Get Mystery Box with random crypto!

Getachew shiferaw

የቴሌግራም ቻናል አርማ getachewshiferaw — Getachew shiferaw
የሰርጥ አድራሻ: @getachewshiferaw
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 44.30K

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 132

2022-08-28 20:28:21 መከላከያም፣ ልዩ ኃይልም፣ ፋኖም፣ ሚሊሻም የማትተካ ነፍሱን እየሰጠ ነው! መከላከያን ብቻ ባለ ድል አድርገህ ብትጠራ፣ ፋኖ ከከበባ የሚያወጣው የመከላከያ አባል ፋኖን መርሳትህን ይታዘብሃል። እርሻውን ጥሎ፣ ቤቱን ትቶ የዘመተን ሚሊሻ ብትረሳው የጥምር ጦሩ አባላት ይታዘብሃል።ልዩ ኃይልና ፋኖን ብቻ ብትጠራ፣ ልዩ ኃይልና ፋኖ ሲፋለም ከመቅፅበት ደርሶ ጠላትን ያደባየው ኮማንዶን ጀግንነት የሚያውቀው ወገንህ ይታዘብሃል። መከላከያ ውስጥም ያለው ወገንህ ነው፣ ልዩ ኃይል፣ ፋኖና ሚሊሻም በቁርጥ ቀን የሚደርስ ወገንህ ነው። ቢሸነፍ ሽንፈትህ፣ ቢያሸንፍ ድልህ ነው። የማትተካ ነፍሱን እየሰጠ ያለን ኃይል መካከል መነጣጠል እንዳይኖር መጠንቀቅ ያስፈልጋል። ሁሉም የወገን ጦር ነው። የወገን ጦር

ለአንተ ህልውና የሚሞትልህ መካከል አንደኛውን ማወደስ፣ ሌላኛውን መርሳት አይቻልም። ጦር ሜዳ ያሉት እጅ ተያይዘው ነው ለድል የሚያበቁን። ሁሉም ወንድሞቻችን ናቸው። ድል ይቅናቸው!
23.8K views17:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 18:31:38 ድልንም ሽንፈትንም በቅጡ መያዝ ይጠቅማል! ለሀዘኑም ለደስታውም መጋል ጥሩ አይደለም። ጦርነቱ ገና ነው። በሀዘንም በደስታም ኃይል አትጨርሱ። ስሜታችን እምቅ ማድረግ እንልመድ!

ይሄ የእግር ኳጭ ጨዋታ አይደለም። የእግር ኳስ ጨዋታ የሚደግፈው ቡድን ጎል ሲስትበት ከግንብ ጋር ካልተጋጨሁ፣ የሚደግፈው ቡድን ጎል ሲያገባ ዘልዬ ከፊትም ከኋላም ከጎንም ያለን ሰው ካልረገጥኩ የሚል ስሜቱን ያልገራ ኩታራ የጦርነት ዜና ላይ እጁን ስብስብ ቢያደርግልን ለራሱም ጤና፣ ለጦርነቱም ውጤት ይጠቅማል። በቲቪ በሚያየው እግር ኳስ በየደቂቃው ብድግ ቁጭ የሚል ስሜታዊነት ጦርነት ላይ አይሰራም። በጣም ይጎዳል።

ጦርነት ላይ ወታደሮቹም ምሽግ ላይ ትንፋሻቸውንም ጭምር ውጠው፣ ከላይ የሚወርድባቸውን የጥይት ናዳ ችለው ሲመቻቸው ነው የራሳቸውን እርምጃ የሚጀምሩት።

በእርግጥ ብዙ ሰው ስሜታዊ ሆኖ የጦርነት ሁኔታን የሚጎዳው፣ ሕዝብ የሚያሸብረው ራስ ወዳድም ስለሆነ ነው። ተንፍሸ ይውጣልኝ ስለሚል ነው። ማታ ላይ አንዱ በቡጢ አቅምሶት ወደቤት ቢገባ ያበጠውን ግንባሩን ከበሩ ተጋጭቸ ነው ብሎ የሚዋሸው በሕዝብ ላይ ሲሆን ግን በዝናቡ፣ በፀሐዩ፣ ፆሙን መከራውን ሲያይ የዋለውን ሰራዊት ሲረግም፣ የተመታና የተሸነፈ ሲያስመስል ይውላል። ያበጠውን ግንባሩን ለቤተሰቡ እየደበቀ፣ የራሱን ሰራዊት ተመታ ወዘተ እያለ ለጠ*ላ**ቱ ጨምሮ ለዓለም ያሳውቃል። ይሄ ስሜትን አለመቻል የሚያመጣው ችግር ነው። ብስጭትንም ደስታንም አለመቻል በሽታ ነው። ትንሽ ቀዝቀዝ ማለት ያስፈልጋል። ብዙው ነገር ገና ነው። ይህ አሸባሪ ቡድን ገና ብዙ የቤት ስራ አሸክሞናል። እንዳንደክም ስሜታችንንም ብስጭታችንንም ቻል፣ ዋጥ ማድረግ ይጠይቃል።

