Get Mystery Box with random crypto!

Tofik Bahiru

የቴሌግራም ቻናል አርማ fiqshafiyamh — Tofik Bahiru T
የቴሌግራም ቻናል አርማ fiqshafiyamh — Tofik Bahiru
የሰርጥ አድራሻ: @fiqshafiyamh
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 6.13K

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2023-04-14 19:42:41 «ኢላሂ!
በዲንህ ላይ መፅናት የሚሻን ቀልብ አግዝ!»
841 views16:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-14 16:20:13 :
ቡኻሪ እንደዘገቡት "ኢብኑ ዑመር [ረዐ] ሶደቀቱል‐ፊጥርን ይሰጡ ነበር። ከዒዱ እለት አንድ ወይም ሁለት ቀን አስቀድመውም ያወጡ ነበር።"
የአላህ መልክተኛ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል: ‐ "ከሶላት በፊት ከሰጠ ዘካው ተቀባይነት ያለው ነው። ከሶላት በኋላ ከሰጠ ደግሞ እንደማንኛውም ምፅዋት የሚቆጠር ነው።" አቡዳዉድ ዘግበውታል።
:
የእህል ዓይነቶች
==========
ዘካቱል‐ፊጥር የሚወጣባቸው የእህል ዓይነቶች ተዘርዝረው አያልቁም። በአጭሩ በሀገሩ ላይ አብዝሀኛው ሰው የሚመገበውን የምግብ [የእህል] ዓይነት ማውጣት ግዴታ ነው። ኢብኑ ዑመር [ረዐ] እንዲህ ይላሉ: ‐ "የአላህ መልክተኛ [ﷺ] የረመዳን ፍቺ ዘካን ግዴታ አድርገው ደንግገዋል። መጠኑም አንድ ቁና ተምር ወይም አንድ ቁና ገብስ ነው።" ያን ጊዜ ገብስ ይመገቡ ስለነበር ነው።
:
አቡ ሰዒድ አል‐ኸኹድሪይ [ረዐ] እንዲህ ብለዋል: ‐ "በነቢዩ [ﷺ] ዘመን በዒዱል‐ፊጥር ቀን አንድ ቁና ምግብ ዘካ እናወጣ ነበር። በዚያን ጊዜ ምግባችን ገብስ፣ ዘቢብ፣ ደረቅ ወተት [አይብ] እና ተምር ነበር።" ቡኻሪ ዘግበውታል።
:
የእህል ዋጋን መስጠት
==============
የዘካቱል‐ፊጥር መጠን በሀገሩ እንደቀለብ ከሚበሉ የእህል ዓይነቶች አንድ ቁና ነው። ይኸውም ለአንድ ሰው ሁለት ኪሎ ከአርባ ግራም (2.4 ኪ.ግ.) ይሆናል። እህሉን መስጠት ድንጋጌው የተዘገበበት ተቀዳሚ አፈፃፀም ነው። ሻፊዒዮቹን ጨምሮ በአብዝሃኞቹ ዓሊሞች መዝሀብ መሰረት በዋጋው መስጠት አይፈቀድም።
:
በእርግጥ ዋጋውን መስጠት እንደሚፈቀድ የሚያምኑ አንዳንድ ዐሊሞች አሉ። ኢማም አቡ ሐኒፋ፣ የአቡ ዩሱፍ፣ የሐሰኑል‐በስሪይ እና ሰውሪይ ከነዚህኞቹ ናቸው። የዘካ ዓላማው የድኾችን ችግር መቅረፍ እስከሆነ ድረስ ነገሩ ሰፊ ተደርጎ መታየት አለበት።
:
ዶ/ር ሙሐመድ አዝ‐ዙሐይሊ "አል‐ሙዕተመድ" በተሰኘው መፅሀፋቸው ላይ እንዲህ ብለዋል: ‐ «በዚህ ዘመን የአቡ ሐኒፋን ሃሳብ ከመያዝ የሚያግድ ነገር የለም። ምክንያቱም በዚህ ዘመን ለድኾች የሚጠቅመው ይህ ስለሆነ ነው። ዘካ የተደነገገበትን ድኾችን የማብቃቃት ትልምንም ያሳካል።»
:
"አል‐ፊቅሁል‐ሚንሀጂይ ዐላ መዝሀቢሽ‐ሻፊዒይ" በተሰኘው የሻፊዒዮቹ ድንቅ መፅሀፍ ላይም እንዲህ የሚል አለ: ‐ «በዚህ ጉዳይ ላይ የኢማም አቡሐኒፋን መዝሀብ መከተል ችግር የለውም። ስለዚህ ዋጋውን መስጠት ይፈቀዳል። በዚህ ዘመን ዋጋውን መስጠት እህሉን ከመስጠት የበለጠ ለድኻው ይጠቅማል። ከዘካው ድንጋጌ የሚጠበቀውን ግብም ያሳካል።»
:
ዘካቱል‐ፊጥር ለማን ይሰጣል?
