Get Mystery Box with random crypto!

Getachew shiferaw

የቴሌግራም ቻናል አርማ getachewshiferaw — Getachew shiferaw
የሰርጥ አድራሻ: @getachewshiferaw
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 44.30K

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 130

2022-08-31 12:46:38 የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ መከላከያውንም አስደምሟል!

ትህነግ በሌሊት በሱዳን በኩል ጦርነት መክፈቱን ተከትሎ የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ ጦርነቱ ወደተከፈተበት አካባቢ ተምሟል። ሴቶችና ወጣቶች ስንቅ ይዘው ሄደዋል። ሁመራና ማይካድራ ከተሞች ሱቅ ውስጥ ውሃ እስኪጠፋ ድረስ በመኪና እየጫኑ ወደሰራዊቱ አድርሰዋል። መከላከያ "ይህ ሁሉ ሕዝብ ለህወሃት ምንም አያደርግም እባካችሁ ተመለሱ። ብሎ ለምኗል። ሕዝቡ ደግሞ "ወያኔ ከመጣ እንኳን ሰው ዛፍ እንደማይተውልን እናውቃለንና ቀድመን እንፋለመዋለን" ብሏል። መከላከያው ብቻ ሳይሆን ሁመራና ማይካድራ ያለው ወጣትም በአርሶ አደሩ፣ በወጣቱ፣ በደጀኑ ሕዝብ ተገርሟል።

በአማራነቱ ምክንያት ተነግሮ የማያልቅ ፍዳ የደረሰበት ሕዝብ ትህነግ መጣ ሲባል እንደ ሰርጉ ይመለከተዋል። ከትህነግ ጋር የሚያወራርደው ሂሳብ አለውና።
16.7K views09:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 12:08:25
13.8K views09:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 12:08:21 ህዝብን የሚረብሽ ዜና የምትሰሩ ወገኖች ከዚህ ተማሩ!

በፎቶው የምታዩዋቸው በወልዲያ ከተማ ሰርገው ገብቶ የተያዙ የትህነግ ደህንነቶች ናቸው። መላጣው በመከላከያ ሰራዊት የ7ኛ ሜካናይዝድ ክፍለ ጦር ውስጥ የጀኔራል መድፍ ተኳሽ እና ከሱዳን የተመለሰ ነው።

እነዚህ የትህነግ ደህንነቶች ዋናው አላማቸው ሰራዊቱን ደጀን ማሳጣት ነው። እነሱ የቀጠሯቸው ሰርጎ ገቦች ቀድመው እቃ የጫነ መኪና እንዲወጣ አድርገው ፎቶ አንስተው በማህበራዊ ያሰራጩታል። በሜሴንጀር ይልካሉ። ለከተማው ህዝብም ሰራዊቱ ስለሸሸ እየወጣን ነው ብለው ይነግሩታል።

ከጦር ግንባር የተቀየረ፣ በሌላ መስመር ትዕዛዝ የተሰጠውን ሰራዊት ፎቶ እያነሱ ታዋቂ ሰዎች ከሚፅፉት ስር ይለጥፋሉ። በሜሴንዠር ግሩፕ ያስቀምጡታል። ሌላው ሳያውቅ ያጋራዋል።

እነዚህ ደህንነቶች ከየከተማው መጀመርያ እንዲወጣ ያደረጉትን ሰርጎ ገባቸውን በሚቀጥለው ከተማም ያሰሩታል። ተፈናቃዩን በየ መንገዱ የሽብር ወሬ ይለቁበታል። ተፈናቃዩ ይህን የትህነግ ደህንነቶች ወሬ ለሚያውቀው ሰው በንዴት ያደርሳል። ይህ ወሬ የደረሰው ከዛው ከቦታው የደረሰኝ ነው እያለ ያሰራጨዋል። ህዝባችን ይረበሻል። ትህነግ አላማውን ያሳካል።

