Get Mystery Box with random crypto!

Tofik Bahiru

የቴሌግራም ቻናል አርማ fiqshafiyamh — Tofik Bahiru T
የቴሌግራም ቻናል አርማ fiqshafiyamh — Tofik Bahiru
የሰርጥ አድራሻ: @fiqshafiyamh
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 6.13K

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2023-04-11 19:22:18 ኢማም ነወዊይ [ረዐ] እንዲህ ብለዋል: ‐
«የመጨረሻዎቹ የረመዳን ሌሊቶች በሙሉ ለይለቱል‐ቀድር ሊሆኑ ይችላል። ነገርግን ነጠላ ቁጥሮቹ የበለጠ ይከጀላሉ። ሻፊዒዮቹ ዘንድ ደግሞ #ሃያ #አንደኛው ሌሊት በይበልጥ #ለይለቱል‐ቀድር ሊሆን ይከጀላል ተብሎ ይታመናል።»
የረመዳን 21 ሌሊት #ዛሬ ነው!
https://t.me/fiqshafiyamh
1.2K viewsedited  16:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 14:54:01 ዱዓ ሰብሳቢ በሆኑ ቃላት፣ ለለአላህ በመዋረድ እና በልመና መዋደቅ የሚንፀባረቅበት ከልሳን በፊት በቀልብ የሚከወን ዒባዳ ነው። ከመቼው ባለቀ በሚል የደከመው እና የተሰላቸ መእሙምና የሀፈዘውን በደረቅ መንፈስ በሚያነበንብ ኢማም መካከል የዱዓ ስሜት ይቀጭጫል። የሷሊሖቹ ዱዓ በተለይም በቁርኣኑ ውስጥ በተጠቀሱት ስፍራዎች ላይ ከሰባት አረፍተ ነገር አይበልጥም። የነቢዩ ዱዓዎች ጥቅል ይዘትና ግሩም ውበት ያላቸው ነበሩ። ኢስቲጃባ ያለው ቃላት በማርዘምና ብዙ በመቆም ሳይሆን በተዶሩዕና በኹዱዕ ነው!
እባካችሁ ሐፊዞቻችን ቁኑታችንን ለወገባችን ጤና እና የረዘመ ነገር ለምትሰለቸው ቀልባችን የተመጣጠነ ጣፋጭ የዱዓ ጊዜ አድርጉልን!
1.2K views11:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 04:04:24 «አዩሃል‐ወለድ»፣ ከገፅ 51‐67
ኢማም፣ ሸይኹል‐ኢስላም፣ ሑጀቱል‐ኢስላም፣ በረከቱል‐አናም፣ አቡ ሓሚድ አል‐ገዛሊይ
ክፍል 6
311 views01:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-10 21:24:04 ረመዳን እና ዘካ?
==========
ብዙ ጊዜ በረመዳን ስለ ዘካ ይወራል። ሰዎች ሂሳባቸውን ይሰራሉ። ዘካቸውን በረመዳን ይሰጣሉ። ዐሊሞችም አብዝተው ስለዘካ ህግ ያስተምራሉ። ረመዳን እና ዘካ ያላቸው ትስስር ምንድን ነው?
እርግጥ ነው ረመዳን የዒባዳ ወር ነው። ምንዳ ይነባበርበታል። የሰዎች ቀልብም ለመልካም ስራ ይነሳሳል። ነገርግን በጊዜ የማይገደበው ዋጂብ ዘካን በረመዳን የገደበው ምንድን ነው?
በረመዳን ዘካ መስጠትስ ብይኑ ምንድን ነው?