===================
ዘካቱል‐ፊጥርን ዘካ ለሚሰጣቸው ስምንቱ ቡድኖች ማከፋፈል ይፈቀዳል። ነገርግን ለድሆችና ምስኪኖች ማከፋፈል ተመራጭ ነው። ሰውየው ራሱ ሊቀልባቸውና ወጪያቸውን መሸፈን ግዴታ ለሚሆንበት ቤተሰቦቹ መስጠት አይፈቀድለትም። ነገርግን ከዚህ ውጪ ለሆኑ ዘመዶቹ መስጠት ሁለት ምንዳ ያስገኝለታል። አንድም ምፅዋት ነው። በሌላ በኩል ደግሞ ዝምድናን መቀጠል ነው።
:
አላህ ዒባዳችንን ይቀበለን። ረመዳኑንም አመት አመት ይድገመን!
http://t.me/fiqshafiyamh
944 views13:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-14 16:20:13 ዘካቱል‐ፊጥር
=========
ለጾም ፍቺ የሚሰጥ ዘካ ስለሆነ ዘካቱል‐ፊጥር ይባላል። እንደሌሎች ዘካዎች በሀብት ላይ ሳይሆን በጾመኛ አካል ላይ የሚያርፍ ዘካ በመሆኑ ደግሞ ዘካቱል‐በደን ይባላል።
:
ከሂጅራ በኋላ በሁለተኛው ዓመት ላይ የተደነገገ የዘካ ዓይነት ነው። የረመዳን ጾም በተደነገገበት ዓመት ማለት ነው። ዘካቱል‐ፊጥር ግዴታ መሆኑ በበርካታ ሐዲሶች ተረጋግጧል።
ከአቡ ሰዒድ አል‐ኹድሪይ [ረዐ] እንደተዘገበው: ‐ «የአላህ መልክተኛ [ﷺ] በመካከላችን እያሉ ዘካቱል‐ፊጥርን እንሰጥ ነበር።» ብለዋል።» ሙስሊም ዘግበውታል።
ከኢብኑ ዐባስ [ረዐ] እንደተዘገበው "የአላህ መልክተኛ [ﷺ] ዘካቱል‐ፊጥርን ግዴታ አድርገው ደንግገውታል።" አቡዳዉድ እና ሌሎችም ዘግበውታል።
:
የድንጋጌ ጥበብ
==========
ዘካቱል‐ፊጥር የተደነገገው በጾም ላይ የተከሰቱ ጉድለቶችን ለመጠገን እና በዒድ ቀን ድሆችን ከልመና ለመጠበቅ ነው። የአላህ መልክተኛ [ﷺ] ዘካቱል‐ፊጥር የተደነገገበትን ምክንያት ሲገልፁ እንዲህ ብለዋል: ‐ "ለጾመኛ ንፅህና ለምስኪን ምግብ እንዲሆን የተደነገገ ነው።" ኢብኑ ዐባስ (ረዐ) ዘግበውታል።
በሌላ ሐዲስ ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል: ‐ "[ድኾቹን] በዚያን እለት ለልመና እንዳይዞሩ አብቃቋቸው።"
ዘካቱል‐ፊጥር በሶላት ውስጥ ለሚከሰቱ አንዳንድ ስህተቶች እንደተደነገገው ሰጅደቱ‐ሰህዉ (የመርሳት ሱጁድ) የሚታይ ነው። ሰጅደቱ ሰህው ሶላትን እንደሚጠግነው ዘካቱል‐ፊጥርም ጾምን ይጠግናል።
ዘካቱል‐ፊጥር በማህበረሰቡ መሀል የመተባበርና የመረዳዳት መንፈስን ያሳድጋል። መተዛዘን እንዲሰፍን፣ የሀዘን እና የደስታ ስሜትን የሚጋራ ህዝብ ለመፍጠርና የማህበረሰብ ትስስርን ለማጥበቅ ያግዛል።
:
ግዴታ የሚሆነው በማን ላይ ነው?
