት አርዓያ እንከተል
የትምህርት ቤቱ ዳይሬክተር መሀመድ ሁሴን እና እስታፉ አጠቃላይ እያደረጋችሁ ያለው እንቅስቃሴ የሚበረታታ በመሆኑ በዚሁ ቀጥሉ።
***
በመጨረሻም እነዚህ ለባህላቸው እድገት እንዲህ የሚለፉ ህፃናት የተሟላ መማርያ መፅሀፍ የላቸውም፣ ወንበር የላቸውም መሬት ላይ የሚማሩ አሉ፣ ክፍሎቹ የፈራረሱና መስኮት በር ያልተሟላላቸው ነው። እነዚህን አይታችሁ ልባቹሁ የሚራራና የምታዝኑ ለጋሾች ትብብር አድርጉ፣ ለNGO ወይም ለበጎ አድራጊ ድርጅቶች በማሳወቅ የዜግነት ሀላፊነት እንወጣ።
***
መጪው ግዜ ለቀቤና ህዝብ ብሩህ ነው

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል
#ቀቤና_ልዩ_ወረዳ
633 viewsHabib Kedir, 13:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