:
በረመዳን የሚሰጡ ዘካዎች ሦስት ዓይነት ናቸው: ‐
⚀ በረመዳን አመቱ የሞላ ዘካ አንደኛው ነው። ለምሳሌ: ‐ ሰውየው ንግድ የጀመረው ባለፈው ረመዳን ከሆነ ዓመቱ የሚሞላው በመጪው ረመዳን ላይ ነው። በዚሁ በየዓመቱ ረመዳን የዘካ ዓመቱ የሚዘዋወርበት ወር ሆኖ ይቀራል። ስለዚህ በረመዳን ዘካውን እየሰጠ ይቀጥላል።

⚁ ሁለተኛው: ‐ ከረመዳን በኋላ ዓመቱ የሚሞላ ዘካ ሆኖ ሰውየው ግን በገዛ ፈቃዱ ዘካውን አስቀድሞ በረመዳን ሊሰጥ ይችላል። ይህም መልካም ነው።
ስለዚህ በሁለቱ ምክንያቶች በረመዳን ወር ዘካውን የሰጠ ሰው የተፈቀደለትን ስራ ሰርቷል።

⚂ ሦስተኛው: ‐ ሰውየው ቀድሞ የወጀበን ዘካ ረመዳን እስከሚገባ ድረስ አቆይቶ የሚሰጥበት ሁኔታ ነው። ይህ የተከለከለ ነው። ዘካ አመቱ ከሞላ በኋላ ረመዳንን ጥበቃ ማቆየት ሐራም ነው። ዘካውን በወጀበበት ጊዜ ወዲያው መስጠት ግዴታ ነው። ዘካ ሰጪው የረመዳኑን ትሩፋት ማግኘት ከፈለገ ከዘካ ውጪ ትርፍ ሶደቃ ማድረግ እንጂ የድኾችን ሐቅ በጫንቃው ላይ ዋጂቡ ካረፈበት በኋላ ሆን ብሎ ማቆየት ክልክል ነው።

በዚሁ አጋጣሚ ለማስታወስ ያክል ከመወጀቡ በፊት አስቀድሞ ዘካውን የሰጠ ሰው ዘካውን ከሰጠበት ቀን አንስቶ አመቱ እስከሚሆንበት ቀን ድረስ ያለውን የገንዘብ ዓቅም በዘካው አመት መጨረሻ ላይ ያሰላል። ከዚያም ዘካ የሚመለከተው የገንዘብ መጠን አስቀድሞ ዘካ ካወጣበት መጠን በልጦ ከተገኘ ተጨማሪውን የዘካ መጠን አስቦ ማውጣት ግዴታው ነው!
አላሁ አዕለም!
https://t.me/fiqshafiyamh
599 viewsedited  18:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-10 09:34:51 የገንዘብ ዘካችንን በምን እንተምን?
======================
የገንዘብ ዘካ አነስተኛ የሀብት መጠንን (ኒሷብን) ለማወቅ የወርቅ ዋጋን መጠቀም ተገቢ ነው። አንዳንድ ሰዎች በብር (ሲልቨር) ይተምናሉ። ይህ ትክክል አይደለም።
በእርግጥ ነቢዩ [ﷺ] የዘካን ኒሷብ በብር እና በወርቅ ያስቡ ነበር። ነገርግን ያን ያደረጉት ሁለት አይነት ኒሷብ ለመመደብ አስበው አይደለም። ኒሷብ አንድ ነው። ይሁንና በርሳቸው ዘመን በሁለት የገንዘብ ዓይነቶች ተተምኗል። ኒሷብ በሸሪዓው "አነስተኛ የሀብት መጠን" ማለት ነው።
:
ዘካ የተደነገገው በሀብታሞች ላይ ነው። የሚሰጠው ደግሞ ለድኾች ነው። ስለዚህ በኒሷብ የሚወሰነው ሀብታም ማን ነው? የሚለው ጥያቄ ነው። ሸሪዓው የሀብት መለኪያ የሚሆን አነስተኛ መጠን አስቀምጧል። ይህ ኒሷብ ተብሏል።
:
በተለያዩ የሀብት ዓይነቶች ላይ በተለያየ ሁኔታ ኒሷብ (አነስተኛ የሀብት ደረጃ) ተገምቷል። ለምሳሌ: ‐ በነቢያዊው ዘመን የነበሩት መገበያያዎች ሁለት ነበሩ፤ ወርቅ እና ብር። ኒሷብ በሁለቱ የገንዘብ ዓይነቶች ተገምቶ ተቀምጧል።
ሃያ 'ሚስቃል' ወይም 85 ግራም ወርቅ የወርቅ ገንዘብ መነሻ ኒሷብ ተደርጓል። በተጨማሪም ሁለት መቶ ዲርሃም ወይም 595 ግራም ብር የሀብት መለኪያ ተደርጓል።
