Get Mystery Box with random crypto!

Tofik Bahiru

የቴሌግራም ቻናል አርማ fiqshafiyamh — Tofik Bahiru T
የቴሌግራም ቻናል አርማ fiqshafiyamh — Tofik Bahiru
የሰርጥ አድራሻ: @fiqshafiyamh
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 6.13K

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2023-04-17 01:19:26 መደበኛ ሆቴሎች ላይ የምትበሉና የምታበሉ፣ በየቁርጥ ቤቱና ክትፎ ቤቱ የምትዞሩና የምታዞሩ፣ የምታፈጥሩ እና የምታስፈጥሩ ሰዎች ግን እንዴት እና በምን መልኩ ሐላል መሆኑን አረጋግጣችሁ ይሆን?!…
በአራቱም መዝሀብ ስምምነት ያለበት የፊቅህ ቃዒዳ እንዲህ ይላል: ‐
"الأصلُ في الذَّبائِحِ التَّحريمُ"
"የእርድ ብይን መነሻ ጭብጥ ሐራም መሆን ነው።"
ሥጋ ሁሉ ሐራም ነው ብለን እንነሳለን። ስለዚህ ሐላል መሆኑን ሳታረጋግጥ መብላት አትችልም!
እና እንዴት አረጋግጣችሁ ነው እየበላችሁ እና እያበላችሁ ያላችሁት?!
ጥያቄው የኢስላማዊ ፕሮግራም አዘጋጆችንም ይጨምራል!
http://t.me/fiqshafiyamh
725 views22:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-16 22:24:52 ዘካተል‐ፊጥርን በውክልና
================
ዘካቱል‐ፊጥር ላይ ገዝቶ የማከፋፈል ሥራውን ለሌላ ሰው ማወከል ይፈቀዳል። በሻፊዒያ መዝሀብ ውስጥ ኺላፍ የለም።
ኢማም ነወዊይ "መጅሙዕ" ላይ እንዲህ ይላሉ: ‐
«ዘካ ዒባዳ ከመሆኑ ጋር ውክልና የተፈቀደበት ምክንያት የሰው እዳን ከመክፈል ጋር የሚያመሳስለው ነገር በመኖሩ ነው። በተጨማሪም የዘካ ገንዘቡ ከዘካ አውጪው በመራቁ እና መሰል ምክንያቶች በውክልና መስራት እጅግ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱም ነው።»

የሻፊዒይ መዝሀብ ልሂቅ የሆኑት ሸይኽ ሰዒድ አል‐ጃቢሪይ እንዲህ ይላሉ: ‐ «ሰውየው በራሱ በቀጥታ ዘካውን መስጠት የተሻለ ነው። የዘካ በረከቱ ቤት ውስጥ ያለውን ሁሉ ያካልል ዘንድ ቤት ውስጥ ሰፍሮ መስጠቱ መልካም ነው። በዚህ ቤተሰቦቹ ስለ ዘካቱል ፊጥር ይማሩበታል። መጠኑን ለይተው ያውቃሉ።
በውክልና በመስጠት ግን በጊዜ ሂደት ከበርካታ ሰዎች አእምሮ ውስጥ የዘካ ግንዛቤ ሊጠፋ ይችላል። ዝርዝር ሑኔታዎቹን የማያውቅ ትውልድ ሊፈጠርም ይችላል።»

ኢማም ነወዊይ እንዲህ ይላሉ:‐ «ታላላቆቹ የሻፊዒይ ባልደረቦች እንዲህ ብለዋል: ‐ «በገዛ ራሱ ዘካቱል‐ፊጥሩን ማከፋፈል በውክልና ከማከፋፈል ይበልጣል። ይህ ልዩነት የሌለበት ጉዳይ ነው። ምክንያቱም ዘካው በትክክል መከፋፈሉን ማረጋገጥ የሚችልበት ሁኔታ ይህ ነው። ወኪል ግን ሊከዳ (ሊያታልል) ይችላል የሚል ስጋት አለበት። በዚያ ላይ ከዘካ አውጪው ጫንቃ ላይ ዘካው አይነሳለትም። ምክንያቱም የወኪሉ እጅ እንደ ዘካ አውጪው እጅ የሚቆጠር ነው። ለድኾቹ ገንዘቡ እስካልደረሰ ድረስ የባለቤቱ ጫንቃም ከዘካ ግዳጅ አይፀዳም።»