ትህነግ በተደራጀ መልኩ የእኛን ወገን ተጠቅሞ ፕሮፖጋንዳ እየሰራ ነው። የህዝብ ጉዳይ ያገባኛል የሚሉ ወገኖች መረጃ ከማጋራታቸው በፊት የዚህ የትህነግ ፕሮጀክት ሰለባና አጋዥ እንዳይሆኑ ቢማሩበት መልካም ነው።
14.0K views09:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 11:33:48
16.9K views08:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 11:33:36 በዓለም አቀፍ ደረጃ የቅጥፈት ውድድር ቢኖር የሚችላቸው የለም።


ከስድስት ወር በፊት የዓለም ተቋማት ኃላፊዎች በግልፅ የትግሬ ወራሪ አማራ ክልል ላይ በርካታ እርዳታ ዘርፏል። ይህን የተቋማቱ ኃላፊዎች ተናግረዋል። በቪዲዮው ተያይዟል። ጌታቸው ረዳ ደግሞ ሰሞኑን ለሰረቁት ነዳጅ መልስ ሲሰጥ መስረቅ ብንፈልግ አማራ ክልል ላይ መጋዘኖችን እንዘርፍ ነበር ይላል። አማራ ክልል ያሉ መጋዘኖችን መዝረፋቸውንኮ ነዳጅ ከመዝረፋቸው ቀደም ብሎ ዓለም ተነጋግሮበታል።

ቪዲዮው የአስፋው አብርሃ ገፅ ላይ የተወሰደ ነው።
17.2K viewsedited  08:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 10:25:53
18.4K views07:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 10:25:42 ጎንደር!

ክፉዎች የእምነት ግጭት ለመቀስቀስ የሚሰሩበትን፣ ሰበብ ፈልገው በሀሰት የጎንደርን ስም የሚያጠፉበትን ጉዳይ አባቶች ተነጋግረው ፈትተውቷል።
18.1K views07:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 19:09:48 ታሪክ የማይረሳው ተጋድሎ!

ትህነግ በራያ ግንባር እስካሁን ባለው መረጃ ከሁለት መቶ ሺህ የማያንስ ኃይል ይዞ መጥቷል። የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት፣ የአማራ ልዩ ኃይል፣ የምስራቅ አማራ ፋኖ እና ሚሊሻው የታገለው ከዚህ ኃይል ጋር ነው። ባለፈው ቆቦን፣ ትናንት ወልዲያን ለመያዝ የአሸባሪው ቡድን ብዙ ኃይል አልቆበታል። ብዙ አልቆበት ወልዲያን የመያዝ ህልሙ ለጊዜው በጀግኖቻችን መክኖበታል። በሕዝባዊ መአበል የጀመረው ጦርነት ለወገን ጦር ከፍተኛ ግፊት የፈጠረ ቢሆንም የወገን ጦር በጀግንነት ሲፋለም ከርሟል።

ፌስቡከኛው ሰግቶ የሸሸ ወገናችን ፎቶ ይለጥፋል እንጅ ብዙ የሚነገርለት ጀግናም ሞልቷል። ለሰራዊቱ ደጀን የሆኑ ወጣቶች፣ ምግብ እያበሰሉ የሚያቀርቡ እናቶች፣ ሰብሉን ትቶ ከሰራዊቱ ጎን የተሰለፈው አርሶ አደራችን ታሪክም በደማቅ ታሪክ የሚፃፍ ነው። እነዚህ ጀግኖች ለክብራችን ተዋድቀዋል። ሌላው ህዝባችን እንዳይጎዳ በርካታ ዋጋ ከፍለውልናል።