ነገርግን ነቢዩ [ﷺ] በሁለቱ የገንዘብ ዓይነቶች ሀብትን የለኩበትን ምክንያት ማወቅ ያስፈልጋል።…
:
ዐረቦች ከነቢዩ [ﷺ] መላክ በፊት ሁለት የገንዘብ ዓይነቶችን ይጠቀሙ ነበር። አንደኛው ከፋርስ የመጣ ነው። ሌላኛው ከሮማ የመጣ ነው። የብር ገንዘብ ወይም ዲርሃም ከፋርስ፤ የወርቅ ገንዘብ ወይም ዲናር ደግሞ ከሮም። በወቅቱ ዐረቦች የራሳቸው የመገበያያ ገንዘብ አልነበራቸውም። የሀብት መለኪያ እና የግብይት መተመኛ አድርገው የሚወስዱት ሁለቱን የገንዘብ አይነቶች ብቻ ነበር።
በመሆኑም ነቢዩ [ﷺ] አነስተኛውን የሀብት መጠን በእነዚህ የገንዘብ ዓይነቶች ለክተዋል። ሃያ ዲናር ወርቅ ወይም ሁለት መቶ ዲርሃም ብርን የሀብት መነሻ አድርገው መድበዋል።
:
በወቅቱ አንድ ዲናር በዐስር ዲርሃም ይመነዘር ነበር።
ነገርግን ከዚያ በኋላ የብር ዋጋ እየቀነሰ መጣ። በኸሊፋዎች ዘመን አንድ ዲናር በአስራ ሁለት ዲርሃም ተመነዘረ። ከዚያም በአስራ አምስት ገባ። ከዚያም በሃያ ዲርሃም፣ ከዚያም በሰላሳ ዲርሃም እያለ ሄደ።…
በዚህ ዘመን ደግሞ ብር ከወርቅ አንፃር እጅግ በጣም ረከሰ። በወርቅ እና በብር ኒሷብ መካከል እጅግ ሰፊ ልዩነት ተፈጠረ። በወርቅ ሂሳብ መሰረት ከመቶ ሃምሳ ሺህ የኢትዮጲያ ብር በላይ ኒሷብ በተደረገበት ሁኔታ በማእድኑ ብር ተሰልቶ ከሃያ ሺህ ብር በታች ያለን ገንዘብ የሀብታምነት መነሻ ማድረግ አግባብ አይሆንም!
:
ስለዚህ ቀልብን የሚያረጋጋ፣ የማይለዋወጥ እና መለኪያ ተደርጎ ሊያዝ ያሚገባው ቋሚ የሀብት መለኪያ ወርቅ ብቻ ነው።
በተጨማሪም ከሌሎች የሀብት ዓይነቶች ኒሷብ ጋር ሁሌም ተመጣጣኝ ሆኖ የሚገኘው ወርቅ ነው። በሌሎች የዘካ ዓይነቶች ላይ ከተመሰደቡት የኒሷብ መጠኖች፣ ከአምስት ግመል፣ ከአርባ ፍየል፣ ከሰላሳ ከብት ጋርም ይመጣጠናል።
:
በጥቅሉ በአንድ ሰው ላይ የሀብት ዘካ መኖሩን ለማረጋገጥ ወርቅን በመለኪያነት መጠቀም አስፈላጊ ነው። ሰውየው ሰማንያ አምስት ግራም ወርቅ ሊገዛ የሚችል የወረቀት ገንዘብ ካለው እና ሌሎች የዘካ መስፈርቶች ከተሟሉ ዘካ አለበት።
ወርቅ ደግሞ ከጥራት አኳያ ይለያያል። ከአስራ አራት ካራንት ጀምሮ እስከ ሃያ አራት ካራንት ድረስ ጥራቱ እየጨመረ ይመጣል። ስለዚህ መካከለኛ የጥራት ደረጃ የሆነውን አስራ ስምንት ካራንትን በመያዝ ሂሳቡን ማስላት ተገቢ ነው የሚሉ ሸይኾች አሉ። በእርግጥ አንዳንድ ዓለም አቀፍ የፈትዋ ማእከላት ሃያ አንድ ካራንትን እና ሃያ አራት ካራንትን ሲጠቀሙም አስተውያለሁ። እንደውም ሀገራቱን ለመጥቀስ ያህል የግብፅ የፈትዋ ኮሚቴ ሃያ አንድ ካራንትን፣ የኦርዶን የፈትዋ ኮሚቴ ሃያ አራት ካራንትን፣ የአልጄሪያ የፈትዋ ኮሚቴ ደግሞ አስራ ስምንት ካራንትን መለኪያ አድርገዋል።
