2023-04-16 14:56:29
ይህን ተቋም እንደግፍ
የየቲም ጉዳይ የሁላችንም ጉዳይ ነው
#አንሷር የየቲሞችና የአቅመ ደካሞች መርጃ ማህበር
***
ለአዲስ አበባ ቅርብ ሆኖ፣ ብዙ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ያልገቡበት አከባቢ ልጥቀስ ብትሉ ቀቤና ወረዳ ወይም ወልቂጤና አከባቢው ቀዳሚ ነው።
አንሷር፦
ማንም አስታዋሽ በሌለበት፣
ብዙ ድርጅቶች ፊታቸውን ባዞሩበት አከባቢ፦
ትልቅ አላማ አንግቦ ተስፋ ባለመቁርጥ፣
በጽናትና በቁርጠኝነት የሚውተረተር ማህበር ነው
*ይህ በጎ አድራጎት ማህበር ከተቋቋመ አጭር ግዜ ቢሆንም ያደረጋቸው እንቅስቃሴዎች በርካታ ናቸው
አቅመ ደካሞዎችና ተረጂ ህጻናትን በየቀበሌው እየዞሩ የሚብሱትን ይለያሉ
ረመዳን ያሲዛሉ፣ ያስፈታሉ፣
ቤት ያድሳሉ፣ ይሰራሉ፣
የሚቀመስ ለሌላቸው እህል ያቀርባሉ፣
ሰዎች ጾም ወለው እንዳያድሩ ይተጋሉ፣
የትምህርት ቁሳቁስ ለህጻናት ያቀርባሉ፣
ልብስ ያለብሳሉ የሚስኪኖችን እምባ ያብሳሉ
ከዚህ በላይ የሚያስደስት ተግባር የትም የለም
***
ይህን የሚያስተባብሩ ወንድሞች ፍጹም በሆነ ቅንነትና በነጻ ተግባራቸውን ይፈጽማሉ፣
ፈጣሪ ለሃይር ስራቸው በመልካም ይመነዳቸው ዘንድ ዱኣ እናድርግላቸው።
የያዙት ግዙፍ ሀሳብ ነው
በቅርብ ቀን እንኳን ለብዙ ህፃናትና አቅመ ደካማ ተረጂዎች በነብሳቸው ደርሰዋል።
የማህበሩ ገቢ የአከባቢው ህዝብና ሲቪል ሰርቫንቱ ነው።
የሚያግዛቸው ሀገር በቀልም ይሁን የውጭ ድርጅት የለም።
የማህበሩ መፈክር “#ሰደቃ_ገንዘብን_አታጎድልም” የሚል ነው።
እውነት ነው “መስጠት አያጎልም” ።
ሁላችንም የማህበሩ አባል በመሆን በጎ ተግባራቸውን ባለንበት እናግዝ፣ ማህበሩን ከፍ ያለና ጠንካራ እናድርገው።
***
አባል ለመሆን የምትፈልጉ መስፈርቱ ቀላል ነው፣ ሰው መሆንና ቅን መሆን ብቻ፣
ዛሬውኑ አባል ይሁኑ፣ መታወቂያ ይውሰዱ፣ በአካልም ጠይቋቸው፣
ወራዊ መዋጮ 20 ብር ነው
መታወቂያ ወስደን የአመት ባንዴ እንክፈል ብንል እንኳን 240 ብር ነው
እናፍጥነው ለበጎ ስራ ረፍዶ አያውቅም
ጽህፈት ቤታቸው
ወልቂጤ ኢሊናም መንደር አንሷር መስጅድ አጠገብ
የየቲም ጉዳይ የኔም ጉዳይ ነው።
***
በባንክ አካውንት ማህበሩን ለመርዳት፦
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000528883595(Ansar yeytimochna akmdekamoch)
አንድ ጉዳይ ባንተ ላይ ሲያስጨንቅህ ሰደቃ ስጥ፣
ሰደቃ ጉዳይን ያቃልላል ፣የልብ እረፍትም ይሰጣል።
ግሩፓቸውን ለመቀላቀል
በዋትሳፕ
Follow this link to join my WhatsApp group: https://chat.whatsapp.com/FcZ44j9aw5hB9VKelmCXT3
በቴሌግራም
https://t.me/+k5QVT8mMR85iYzg0
አንሷር የቲሞች እና አቅመ ደካሞችን መርጃ ማህበር
አንሷር
የየቲሞች አጋር
796 viewsHabib Kedir, edited 11:56