Get Mystery Box with random crypto!

Getachew shiferaw

የቴሌግራም ቻናል አርማ getachewshiferaw — Getachew shiferaw
የሰርጥ አድራሻ: @getachewshiferaw
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 44.30K

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 131

2022-08-30 13:22:25 እናሸንፋለን!

ለማሸነፍ ግን:_

ዳር ላይ ያለች ትንሽ ከተማ ተያዘችም፣ ትልቅ ከተማ ተያዘም ክብራችን ተነክቷል። የቀበሌ፣ የወረዳ፣ የዞንና የክልል ከተማ ቢያዝ ከብዙ ፋይዳ አንፃር ሊታይ ይችላል። ክብር ግን የትኛም ላይ ተመሳሳይ ነው። ከራሱ ድንበር አንድ ኢንች ሲያልፍ ተወርረናል የሚል ስሜት መኖር አለበት። ትንሽ ከተማ ሲያዝ ምንም የማይመስለን፣ ትልቅ ሲያዝ እንቅልፍ የምናጣ መሆን የለብንም። ከሩቅ ያለቦታ ሲያዝ ግድ የለሽ ወደእኛ ሲቀርብ የምንሰጋ መሆን የለብንም።

ትህነግ የራሱን አልፎ ከመጣ ቆይቷል። አሁን የራሳችን ከተማ የምንቆጥርበት አካሄድ መቆም አለበት። ከወረረው እስካልወጣ ድረስ የትም ይሁን የት ህመሙ እኩል መሆን አለበት። የራሳችን ከተማ እየተወረረ ዛሬ ከዚህ ደርሷል፣ ነገ ከዚህ ይደርሳል እያልን መቁጠር ለውጥ አያመጣም። ከየትኛውም እንዲወጣ የሚያስችል ስራ መስራት አለብን።

የትም ደረሰ፣ የት እንደምናሸንፈው ደግሞ ጥርጥር የለውም። ባለፈው ገና ከራያ ጀምሮ ባለው ከህዝባችን ከፍተኛ ትግል ገጥሞታል። በየመንደሩ ሲያልፍ በጀግናው ህዝባችንና ሰራዊቱ በርካታ ኃይሉን እያጣ ነው ሸዋና ጎንደር ድረስ የደረሰው።

ሸዋ ደርሶ ተመትቶ ተመልሷል። ከደብረታቦር ቅርብ ርቀት ደርሶ ተመትቷል። ከደባርቅ ቅርብ ርቀት ደርሶ ተመትቷል። ተስፋ በቁረጡት ሳይሆን ተስፋ ባልቆረጡት ተሸንፏል። ወገናቸውን በጎነተሉት ሳይሆን በቻሉት ከወገናቸው ጋር በቆሙት አቅም ተመትቷል። ባቅማሙት ሳይሆን በቆረጡት ተመትቷል። ሰራዊቱ ሸሸ ብለው ባራገቡት ሳይሆን ያለበት ድረስ ሄደን እንገጥዋለን ባሉ ክንደ ብርቱዎች ተመትቷል። ከቻልን አሁን ባለበት አስቁመን ወደመጣበት ለመሸኘት መስራት ነው። ባይቻል ደግሞ የትም ይግባ የት መሸነፉ እንደማይቀር አምነን መስራት አለብን። ደብረብርሃን ይድረስ ጎንደር፣ ላሊበላ ይድረስ ደጀን እንደምናሸንፈው ሳንጠራጠር መስራት አለብን።

እነሱ ዋሻ ገብተው ወጥተዋል። መቀሌም ይሁን አዲግራት ሲያዝባቸው ሰራዊቱ ሸሸ ብለው ብዙ አጀንዳ አላደረጉትም። ሲይዙ እንጅ ሲያዝባቸው ከተማ አልቆጠሩም። ከማን ጋር እንደገጠምን ማወቅ አለብን። የራስን ከተማ መቁጠር መቆም አለበት።

ባለፈውም ዘንድሮም መወረር አልነበረብንም። ግን ሆኗል። በሆነ ጉዳይ ጉንጭ ማልፋት የለብንም። ባለፈው እንዳደረገው ዘንድሮም ከራያ ጀምሮ ሕዝባችን የቻለውን እያደረገ ነው። ትልቅ መስዋዕትነት እየከፈለ ነው። ወደፊት ሲያልፍ አጨብጭቦ አያሳልፈው፣ ባገኘው አጋጣሚ እየገጠመው ኃይሉን እያጣ ነው የሚያልፈው። የትም ይድረስ የት ተመትቶ ይመለሳል።