እንደውም ግብጾቹ ቀድመው ከሰጡት ፈትዋ ከሃያ ሦስት ነጥብ አምስት ካራንት ወደ ሃያ አንድ ካራንት ፈትዋቸውን የለወጡበትን ምክንያት ሲያስረዱ «ቀድመን እንሰጥበት የነበረው የ23.5 ካራንት ፈትዋችን ድኾችን ይጎዳል ብለን በማሰብ፣ ለድኾች ጥቅም ቅድሚያ ለመስጠት ሲባል ወደ 21 ካራንት ለመዞር ወስነናል።» በማለት ነው።

በአፕሪል 07/2023 ቀን በተለጠፈው የኢትዮጲያ ብሄራዊ ባንክ መደበኛ ድረ ገፅ መረጃ መሰረት የ21 ካራንት ወርቅ የአንድ ግራም የመግዣ ዋጋ 2952.9070 የኢትዮጲያ ብር ነው። ስለዚህ በዚህ ፈትዋ መሠረት የሰሞኑን የገንዘብ ዘካ ኒሷብ በ21 ካራንት ወርቅ ሲሰላ 85 ግራም * 2952.9070 ብር = 250,997.095 ብር (ሁለት መቶ ሃምሳ ሺህ ዘጠኝ መቶ ዘጠና ሰባት ብር ግድም) ይመጣል።

እንደ አዲስ አበባችን እና የሸዋ ግዛት ሁሉ በርካታ ሻፊዒዮች የሚገኙባቸው፣ የሻፊዒያ መዝሀብ በእጅጉ የሚጠናባቸው እና በመዝሀቡ ፈትዋ የሚሰጥባቸው የየመን እና የኦርዶኖቹን ፈትዋ መነሻ በማድረግ ሰማንያ አምስት ግራም የሚታሰበው በሃያ አራት ካራንት ነው ብለን ስንነሳ ደግሞ የሰሞኑን የገንዘብ እና የንግድ ዘካ ስሌት እንደሚከተለው ይሆናል: ‐
ከላይ በጠቀስኩት የመረጃ ምንጭ መሰረት የ24 ካራንት የአንድ ግራም ወርቅ ዋጋ 3374.7509 ብር ነው። ስለዚህ በሰማንያ አምስት ግራም ሲባዛ 286,853.8265 (ሁለት መቶ ሰማንያ ስድስት ሺህ ስምንት መቶ ሃምሳ ሦስት ብር ግድም) ይመጣል።

ለድኾች ይጠቅም ዘንድ የዘካ ቋቱን ለመጨመር የአንዳንድ የፈትዋ ኮሚቴዎችን እና መሻዪኾችን ሃሳብ ተጠቅመን መካከለኛ የጥራት ደረጃ ባለው 18 ካራንት ካሰብነው ደግሞ የአንድ ግራም ወርቅ ዋጋ ብር 2531.0632 (ሁለት ሺህ አምስት መቶ ሰላሳ አንድ ብር አካባቢ) ነው። ይህንን በሰማንያ አምስት ግራም በማባዛት ኒሷቡ 215,140.372 (ሁለት መቶ አስራ አምስት ሺህ አንድ መቶ አርባ) ብር ይመጣል።

ስለዚህ ከዚህ ጀምሮ ሌሎች የዘካ ሹሩጦችን ያሟላ ሀብት ያለው ሰው 2.5% ዘካውን መክፈል አለበት። በበኩሌ ጥንቃቄ ለመውሰድ እና ድኾቹን ለመጥቀም ሲባል ከሁለት መቶ ሺህ ብር በላይ መስፈርቱን ያሟላ የዘካ ገንዘብ ያለው ሰው ዘካውን ቢከፍል መልካም ነው እላለሁ።
አላሁ አዕለም!
https://t.me/fiqshafiyamh
1.0K viewsedited  06:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-09 00:01:02
ሰውን ያላመሰገነ አላህን አያመሰግንም!
የምታዩት ዛሬ ማንነቱ እንዳይታወቅ የፈለገ ወንድም/እህት ያበረከተልኝ የከበረ ስጦታ ነው። አላህ በኸይር ስራ ሚዛኑ ላይ ያኑርለት። ሰው ለሰው በሰጠው ክብር ልክ አላህም ሆነ ሰው ዘንድ ይከበራል። እኔን ከሰው መቁጠሩን ለርሱ/ሷም የክብር ማእረግ ያድርግለት። ከገመተኝ በላይ ያድርገኝ። ዐይቤንም ሆነ የሰጪውን ዐይብ ይሸፍንልን። ወንጀላችንን ይተውልን። የመልካም ስራ እድሜያችንን ያርዝምልን። የርሱንም ሆነ የሙእሚኖችን ፍቅር ይስጠን!