ስለዚህ በዚህ መሰረት አንድ ሰው ገንዘቡን ለዘካ አሰባሳቢ ድርጅት መስጠቱ ብቻውን ጫንቃውን አያፀዳለትም። ወኪል ድርጅቱ ለሚገባቸው ሰዎች ማድረሱ የግድ ነው። በመሀል ገንዘቡን በግፍ ከበላው ወይም መሰጠት ካለበት ወቅት ካዘገየው፣ ለማይገባው ሰው ከሰጠው [ወዘተ] ወኪሉን በወንጀል ሊያስጠይቀው ከመቻሉ ጋር ዘካ አውጪውም ይህንን እስካወቀ ድረስ ሊያስጠይቀው ይችላል። በዚያ ላይ ለተገቢዎቹ ሰዎች እስካልደረሰ ድረስ የዘካ አውጪው ጫንቃም በምንም መልኩ ከተጠያቂነት አይድንም።

በመሆኑም ዘካቱል‐ፊጥራችሁን በተለያዩ አይነት ውክልናዎች የምታከፋፍሉ ሰዎች ዘካችሁ ከዒድ ሶላት በፊት ለተገቢዎቹ ሰዎች መድረሱን አጣሩ! በወኪላችሁ እጅ ላይ እንዳይከርምና ቀኑ እንዳያልፍባችሁ ተጠንቀቁ!
አላሁ አዕለም!
http://t.me/fiqshafiyamh
870 viewsedited  19:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-16 16:36:13 «አላህ ሆይ!
ኃጢኣታችንን እንደ ወደድካቸው ሰዎች ኃጢኣት አድርግልን።
መልካም ሥራችንን እንደጠላሃቸው ሰዎች መልካም ሥራ አታድርግብን።
ካንተ በኩል ጥላቻ ኖሮ መልካም ሥራ አይጠቅምም። ካንተ በኩል ፍቅር እያለ ኃጢኣት አይጎዳም!»
ሰይዲ አቡል‐ሐሰን አሽ‐ሻዚሊይ [ቀደሰላሁ ሲረሁል‐ከሪም]
:
"ኃጢኣታችንን እንደ ወደድካቸው…" ማለት: ‐ እንደ በድር ሰዎች "የፈለጋችሁን ሥሩ። በእርግጥም ምሬላችኋለሁ!" እንዳልካቸው አድርግልን ማለት ነው።
"መልካም ሥራችንን እንደጠላሃቸው…" ማለት: ‐ በቁርኣኑ እንዲህ እንደተባለው ነው: ‐ «ከሥራም ወደ ሠሩት እናስባለን፡፡ የተበተነ ትቢያም እናደርገዋለን፡፡»
ዱዓችንን እና ሌላውንም ሥራችንን ይቀበለን!
998 views13:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-16 14:05:12 Tofik Bahiru pinned an audio file
11:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-16 14:02:58 «አዩሃል‐ወለድ»፣ ከገፅ ከ75‐79 (የመጨረሻ ክፍል)
ኢማም፣ ሸይኹል‐ኢስላም፣ ሑጀቱል‐ኢስላም፣ በረከቱል‐አናም፣ አቡ ሓሚድ አል‐ገዛሊይ
ክፍል 11
1.0K viewsedited  11:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-16 04:41:03 ኢላሂ!
የራቁህን ወደ እዝነትህ እየጠራህ፤
ያመፁህን ወደ ፍቅርህ እየጋበዝክ፤
በረመዳን ሌሊት፣ በዐሽሩል‐አኺሩ፣ ውዷን ሌሊት ፍለጋ የቆሙ ወዳጆችህን ታሳፍራለህን?!… ሓሻከ ረቢ! ሓሻክ!
:
የአላህ ባሮች ሆይ! እርጉ፤ ጌታችሁ ረሒም እና ወዱድ ነው!
1.1K views01:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-15 17:02:22 የሙሒብ እውነታ: ‐
«ለይለቱል‐ቀድሬ ወዳጄ!…
ለቀልቤ ዐይን የሙሐመድ ፊት የበራለት ጊዜ ነው!»
#የረመዳን 25ኛው ለሊት!
1.3K views14:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-15 05:58:54 ኢላሂ!
በትእግስትህ ተሞኝቼ ነው፤ ማረኝ።
በቸርነትህ ተዘናግቼ ነው፤ እዘንልኝ።
በነፍሴ ተሸንፌ ነው፤ ይቅር በለኝ።
496 viewsedited  02:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-14 22:16:36 Tofik Bahiru pinned an audio file
19:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-14 20:05:35 «አዩሃል‐ወለድ»፣ ከገፅ 72‐75
ኢማም፣ ሸይኹል‐ኢስላም፣ ሑጀቱል‐ኢስላም፣ በረከቱል‐አናም፣ አቡ ሓሚድ አል‐ገዛሊይ
ክፍል 10
816 views17:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