በአካል፣ በስልክ፣ በፌስቡክ የማውቃቸውን የራያ፣ የወልዲያ አካባቢ ወገኖች ደውዬ አነጋግሬያለሁ። ብርታታቸው የሚገርም ነው። ቤተሰቦቻቸው የተገደሉባቸው፣ የተዘረፉባቸው፣ ቤተሰቦቻቸው ይሙቱ ይኑሩ የማያውቁ ናቸው። ብዙ ነገሮችን እምቅ አድርገው ችለው መንፈሳቸውን ያበረቱ ጀግኖች ናቸው። የቤሰተቦቻቸውን ሕመምና ስጋት በሚገባ ያልተረዳንላቸው፣ ነገር ግን በርካታ ፅኑ ወገኖች አሉን። አሉባልታና ወሬ፣ ሰበርና አሳዛኝ ዜና ከሚለጠፈው በላይ የእነዚህ ጀግኖቻችን ፅናት ብዙ ትርጉም ነበረው። ለእኛ ሲሉ በየጥሻው ትህነግ ጋር ተናንቀው መስዋዕትነት የከፈሉ ጀግኖች፣ በአካባቢው ንቅንቅ ሳይል ለሰራዊቱ ደጀን የሆነው በርካታ ሕዝባችን ፅናት ሊያስተምረን፣ ላላወቀው ልናሳውቅ ሲገባ እንቶፈንቶው ሊያጨቃጭቀን አይገባም ነበር።
15.3K viewsedited  16:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 18:44:02 አንድ ነገር ልለምናችሁ!

( ዘሪሁን ገሠሠ )

ምንም ዝርዝር ሳያስፈልገው ፥ ለአማራ ህዝብ ብሎም ለወንድሞቻችን የምታስቡ ከሆነ ፋኖን በተናጠልም ሆነ በቡድን አብሮት እየተዋደቀ ካለው የሀገር መከላከያ ሰራዊትና ልዩ ሀይል ነጥላችሁ ከማወደስና ሌላውን ከማንኳሰስ ትታቀቡ ዘንድ በተማፅኖ ጭምር ላሳስባችሁ እወዳለሁ!

ሌላው…!

በተረጋገጠ መረጃ ወያኔ በሰው ማዕበል በራያ ግንባር ያለውን ሜካናይዝድ ጦር ለመማረክና በወልቃይት በኩል የተቀናጀ ጥቃት ለመጀመር ያቀደችው እቅድ በጀግኖቹ የኢትዮጵያ ልጆች መስዋትነት እንዳሰበችው ሊሳካ አልቻለም!

እንደተለመደው ሠውን እንደጥይት ማብረጃ እየተጠቀሙ የመጡበት መንገድ በጎብዬ ፣ በቃሊምና በመሳሰሉት በሁሉም የግንባሩ አቅጣጫዎች በደም ዋበላ እንዲታጠቡ አድርጓቸዋል፡፡ ከፍተኛ ዋጋን ከፍለውበታል!

ይህ ማለት አንድ ሙከራ ሞክረው ሲከሽፍ ሌላኛውን አይቀጥሉም ማለት ባለመሆኑ ፥ ሁሉም ለህዝባዊ ሀይሉ ደጀን በመሆን ፥ በግንባር ካለው ሀይል ጋር በመሠለፍና በፐርሶኔልም ሆነ በሎጂስቲክስ ረገድ እጅግ ትልቅ አቅም በመፍጠር ወያኔ በወልቃይት በኩል ያቀደውን እቅድ ራያ መሬት ላይ ከአፈር መቀላቀል ይገባል!
16.4K views15:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 18:05:48 ሕዝብን ማሸበር እውነተኛ አያስብልም!

ጉዳዪ የጦርነት ነው። አውዳሚ ነው። ወገናችን የተሰቃየበት ነው። ሴቶች የተደፈሩበት ነው። ሕዝብ ይህ አደጋ መልሶ መጣ ሲባል ቢፈናቀል አይገርምም። ስራ ያልሰራነው እኛው ነው። አሸባሪው ከተፈናቃይ ጣቢያ አምጥቶ ሲወርረን እኛ የሞቀ ቤቱ ያለውን ሕዝብ እንዲሳደድ እያደረግን ነው። ከባለፈው ጦርነት በኋላ ብዙ ስራ አልተሰራም። ያ አልበቃ ብሎ ግን ሕዝብን በሆነው ባልሆነው ማሸበር ከጠ*ላ*ት የማይለት ተግባር ነው። ጠ*ላ*ት በሰርጎ ገብ በኩል ውጡ መከላከያ ሸሽቷል እያለ ሲያሸብር እናውቀዋለን። የሰራዊት ልብስ ለብሶ ጭምር ብዙ ድራማ ሰርቷል። ፌስቡክ ላይም ይህን ሽብር እየፃፉ ያሉ ሰዎች እንደ እውነተኛ እየተቆጠሩ የጀግንነት ስራ አድርገው ቀጥለውበታል። ሕዝብ ሰግቶ በሸሸበት ለሰራዊቱ ደጀን የሚሆን አይገኝም። ሕዝብን ከቀየው እንዲሸሽ እያደረግን ከሌላው የኢትዮጵያ ጫፍ የመጡ ወንድሞቻችን ሕዝብ ነቅሎ ከወጣ ለምን እዋጋለሁ ብለው ቢሸሹ ችግሩ የእነሱ ብቻ አይሆንም። ችግሩ በሕዝብ ላይ ሽብር የሚፈጥረው አካል ነው።