ደርሶኛል፤ ጀዛኩሙላሁ ኸይረን!
1.2K viewsedited  21:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-08 15:40:55 ሸሂድ ሆነ!…
ጀነት ገባ!…
በመሀል ምንም የለም።
ሸሂድ ሆነ!…
ያለ ጥርጥር ጀነት ገባ!
:
በድር ወስጥ የዑመይር አይነት ሰዎች በርካታ ናቸው፡፡ የአላህ መልክተኛ [ﷺ] ባልደረቦቻቸውን ያነጹት በጀነት ፍቅር ነው፡፡ በጀነት ውስጥ የልፋት ዋጋ ይገኛል፡፡ በጀነት ውስጥ ድካም ይረሳል፡፡ ቁስል ይሽራል፡፡ አላቂው ሕይወት በዘልዓለማዊነት ይተካል፡፡
‹‹የጀነት ሰዎች ሆይ! በህይወት መኖር ጸደቀላችሁ፤ መቼም ቢሆን አትሞቱም፡፡ ዘልዓለም በጤና ትኖራላችሁ፤ መቼም ቢሆን አትታመሙም፡፡ ሁሌም ወጣቶች ትሆናላችሁ፤ መቼም አታረጁም፡፡ ሁሌም በጸጋ ውስጥ ትኖራላችሁ፤ መቼም ቢሆን አትቸገሩም፡፡››
ይህ የአላህ አዋጅ ነው!
የበድር ድል በጀነት ፍቅር የተሰራ ድል ነው!
አሁን ነፍሴንና ወዳጆቼን ልጠይቅ ጀነትን ናፍቀናል? በምንስ ተዘጋጅተናል!?
https://t.me/fiqshafiyamh
1.5K views12:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-08 15:40:54 የበድር ዘመቻ እና የጀነት ናፍቆት
¨¨¨¨¨¨¨¨¨¨¨¨¨¨¨¨¨¨¨¨¨¨¨¨¨¨
ረመዳን 17 የበድር ድል ቀን ነው፡፡ ኢስላም በበደል ላይ ያነሳው የመጀመሪያው #ጦርነት የሚታሰብበት ዕለት ነው፡፡ የዘመቻውን መዋዕል ብዙዎች በተለያየ አጋጣሚ አንስተውታል፡፡ እዚያ ውስጥ መግባት አልሻም፡፡ ነገርግን ያንን ገድል የሰራውን ዋናውን ስሜት መግለፅ እፈልጋለሁ፡፡ ከበድር ድል በስተጀርባ የነበረው ቀስቃሽ ኃይል የጀነት ናፍቆት ነበር!

በጦር አውድማው ላይ የአላህ መልክተኛ (ﷺ) ሁሉም እንዲሰማቸው ድምጻቸውን ከፍ አድርገው እንዲህ አሉ፡- ‹‹ነፍሴ በእጁ በሆነው #ጌታ እምላለሁ ዛሬ ቀን በትእግስት፣ ምንዳውን ከአላህ ከጅሎ፣ ፊትለፊት ተጋፍጦ፣ ሳይሸሽ የሚዋጋቸውን ሰው #አላህ ጀነት ያስገባዋል፡፡››
:
እውነቱን ልንገራችሁ ብዙዎቻችን ጀነት ስለሚያስገቡ በርካታ ተግባራት በተደጋጋሚ እንሰማለን፡፡ ነገርግን ምን ያህላችን በዚህ ቃል ኪዳን ቀልባችን ተነክቶ ያለንን ሁሉ ለመሰዋት ተዘጋጅተናል?!