ባለፈውም ብለናል። ሆኗልም። እንዳትጠራጠሩ እናሸንፋለን!
20.1K viewsedited  10:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 12:15:34
20.3K views09:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 12:15:29 "ጠባችን ከአማራ ጋር ነው።" የትህነግ መግለጫ

ወ*ያ*ኔ ዛሬ ያወጣው መግለጫ ነው።

መግለጫው ለኢትዮጵያና ለኤርትራ ህዝብ የተላለፈ ጥሪ ሲሆን የመግለጫው አንኳር ይዘት ባጭሩ .......
"የኢትዮጵያና የኤርትራ ጦሮች በጋራ ትግራይን ለመውረር ዝግጅት መጨረሳቸውን ተረድቻለሁ ፤ በመሆኑም እኛ ከኢትዮጵያና ከኤርትራ ህዝብ ጋር ጠብ የለንም፤ጠባችን ከአማራ ጋር ብቻ መሆኑን ተረድታችሁ ይሄንን እኩይ የጥፋት ድግስ እንድታወግዙ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን" ይላል ።


ከአስፋው አብርሃ ገፅ የተወሰደ ነው።
20.3K views09:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 17:39:10 ለመከራከር ጊዜ የለንም!

በዚህ ቀደም የነበረ እልህም፣ ስሜትም፣ በደልም ከጦርነት ጋር መያያዝ የለበትም። ጦርነቱ ብቻውን ነው መታየት ያለበት። ከአሁን ቀደም አንድ አይናችን የጎዳን ኃይል ቢኖር ሌላውም ከባለፈው ጠላት የተለየ ምንም አያደርግምና የቀረችውን መጥቶ ያጥፋት የሚል አስተሳሰብ ራስህን የማጥፋት ያህል ጎጅ ነው።

ትናንት ቆቦ ላይ በርካታ ንፁህን ተገድለዋል። መምህራን ተረሽነዋል። ቆቦ እንዳትነሳ ሆና ተዘርፋለች። ቀሪው ሕዝባችን ላይ አደጋ አንዣብቧል። በዚህ ወቅት የቆየ ቁስል ብናክክ የባሰ ጉዳት እንጅ መፍትሔ አናመጣም። እየመጣ ያለው ኃይል የማይበላውን የአርሶ አደር በሬ መንገድ ላይ ገድሎ የሚሄድ ነው። ቀሳውስትንና ሸኮችን የማይምር ነው።

ይህ በሆነበት ከፋፋይ ሀሳቦች ሕዝባችን አይጠቅሙትም። አሁን ለመከራከርም፣ ለመናቆርም ጊዜ የለንም። አሁን ያለችን ትንሽ ጊዜ ምን እንስራ የምንልባት ብቻ ነች።

ጦርነት የተከፈተው በእኛ አይደለም። ወደእኛ ነው የመጡት። እያንዳንዱን ቤት አንኳኩቶ ሕዝባችን ያጠቃል። ስለሆነም ጉዳዮችን መነጣጠል ያስፈጋል። የኩርፊያ፣ የመጠራጠር፣ የእልህ ጉዳይ የበለጠ ያደማናል። እነሱ የራሳቸውን ብቻ ሳይሆን የውጭ ኃይልንም ጭምር አስተባብረው፣ የፌደራሊስት ወዘተ የሚሉትን ቡድን ጯሂ አድርገው እየዘመቱብን እኛ እርስ በእርስ ጦርነቱ ላይ የምንከራክርበት የቅንጦት ጊዜ የለንም። ይህ ያልረባ ክርክር ደጀን ያሳሳል፣ ለአሸባሪው የሞራል ስንቅ ይሆናል። አሁን ለመከራከር ጊዜ የለንም። ይህ ጉንጭ አልፋ ክርክር የምናደርግበት ወቅት ተጨማሪ ወገን ያሳጣናል እንጅ ሊያድነን አይችልም። በይደር የሚቆዩ ነገሮችም ካሉ አቆይቶ ከጦርነት በኋላ በሰፊው መመለስ ይቻላል።
17.2K views14:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 11:38:39
21.1K views08:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 11:38:30 ልዩነት!

የትህነግ ሰዎች ጎረምሳ ልጆቻቸውን በቅንጡ የውጭ አገር ዩኒቨርሲቲ ያስተምራሉ! የምስኪኑ ትግራይ አርሶ አደር ህፃናት ወደ ጦርነት ይማገዳሉ።
20.9K viewsedited  08:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 10:16:12
24.0K views07:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 10:16:02 የገጠመን እጅግ እልህ አስጨራሽ ትግል!