አሸባሪው ቡድን በጊዜያዊ ጠብ አይደለም እየጎዳን ያለው። ከሀምሳ አመት በፊት የሀሰት ትርክት የፃፈበትን ሕዝብና አገር ነው እየመታ ያለው። የጣለብን የቤት ስራ በርካታ አመታትን የሚፈጅ ነው። ትንፋሽ ስቦ ስሜትን ዋጥ ማድረግ ያስፈልጋል።

ቸር ያሰማን!
25.5K views15:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 14:57:55 የእኛ ሚና ምንድን ነው?

ትህነግ ዳግመኛ ጥ*ቃ*ት ፈፅሞብናል። ይህ ኃይል ባለፈው ከቆቦ እስከ ሸዋሮቢት፣ ከላሊበላ እስከ ጋይንት፣ ከዋግኸምራ እስከ ጭና የፈፀመብንን እናውቃለን። ያን በደል አሁን እንዲደግመው መፍቀድ የለብንም። ለሕዝባችን የሚጨንቀን ከሆነ እኛ እንችለዋለን የምንለውን ሚና መጫዎት ግድ ይለናል። የራያ ወገናችን ሲጠቃ ጦርነቱን ከዘነጋን ከትናንቱ አልተማርንም ማለት ነው። የራያ ወገናችን ላይ የተከፈተውን አሁኑኑ መቀልበስ አለብን። ሁላችንም በምንችለው ማበርከት አለብን! እስከ ነገ መዘግየት የለብንም። ዛሬ

1) ስንቅ ማሰባሰብ የሚችል በስንቅ ማገዝ አለበት
2) ኃይል አሰባስቦ መድረስ የሚችል ዛሬውኑ ያን ጥቃት ለመቀልበስ መነሳት ግዴታው ነው።
3) ሕዝብ በተሳሳተ መረጃ እንዳይረበሽ ማረጋጋት የጦርነት አንዱ አካል ነው። ትህነግ ከመሳርያው ያላነሰ ፕሮፖጋንዳን የስነ ልቦና ጦርነት አካል አድርጎ ይጠቀማል።
4) ሰርጎ ገብ ሊያደርሰው የሚችለውን ጉዳት ከአሁኑ ለመከላከል መዘጋጀት ያስፈልጋል።
5) መረጃዎችን መቀያየር፣ ለሕዝብ በሚጠቅም መልኩ ማሰራጨት ያስፈልጋል።

በትክክለኛውም ሆነ በተሳሳተ ወሬ ተደስቶም ተበሳጭቶም ለውጥ አይመጣም። ለውጥ የሚመጣው የእኔ ሚና ምንድን ነው ስንል ነው። በሰበር ዜና ተደስተን ደስታው ቀጣይ ሊሆን አይችልም። ትህነግ ሰበር ዜና በሚለው ተናድዶ ለውጥ አይመጣም። የገባንበት ጦርነት ብዙ ዋጋ ያስከፍላል። ብዙ ፅናት፣ ብዙ ትግስት ያስፈልገዋል። ስሜታችን ትንሿ ነገር ነች። የእህቶቻችን ተስፋ ያጨልማል፣ የወጣቶችን ህይወት ይቀጥፋል። ስሜታችንን እምቅ አድርገን ሚናችን ምንድን ነው እንበል።

ሚናችን ከለየን የተነገረው ሰበር ዜና ሁሉ ጮቤ አያስረግጠንም። ሚናችን ከለየን የተነገረው የትህነግ እውነትም ይሁን ውሸት ተስፋ አያስቆርጠንም። ሚናችን ከለየን በቀጣይስ የምንሰራው ምንድን ነው የሚለው ያስጨንቀናል። ሁላችንም ሚናችን ምንድን ነው እንበል። በሰበር ዜና መደሰት፣ መጨነቅም ሚና አይሆንም። ከአሁኑ ጀምረን ሚናችን ምንድን ነው እንበል!