ሶሓባዎች ለጀነት የነበራቸው ናፍቆት ልዩ ነበር፡፡ ከጀነት ውጪ ልባቸውን ምንም ነገር ሊያነሳሳውና ጉልበታቸውን እና ጽናታቸውን ሊያበረታ አይችልም፡፡
ምክንያቱም ለዱንያ የተዋጋ ምናልባት አሁን ሲገደል ሁሉም ነገር ያበቃለታል፡፡ ለጀነት የተዋጋ ሰው ግን ለሞቱ ትርጉም የሰጠ ሰው ነው፡፡ እንደውም ሞት ለሱ ህይወት ነው፡፡ የሚናፍቃት #ጀነትን ለማግኘት ካገደው የዱንያ ህይወት የሚገላገልበት ምኞቱን የሚያሰምርበት እድሉ ነው፡፡ ሸሂድ ያለ ሒሳብ ጀነት ይገባል፡፡
:
ስለዚህ ከውጊያው በፊት የሶሐቦቹ ስሜት ይህ ነበር፡- ‹‹ከሞትን ጀነት እንገባለን፡፡ ስለዚህ ሞትን ናፋቂዎች ነን!››
:
ሰዎች ሞትን ይጠላሉ፤ ይፈራሉ፡፡ የጀነት ትርጉም ለገባው ደግሞ የምኞቱ ጣሪያ ሞቱ ነው፡፡ የአላህ መልክተኛ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፡- ‹‹ጀነት ውስጥ አላህ በመንገዱ ለሚታገሉ ሰዎች ያዘጋጀው አንድ ደረጃ አለ፡፡ በርሱና ከርሱ ውጪ ባለው ደረጃ መሀል ያለው ልዩነት በሰማይና በምድር መካከል ያለውን ርቀት ያክላል፡፡›› ቡኻሪ ዘግበውታል፡፡
:
ከአነስ (ረ.ዐ.) እንደተዘገበው የአላህ መልክተኛ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፡- ‹‹በጧት ወይም ከከሰዓት በኋላ በአላህ መንገድ ለትግል መውጣት ዱንያና በውስጧ ካለው ይበልጣል፡፡ በጀነት ውስጥ ደጋን [ቀስት ማስወንጨፊያ] የሚያክል ስፍራ ዱንያና በውስጧ ካለው ሁሉ ይበልጣል፡፡ ከጀነት ሴቶች አንዷ ወደ ምድር ብቅ ብትል ዱንያን በሙሉ በብርሃን ታፈካት ነበር፡፡ በሰማይና በምድር መሀል ያለውን ሁሉ በመልካም መዓዛዋ ታውደው ነበር፡፡ በጭንቅላቷ ላይ ያለው ሻሽ ዱንያና በውስጧ ካለው ሁሉ ይበልጣል፡፡››
:
በእውነተኛው ነቢይ ልሳን በሚነገረው በዚህ እውነተኛ ቃል እርግጠኛ የሆነ ሰው ይችን ሀገር መናፈቁ አይቀሬ ነው! ስለዚህ በበድር ያሸነፈው ኃይል ልክ እኛ ህይወትን እንደምንወደው ሞትን የሚወድ ኃይል ነው፡፡ ከሁለት መልካም ውጤቶች አንዱን እንደማያጣ ተማምኖ ሜዳ ላይ የተሰለፈ ሰራዊት ነው፡፡ ድል ወይም ሞት፡፡ ድል ወይም ጀነት!
:
የአላህ መልክተኛ (ﷺ) ስለ 'ገለባው' ትውልድ ተናግረዋል፡፡ የዚያን ገለባ ትውልድ ማንነትም ‹‹ድክመት›› ያለበት ትውልድ ብለው ገልጸውታል፡፡ ‹‹ድክመቱ ምንድን ነው?›› ሲባሉም፡- ‹‹ዱንያን ማፍቀርና ሞትን መጥላት!›› በማለት መልሰዋል፡፡
የጀነት ፍቅር የሙስሊሞች የድል ቁልፍ ነው፡፡ ጀነትን ሲናፍቁ ድልም ጀነትም ያገኛሉ፡፡ የጀነት ናፍቆት ከቀልባቸው ሲጠፋ ድልንም ሆነ ጀነትን ያጣሉ፡፡
:
የድል መጀመሪያው ፍርሀትን ድል መንሳት ነው፡፡ ስለዚህ ሞትን የሚመኝ፣ ሞትን ፈልጎ የወጣ፣ ለሞት የተዘጋጀ፣ ላይመለስ ኑዛዜውን ጽፎ ከቤቱ የወጣ፣ እንደውም አለመሞትን የሚፈራ ሰው ምንን ሊፈራ ይችላል?! እንዲያፈገፍግ የሚያደርገው ኃይልስ ይኖራል ወይ?!