መጀመርያ ዲጅታል ወያነ ሆኖ ፌስቡክ ላይ የሚፅፍበትን ፌክ አካውንትን ሆኖ ነው። ሁለተኛው ራሱ ነው።
23.8K views07:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 06:42:36 ሰላም ለትግራይ ሕዝብ! ሰላም ለኢትዮጵያ!

የትህነግ አክቲቪስቶች "ሰላም! ሰላም!" እያሉ ነው። በጣም ጥሩ! እንኳን ደሕና መጣችሁ!

ለትግራይ ሕዝብም፣ ለኢትዮጵያም ሰላም የሚሰፍነው ግን ትህነግ ትጥቅ ሲፈታ ብቻ ነው። ትህነግ ትጥቅ ይፍታ! ሰላም ለትግራይ ሕዝብ፣ ሰላም ለኢትዮጵያ ይስፈን! ትህነግ በአስቸኳይ ትጥቅ ይፍታ! የሰላም እድል የሚፈጠረው ትህነግ ትጥቅ ሲፈታ ብቻ ነው! ሰላም የሚፈልግ በአስቸኳይ ትህነግን ትጥቅ ማስፈታት ላይ ይረባረብ!

ሰላም! ሰላም! ሰላም!
23.0K views03:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 21:51:08 እንዲህ ብናደርግስ ወገኖች!

1) ትህነግ የትግራይን ሕዝብ ምሽግ በማድረግ ነው የኖረው። እኛ የትግራይን ሕዝብ ብንፈርጅለት ደስታው ነው። ይቀሰቅስበታል። ስለሆነም ለትህነግ ላለማገዝ ትኩረታችንን ቡድኑ ላይ እናድርግ። በደስታም ሆነ ተናድደን የምንፅፈውን ትህነግ በሀሰት ለመቀስቀሻነት እንዳይጠቀምበት፣ ጠምዝዞ ሕዝብን እንዳያሳስትበት መጠንቀቅ ብንችል መልካም ነው። የትግራይ ሕዝብ በትህነግ አፈና ውስጥ ነውና ነፃ እንዲወጣ እየሰራ ያለውን የወገን ጦር በቀናነት ብናግዝ ለሁላችንም ይጠቅማል።

2) አሁን ያለንበት እጅግ ፈታኝ ወቅት ነው። የወገን ጦር ሲያሸንፍ ያን ክፉ ቡድን ጥፋቱ ይቀንሳል። ትህነግ ባይሸነፍ ህልውናችን አደጋ ውስጥ ይገባል። ስለሆነም የያዝነው የህልውና ጉዳይ መሆኑን አውቀን ያደሩ ልዩነቶቻችን ብንችል ማስታረቅ፣ ካልሆነ በይደር መተው ብንችል አሸናፊዎች እንሆናለን።

3) የወገን ጦር ጫካና ተራራ፣ ፀሐይና ዝናብ እየተፈራረቁበት ነው ለእኛው የቆመው። እኛ ፌስቡክ ላይ በሚፃፍብን ጉንተላ ወዘተ ስንጣላ፣ የወገን ጦር በምሽጉ አናት መድፍ እየጮኸበት፣ የሞርታር ጋጋታን እየጣሰ ነው ለእኛ የቆመው። ስለሆነም የወገን ጦር ለእኛ ሲል እየከፈለው ያለው ጋር አነፃፅረን እኛ ያለንበትን አለመግባባት ወዘተ ቀለል ብናደርገው መልካም ነው። በኮሜንት መተጋተግን እንደ ትልቅ ጦርነትና ፍልሚያ ከማየታችን በፊት እጅና እግሩ ቆስሎ እየተዋጋልን ያለውንም ብናስታውስ ጥሩ ይሆናል።

4) የወገን ጦር ሲያሸንፍ የምንደሰተውን ያህል ሳይቀናውም መታገስ አለብን። ብዙ ፈተናዎች አሉበት። ተከብቦ ለቀናት ውሃና ምግብ ሊያጣ ይችላል። ከራሱ ወገን ጋር ተመሳስሎ የሚመጣበት ትህነግን ማሰብ አለብን። እኛ በፕራንክ ስንደነግጥ እየዋል፣ የወገን ጦር የጥይት አረር ሰውነቱን ሲገርፈው እንደሚውልም ማስታወስ ይገባናል። እኛ የፌስቡክ ጩኸት አልችል ብለን የወገን ጦር ጆሮ የሚቀደውን የከባድ መሳርያ ድምፅ ብቻ ሳይሆን ጥይቱም በየአቅጣጫው እየመጣበት ችሎ እንደሚታገል ማስታወስ አለብን። ስለሆነም በብቃቱ ሲያሸንፍ የእኛ ድል እንደምናደርገው፣ በተለያየ ምክንያት ባይቀናው መረጃዎች ሳይኖሩን ዘልለን ተጠያቂ ከማድረግ ብንቆጠብ። ድክመቱንም የጋራ ማድረግ ብንለምድ መፍትሔ ለማምጣት ይቀልለናል።