ማሳሰቢያ:_

በዚህ ወቅት በረባ ባልረባው መጨቃጨቅ ለጠላት የሚጠቅም እንጅ ለወገን የምንሰራለት ሚና አይደለም።

ትህነግ በየትኛውም ማንነት አይነጥለንም። የሁላችንም አንገት ለእሱ አንድ ነው። በስስት የሚያቅፈው አይደለም። በጥላቻ የሚቆርጠው ነው።
16.4K viewsedited  11:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 11:06:28 የባለፈው ስህተት እንዳይደገም!

ትህነግ በራያ ግንባር እንደለመደው በሕዝብ መአበል መጥቷል። ዘራፊውንም ተዋጊውንም አግተልትሎ በኢትዮጵያ መከላከያ ላይ ጥ*ቃት ከፍቷል። ከእርዳታ ድርጅቶች ነዳጅ ሰርቆ ወደ ማ*ጥ* ቃ**ት የገባው ትህነግ ለእርዳታ ድርጅቶች ከአማራ ክልል ዘርፌ እመልስላቸዋለሁ ብሎ አስቧል። ከፍተኛ የተተኳሽ እጥረት ያለበትም በመሆኑ ሰራዊቱን ከብቤ ተተኳሽና መሳርያ አገኛለሁ የሚል እቅድ አለው። ከፊት የሚያሰልፈውን መንጋ ዘርፈህ ትመጣለህ እያለ አባብሎታል። ትግራይ ውስጥ በትህነግ ታፍኖ የከረመው ወጣት ከባለፈው አመት በበለጠ እድል ሲያገኝ ለኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት እጅ እየሰጠ ቢሆንም ትህነግ የገፋ ሲመስለው ግን ባለፈው ከፈፀመው ግፍ በላይ ለመፈፀም ወደኋላ የማይል ጨ*ካ*ኝ መሆኑ መረሳት የለበትም።

ትህነግ እስካሁን ባለው ከፍተኛ ኃይል እየረገፈበት ቢሆንም ለእሱ የሚያልቀው የትግራይ ወጣት ነፍስ ከጥይት ዋጋ አይበልጥበትም። የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት፣ የአማራ ልዩ ኃይልና ፋኖ ከፍተኛ ተጋድሎ በማድረግ የትህነግን መንጋ እየመከተ ይገኛል። ይሁንና ትህነግ ካለው እቅድ አንፃር በዚህ ግንባር የመጣውን የትህነግ መንጋ ኃይል አሰባስቦ መመከት ግዴታ ነው።


ትህነግ እድል ካገኘ ባለፈው ከፈፀመው በላይ ውድመት እንደሚያደርስ የሚገመት ነው። ስለሆነም የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት፣ ባለፈው አመት መከራውን ያየው ሕዝባችን ላይ የተከፈተውን ጥ**ቃ*ት ከየትኛውም ጉዳይ አስበልጦ ኃይልን አሰባስቦ መመከት ያስፈልጋል።


የባለፈው ስህተት እንዳይደገም፣ ከአሁኑ መረባረብ ግዴታ ነው። ሁሉም በሚችለው ተረባርቦ ሕዝብ ከስቃይ ማዳን ግድ የሚልበት ሌላ ዙር የትህነግ ጥ*ቃ**ት ላይ ነን።
18.3K views08:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 21:10:17
20.5K views18:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 21:10:03 ነዳጅ የዘረፈው ትህነግ በወዳጁ በሳማንታ ፓወር ውግዘት ገጥሞታል!
20.0K views18:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 19:29:17
20.8K views16:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 19:29:11 የትህነግ ነጣጥሎ ማጥቃት ስልት

(የጥላቻቸውን ጥግ ተመልከቱ)

ከስር ያለውን ፅሁፍ የፃፈው እነ ደብረፅዮን ቀጥረው ሲያሰሩት የነበረው አክቲቪስት ነው። ዋናው አላማቸው እየነጣጠለሉ መምታት ነው። ሀሰት መረጃ አገኘን እያሉ የአማራን ክፍሎች እየነጣጠሉ የሚያጠቁትም ይህን የትህነግን አላማ ይዘው ነው። ዛሬ ጎንደርን፣ ነገ ሌላውን እያሉ እየነጣጠሉ ያጠቃሉ። በዛውም ጥላቻቸውን ተመልከቱት።

ትርጉሙ እንዲከተለው ቀርቧል።
*****
ያቺ ከተማ ትጠመቅ!!