:
ጉዳዩ የእምነትና የፍላጎት ነው፡፡ የኒያ ጉዳይ ነው፡፡ የህልም ጉዳይ ነው፡፡ የናፍቆት ጉዳይ ነው፡፡
አንተስ ጀነትን ትፈልጋለህ?! ጀነትን ትናፍቃለህ?!…
ጀነትን የምር ከፈለግከው በሰላሙ ጊዜም አታጣውም፡፡ የአላህ መልክተኛ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፡- ‹‹ሸሂድ መሆንን በእውነት አላህን የለመነ ሰው በፍራሹ ላይ እንዳለ ቢሞትም አላህ የሸሂዶችን ደረጃ ያደርሰዋል፡፡››
ጉዳዩ የኒያ ነው! ከአላህ ጋር የተጋባኸው እውነተኛ ቃልኪዳን!
:
ወደ ኋላ እንመለስ!
የጀነት ፍቅር #በድር ላይ ምን ሰራ?!
አንድ ክስተት ብቻ ላንሳ።
ዑመይር ኢብኑል-ሑማም ከአላህ መልክተኛ [ﷺ] አጠገብ ነበር፡፡ የአላህ መልክተኛ (ﷺ) ‹‹ስፋቷ ሰማያትና ምድርን ለምታህለዋ ጀነት ተነሱ!›› አሉ፡፡
ይህ ቃል በቁርኣን ውስጥ ያለ ቃል ነው፡፡ ደጋግመን ቀርተነዋል፡፡ ደጋግመን ሰምተነዋል፡፡ ነገርግን ስንት ጊዜ ሰርተንበታል?! ስንት ጊዜ ጀነትን ናፍቀንበታል?! ምንም ወይም ጥቂት!!
ዘር መሬት መርጦ እንደሚያፈራው መልእክቱም ልብን መርጦ ያብባል፡፡ ዑመይር ኢብኑል-ሑማም ይህንን ቃል ሰማ፡፡ በልቡ ነው የሰማው፡፡ ገረመው፡፡ ‹‹ስፋቷ ሰማያትና ምድርን የሚያህል!›› አለ፡፡
የኮንዶሚኒየም ቤት ባለቤት መሆን ምን ያህል እንደሚያለፋ ሁላችንም እናውቃለን፡፡ ዘልዓለማችንን ደክመንም ላይሳካ ከመቻሉ ጋር ማለት ነው!
ጀነት ግን የአላህ ቃል ነው፡፡ አምኖ ኒያውንም ለአላህ አጥርቶ ሳይሸሽ የታገለ ሰው ጀነት ይገባል!
ዑመይር በአግራሞት ጠየቀ፡- ‹‹ስፋቷ ሰማያትና ምድርን ያህላል!?››
‹‹አዎን!›› አሉት፤ በአጭሩ፡፡ ማብራሪያና ዝርዝር ውስጥ ሳይገቡ፡፡
ዑመይርስ? እሱም በእርግጠኝነት ንግግሩን ተቀብሏል፡፡ አልተከራከረም፤ አላንገራገረም፤ ማብራሪያ አልጠየቀም!
‹‹እሰይ እሰይ!›› አለ፤ በመደነቅ፡፡
‹‹እሰይ! እሰይ! ያልከው ለምንድን ነው? በንግግሬ ተጠራጥረህ ነው?›› አሉት፤ የአላህ መልክተኛ ﷺ፡፡
ዑመይር በፍጥነት እንዲህ አለ፡- ‹‹የአላህ መልክተኛ ሆይ በፍጹም! እሰይ ያልኩት የጀነት ሰው መሆንን ተመኝቼ ነው!›› አለ፡፡
እርሳቸውም ‹‹አንተ የጀነት ሰው ነህ!›› አሉት፡፡
ዑመይር የጀነት ሰው ነው! በዱንያ ውስጥ ህይወቱ በስጋው ላይ እያለም ይህንን ያውቃል! ጀነት ከመግባት ያገደው ደግሞ አለመሞት ነው!
ሱብሐነላህ!
ከዚህ በኋላ ግን ለአፍታም ቢሆን በምድር ላይ በህይወት መቆየት አልፈለገም፡፡ በውጊያው ላይ ብርታት ይሆነው ዘንድ እየተመገባቸው የነበሩ ጥቂት የተምር ፍሬዎች በእጁ ላይ ነበሩ፡፡ ለአፍታ አሰበ፡፡
ለምንድን ነው ይህንን ተምር በእጄ የያዝኩት!?