5) የገጠመን ኃይል አወናባጅ ነው። መረጃን እንደዋነኛ ጦርነት ስልት ይጠቀምበታል። ሰርጎ ገብነትን ትልቅ ስልት አድርጎ ይጠቀምበታል። የእኛን መወዛገብ ይጠቀምበታል። ተደስተንም ሆነ ተናድደን የምናሰራጨውን እንደ መረጃ ይጠቀምበታል። ስለሆነም የገጠመንን ኃይል በሚገባ ተገንዝበን የምናሰራጨውን መረጃ ጉዳትና ጥቅም መዝነን መሆን ይኖርበታል። ሲቀናው ብቻ ሳይሆን ድክመቶች ሲኖሩም ለመታገስ፣ ተጋግዞ ችግሮቹን ለመቅረፍ ለራሳችን ቃል መግባት አለብን።

6) የወገን ጦር አባል ከመዋጋት ይልቅ ሰርቶ መብላትም የሚችልበት አቅም አለው። ባለሙያ፣ ባለሀብት ሆኖ ለእኛ ሕልውና የቆመ አለ። በዝናብና በፀሐይ የቡድን መሳርያ የሚሸከመው ከፍ ያለ አላማ ይዞ እንጅ ይህ አላማ ባይኖረው የቀን ስራ ሰርቶ፣ ሰራዊቱ ከሚያድርበት አውላላ ሜዳ አንፃር የሞቀ ከሚባል ቤት ማደር ይችል ነበር። ይህ ባይሆን እንኳን እንደ ክፉ ወጣት ዘርፎም መኖር ይችላል። በአንፃሩ ግን አሁን የግሉን ምቾት ህይወት አስይዞ ዋጋ እየከፈለ ነው። ለዚህ ዋጋ እኛም የበኩላችን ማውጣት አለብን። ማገዝ አለብን። ስንቅ፣ ልብስ፣ ደጀንነት ያስፈልጋል። እንደዚህ አግዘን፣ በቅርብ አይተነው፣ መረጃ ይዘን ሲያጠፋ፣ ሳይሳካለት ሲቀር ብንተቸው የተገባ ነው። ምንም አይነት ድጋፍ ሳናደርግለት፣ ሲያሸንፍ እየተደሰትን፣ ሳይቀናው ልንጮህበት ሞራል የለንም! ስለሆነም ከወገን ጦር የበኩላችን ማድረግ ይጠበቅብናል።

7) የወገን ጦር ወደ ትግራይ ከገባ ትልቁ ፈተና የሚሆነው ታፍኖ የከረመውን ሕዝብ ጉዳይ ማስተካከል ነው። ትህነግ የእርዳታ እህሉን ሲዘርፈው የከረመው የትግራይ ሕዝብ እርዳታ ይፈልጋል። ትህነግ አጥሮት የከረመው ድንበር ሲከፈትም በርካታ ስደተኛ ይኖራል። ስለሆነም ስለ ሰብአዊነት ያገናኛል የሚል ሁሉ የትግራይ ሕዝብን ለማገዝ ከአሁኑ ማሰብ፣ መዘጋጀት ይኖርበታል። ከአሁኑ ከታሰበበት የትግራይ ሕዝብን ማገዝ ቀላል ይሆናል።

8/ ይህ ጦርነት ብዙ ጉድ አሳይቶናል። ሞት ረክሶ ከርሟል። የምናውቀውንም የማናውቀውንም ወገናችን አጥተናል። ውድመቱና የተፈፀመው ሁሉ ስሜታዊ ያደርጋል። ቦታ ተያዘ ተለቀቀ እየተባለ ጭንቅ ከርሟል። ይህ ሁሉ ባሕሪያችንን ሊቀይር፣ ስሜታዊ ሊያደርገን ይችላል። በዚህ ምክንያት ብንሳሳት፣ ለወገን ጦር የማይጠቅም ነገር ብናጋራ መተራረምን መልመድ ይኖርብናል። ያልተጣራ መረጃን ወዳጅ ጠይቀን አረጋግጠን ማጋራት ብንችል።
24.0K viewsedited  18:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