ትህነግ ሰሞኑን በገባባቸው አካባቢዎች ከየትኛውም በላይ ተዘግተው የተገኙ ቤቶች ምንም ሳይተርፋቸው ተዘርፈዋል። ያልሸሹት ቢያንስ የተወሰነ ነገር ተርፎላቸዋል። ሕዝብ ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ የሚፅፈውን አመዛዛኝና አሳቢ አድርጎ ያስባል። ያምናል። እውነትም ሆነ ሀሰት እንዲሳደድ የሚያደርገው መረጃ ሲለጠፍም ከእነዚህ አረመኔዎች ለማምለጥ ቢሞክር በእሱ አይፈረድም። የመጀመርያው ችግር ሳያውቀው ህወሃት ለሰርጎ ገብ የሰጠውን ሚና የሚወጣው አካል ነው።

የሚገርመው ደግሞ የሽብር ወሬ ሲነዙ ከቆዩ በኋላ ሕዝብ አካባቢውን ለቅቆ ሄደ ብለው የሚወቅሱ፣ ፎቶውን እየለጠፉ ሁለተኛ ሲዘልፉት የሚውሉ ለህዝብ ያገባናል የሚሉ ሰዎችም አሉ። ሕዝባችን ከጥይት በላይ የማሕበራዊ ሚዲያ ዜና እንዲያሸብረው ብዙ ተሰርቶበታል።

አንዳንዶቹ ደግሞ እውነቱ ካልተዘገበ ወዘተ ይላሉ። እውነት ምንድን ነው? ከተማ ተያዘ ብሎ መፃፍ የሀቀኝነት መለኪያ የሆነበት ምክንያት በራሱ ግራ የሚያጋባ ነው። አሁን አሁንማ የእኛው ፌስቡከኛ ቀድሞ ስለሚያስጮኸው የትህነግ ፌስቡከኞች ሰበር ዜና ብለው መስራቱን ትተውታልኮ። ጥቅሙ ምን እንደሆነ ሳይታወቅ የሚለጠፈው ነገር በዝቷል። ሕዝብን የሚያስጨንቅ ነገር በደፈናው ይፃፋል። ማስፈራሪያ ይፃፋል። በጦርነቱ አካባቢ የሚኖረው ሕዝብ ሳይሆን ራቅ ካለ ቦታ የሚኖረው ዘመድ አዝማድ፣ ወገን እንቅልፍ አጥቶ ያድራል። ይህ ለውጥ የሚያመጣ ቢሆን መልካም ነበር። ያለንን መረጃ ለሕዝብ በሚጠቅምና፣ ጠላት በማይጠቀምበት መንገድ ብንገልፅ ጥሩ ነው።