የጀነት ፍሬዎች የት ሄደው ነው ይህንን የምመገበው!?
የጀነት አዕዋፋት፤ የጀነት መጠጥ፤ የአላህ መልክተኛ ሐውድ የት ሄዶ!?…
…እያለ ማሰብ ጀመረ፡፡
በእጁ የነበሩትን ተምሮች ጣለና በወርቅ ቀለም መመዝገብ የሚገባው አስደናቂ ቃሉን ተናገረ፡— ‹‹እነዚህ የተምር ፍሬዎችን እስጨርስ በህይወት ከቆየሁ ረዥም ሕይወት ነው!›› አለ፡፡
ጀነትን ሲናፍቅ የተምር ፍሬዎችን ለመብላት መቆየት እንኳን ረዘመበት፡፡
ለህይወቱ ሳይሳሳ ጠላት መሀል ዘሎ ገባ!
1.2K views12:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-08 06:08:54 አንተ ሩሕ ሆይ!…
ከፅልመት ጋር መወዳጀት፣ ከድፍርስ ጋር መጎራበት አልሰለቸህም ወይ?!
ከተሰቀልክበት ከፍታ መውረድ፣ በአሽከሩ ስጋህ መጠለፍ፣ በአፈር ሰራሽ አካል መጠርነፍ አልበቃህም ወይ?!
ንጉስ በሆንክበት ግዛት ውስጥ ሎሌ መሆን፣ ዋና በሆንክበት መድረክ ልጥፍ መሆን፣ እንቁ በሆንክበት ሜዳ ኮረት መሆን አልሰለቸህም!?

ለመሆኑ… ስጋ ሳትለብስ በፊት አልነበርክም እንዴ?
በተቀደሰው ስፍራ፣ በጌታህ የክብር ማሳ፣ ከታላላቆች ጋር፣ በኡንስ ባህር ውስጥ ሰርገህ ስትዋኝ አልነበር?!
ከሪዷ ኩሬ እየጠለቅክ፣ የሸውቅን ፅዋ እየተጎነጨህ፣ በተውሒድ ድምቀት ፈክተህ፣ የቁርብን ነፋስ እያሸተትክ፣ በመዕሪፋ ከተማ እንዳሻህ ትንሸራሸር አልነበር?!
ታዲያ ያኔ መች ስጋ ነበር?!… እርሱ የትናንት ነው! ቀድመህ የነበርከው አንተ ነህ!…

ዘንግተህ እንጂ ስጋ መታሰሪያህ ነበር። እንደ ወፍ ስትበር ኖረህ በገደብ እንድትቆይ የተከረቸምክበት መኖሪያህ። እርግጥ ነው መታገትህ ውስጥ ጥበብ አለ። በስጋህ ላይ ያለውን ዓቅም ተጠቅመህ የዓለመል‐ኸልቅን ትንግርት መመልከት ትችላለህ! በነጠላ እያለህ የማይታይህ የነበረውን የኻሊቁን ዓጃኢብ ስጋን ተፈናጠህ፣ በህዋስ መነፅር ታያለህ!

አንተ ግን ምን አደረግክ?!…
ዝቅ አልክ። ባርያ ሆኖ እንዲያገለግልህ በታዘዘው ስጋህ ተገዛህ። በስሜት ጭቃ አደፍክ። ፈረስህ እንዲሆን በተቸርከው አካልህ ተጋለብክ! መብረር ስትችል ዘቀጥክ!
የመጣህበትን ሀገር ዘነጋህ። የቀደመ ታሪክህን ረሳህ። አንተ የጌታ ምስጢር፣ የመለኮት ልዩ ስሪት፣ የአስደማሚው ቅድስናው ታዛቢ፣ የ"አለስቱ ቢረቢኩም" ምስክር ነህ!
አንተ ሩሕ ሆይ! እስኪ ንገረኝ። ወደ መጣህበት ሀገር፣ ወደ ቀዬህ የምትመለሰው መቼ ነው?! በእንግድነት መኖር አልበቃህም?!
1.2K viewsedited  03:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-06 14:48:03
ይህ ምስል ከላይ የተብራራውን አሰጋገድ ይገልፃል። በአማርኛ አሳምሮ ሰርቶ የሚሰጠን የግራፊክስ ባለሙያ ካለ ደስ ይለናል!
742 views11:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