የትምክህትና የስርዓት አልበኝነት ማዕከል ብቻ አይደለችም። ይቺ ከተማ ከአስመራ ቀጥሎ ሁለመናዊ የትግራይ ህዝብ ኪሳራ መለኪያ ናት። የትግራይ ህዝብ እንደ ህዝብ እንዲጠፋ፣ እንዲበተን፣ ከስር መሰረቱ ተነቅሎ እንዲወድቅ ብቻ ሳይሆን ከጥንት እስካሁን እድሜውን በሙሉ ያፈራው፣ የኮተኮተው፣ለሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ ያካፈለውን ቁሳዊና መንፈሳዊ ስልጣኔው ተሟጦ በታሪክ ከአለም ስልጣኔና ከሰው ልጅ ህሊናም ሳይቀር እንዲጠፋ የተወጠነባት ቦታ፣ የጥፋት ውል የታሰረባትና ሁሉም የትግራይ ደመኛ ጠላቶች ለተግባራዊነቱ በአዋጅ የተንቀሳቀሱባት ሲኦላዊት ከተማ ናት! ይቺ ከተማ የዚህ ዘመን ትልቋ ውጫሌ ናት። ህያዋን ካለፉ በኋላ ኃጣን የወረሷት ገሃነማዊት ከተማ ናት። ተጋሩ ከ16ኛው ክ/ዘመን ጀምሮ በተለይም በ18ኛው 19ኛው ክ/ዘመን ይቺን ከሃዲ የሆነች ከተማ በደማቸውና በተጋድሏቸው ክብሯን ጠብቀው ከአጥፊዎች፣

አውዳሚዎችና አማፂ ሽፍቶች አድነዋታል። አፄ ፋሲል፣ ራስ ሚካኤል ስሁል፣አጼ ዮሃንስ 4ኛ፣ አሞራና ቀሺ ገብሩ ለዚያች ከተማ ውለታ የዋሉ ምስክሮች ናቸው። እሷ ግን 'ባጎረስኩ እጄን ተነከስኩ' እንዲሉ ሁሌም ከተጋሩ በተፃራሪ እንደቆመች ናት። ይቺ ከተማ ወይ እንደ ባህረ ዮርዳኖስ በTDF ልትቀደስ ይገባል ወይም እንደ ሰዶምና ጎመራ በTDF ተንዳ ወደ አፈር ልትቀየር ይገባል። ጊዜው ደግሞ አሁን ነው። የኢትዮ-ኤርትራ ፖለቲካዊና ወታደራዊ ሚዛን ወሳኝ በሚባል ደረጃ እንዲቀየር ከተፈለገና ተጋሩ ሉዓላዊ ግዛታቸውንና ታሪካዊ ክብራቸውን እንዲመለስ በማድረግ ቢያሻቸው የምስራቅ አፍሪካ ሁለመናዊ ሚዛን አስጠባቂ እንዲሆኑ ከተፈለገ ጎንደር መጠመቅ ያለባት አሁን ነው።
20.3K views16:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 17:56:43
19.3K views14:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 17:56:34 እባካችሁ ክፋ በማያውቁት በህፃናትም አትነግዱ!

ትህነግ መዋለ ህፃናት ትምህርት ቤት በአውሮፕላን ተደበደብኝ ብሏል። በእርግጠኝነት እውነት ከሆነ ማሰልጠኛ አድርጎታል ማለት ነው። ትህነግ ግን ውሸቱንም ለመደበቅ ብዙ አልጣረም። ለምሳሌ!

በእኛ አገር ደረጃ ይህ ገና ቆሞ መሄድ የማይችል ልጅ መዋለ ህፃናት ውስጥ ምን ያደርጋል? የሚያለቅሰው ህፃን ላይ ሌላ ጉዳቱ አይታይም። የሚታየው መርፌ ሲወጋ ነው። ምንድን ነው የሚጠቅማቸው? ቀደም ሲል የለጠፍኩት ፎቶ ደግሞ የጎረምሳዎች ነው። በትንሹ ከ15 አመት በላይ ይሆናቸዋል። ህወሃት ከ7 ክፍል ጀምረው ያሉትን ተማሪዎች በግዳጅ ወደ ወታደራዊ ስልጠና እያስገባ ነው። ታዲያ እነዚህ ወጣቶች መዋለ ህፃናት ውስጥ ምን ያደርጋሉ? ደግሞ ትምህርት ቤት በክረምት አለ ወይ?

ጦርነት የመረረውን የትግራይ ህዝብ ለመቀስቀስና ዓለም አቀፍ ማህበረሰቡን ለማወናበድ ተብሎ በህፃናት ላይ የፖለቲካ ንግድ ጀምረዋል።
19.3K views14:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