ፌስቡከኛው እንደዚህ አያያዙኮ እውነት ሁሉ መፃፍ አለበት ብሎ በጀግንነት የተሰዋን ሰው ሁሉ በፌስቡክ ሊያረዳ ይችላል። በተለመደው መንገድ እንኳን ሰው ሲረዳ ጊዜና ቦታ ተጠብቆ ነው። ገበያ ላይ እያለ አይነገርም፣ ሰርግ ላይ ሆኖ አይነገርም፣ መንገድ ላይ ሆኖ አይነገረውም። ግዴታ ካልሆነ ምሽት ላይ አይነገረውም። ብዙውን ጊዜ ቤቱ ከገባ በኋላ በጠዋት ይነገረዋል። ያውም መቸ ይነገረው፣ ማን ይንገረው፣ እንዴት ይነገረው ተብሎ ነው። ራቅ ያለ አካባቢ ከሆነ ደግሞ የሞተ ዘመዱ እንደታመመፐተደርጎ ነው ድረስ ተብሎ ነው የሚላክበት፣ አሊያም ሰበብ ተፈልጎ እንዲሄድ ይደረጋል። ይህን ያደረገው ውሸታም አይባልም። ይህ ሁሉ ሰውን ላለመጉዳት ሕዝባችን የሚያደርገው ነው። አይደለም የጦርነትን ያህል የግለሰብ ጉዳይ እንኳን በሕዝባችን ዘንድ የሚነገርበት ወግ አለው። ህፃናት፣ ነፍሰ ጡሮች፣ አዛውንቶች እንዳይሰሙ ተብሎ የሚደበቃቸው እውነት አለ። ይሸበራሉ፣ ይጨነቃሉ፣ ይታመማሉ ተብሎ ነው። የሕዝባችን ወግ ይሄ ነው። እውነት የተባለው ሁሉ ሲዘረገፍ አይውልም። እያንዳንዱ ፌስቡክ ላይ ሲሆን የሕዝብን ጉዳይ "እውነት ስለሆነ ይፃፍ" የሚለው ለቅርብ ቤተሰቡ ይጨነቃል ብሎ የማይነግረው እውነት አለው። ለራሱም ደግሞ ደጋግሞ የማይነግረው ማስረሻ የሚፈልግለት አስጨናቂ እውነት አለ። የአሁኑ ፌስቡከኛ ግን እንዲሁ ያገኘውን ሳያጣራም ጭምር ይለጥፋል። እውነቱ ይውጣ ወዘተ ይባላል። ሕዝብ የሚያሸብር እውነት ምኑን ይጠቅማል? ሕዝባችን ስለተሳደደ ምን ጠቀምነው?

የሕዝብን ስነ ልቦና መጠበቅ አንደኛው የትግሉ አካል ነው። ስነ ልቦናው የተጎዳ ሕዝብ ሁሉ ተጠቂና ተሳዳጅ እንደሆነ ነው። ሕዝባችን እረፍት የሚነሱ ነገሮችን ጥሬ እውነት ናቸው ብለን አደባባይ ላይ ስንደፋ መዋል የለብንም። ሕዝባችን ያጠቁት አካላት በርካታ ሰው ሞቶባቸዋል። ነገር ግን በአደባባይ ሲያለቅሱ አናያቸውም። ሟቾቹን ስለማይወዷቸው አይደለም። ከስነ ልቦና አንፃር ስለሚያዩት ነው።

እውነት የሚገለፅበት አግባብ፣ ቦታና ሁኔታ አለው። ዝም ብሎ የትም አይጣልም። ፌስቡክ የሚጠቅምም የማይጠቅምም እውነት የሚጣልበት ሜዳ ሆኗል። በዚህ ጦርነት ወቅት ከዚህ መለየት ይኖርብናል። ለሕዝብ የሚጠቅመው እውነት ብቻ ነው መነገር ያለበት። ሰበር ዜናውም የህዝባችን ስነ ልቦና የሚሰብር ዜናም እውነት እየተባለ ባይለጠፍ ጥሩ ነው።

ይህ የፖለቲካ መድረክ ነው። የጦርነት ወቅት ነው። ሌሎች በሴራ፣ እውነታን ከእነሱ አንፃር በመመንዘርና በመጠምዘዝ ፕርፖጋንዳ በሚያበዙበት ወቅት እውነት ነው እየተባለ የሆነ ያልሆነው አይለፈፍም። እውነተኛም አያስብልም።
23.2K viewsedited  15:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