=====================
ዘካቱል‐ፊጥር ማውጣት የእያንዳንዱ ሙስሊም ግዴታ ነው። ወንድን ከሴት፣ ህፃንን ከዐዋቂ፣ እብድን ከጤነኛ አይለይም። ዐብዱላህ ኢብኑ ዑመር [ረዐ] እንደዘገቡት: ‐ "የአላህ መልክተኛ [ﷺ] የረመዳን መግደፊያ ዘካን ግዴታ አድርገዋል። መጠኑ አንድ ቁና ተምር ወይም አንድ ቁና ገብስ ነው። ባሪያም ሆነ ጨዋ፣ ወንድም ሆነ ሴት፣ ህፃንም ሆነ ዐዋቂ በሙስሊሞች ላይ ሁሉ ግዴታ ተደርጓል።" ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።
ኢብኑል‐ሙንዚር እንዲህ ብለዋል: ‐ "ዘካቱል‐ፊጥር ግዴታ መሆኑ ላይ የምናውቃቸው ዐሊሞች በሙሉ ተስማምተዋል።"
:
የግዳጅ መስፈርቶች
============
ዘካቱል‐ፊጥር ግዴታ ይሆን ዘንድ መሟላት ያለባቸው መስፈርቶች ተከታዮቹ ናቸው: ‐
❶ ሙስሊም መሆን: ‐ ሙስሊም ያልሆነ ሰው ዘካቱል‐ፊጥር ቢያወጣ ተቀባይነት የለውም። አላህ እንዲህ ብሏል: ‐ «ልግስናዎቻቸውን ከነሱ ተቀባይ የሚያገኙ ከመኾን እነሱ በአላህና በመልክተኛው የካዱ… መኾናቸው እንጂ ሌላ አልከለከላቸውም፡፡»
❷ ችሎታ: ‐ በዒድ ሌሊትና በቀኑ ላይ ከራሱና ከቤተሰቡ ቀለብ እና መሰረታዊ ወጪ የተረፈ ገንዘብ መኖር።
:
ሰውየው ከራሱ በተጨማሪ ወጪያቸውን ሸፍኖ ማኖር ግዴታ የሚሆንበትን ሰዎች ዘካ መስጠትም ግዴታ አለበት። የህፃናት ልጆቹን፣ የሚስቱን እና [በርሱ ስር የሚተዳደሩ] ወላጆቹን ማለት ነው።
:
ኢብኑ ዑመር [ረዐ] በዘገቡት ሐዲሰ የአላህ ነቢይ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል: ‐ «ለምትቀልቧቸው ሰዎችም ዘካቱል‐ፊጥር አውጡላቸው።» ዳረቁጥኒ ዘግበውታል።
:
አንዲት ሴት ባሏ ዐቅም ከሌለው ዘካቱል‐ፊጥር ማውጣት በርሷ ላይ ግዴታ በመሆኑ ላይ የዐሊሞች ልዩነት አለ። ዘካዋን በራሷ መክፈል ግዴታ ይሆንባታል የሚለው ሃሳብ ግን የአብዝሃኞቹ ዐሊሞች ነው።
ሰውየው በዕዳ የተያዘ ሰው መሆኑ ዘካቱል‐ፊጥርን ለመተው ምክንያት አይሆንም።
:
ግዴታ የሚሆንበት ጊዜ
==============
ዘካው ግዴታ የሚሆንበት ጊዜ የሚጀምረው በዒድ ዋዜማ ፀሀይ ከመጥለቋ አንስቶ ነው። ምክንያቱም ዘካቱል‐ፊጥር የተደነገገበት ምክንያት ጾም ነበር። እርሱ ደግሞ ፀሀይ በመጥለቋ ምክንያት አብቅቷል። ይህ የኢማም ሻፊዒይና የኢማም አሕመድ ሃሳብ ነው።
በዚህ መሰረት የዒድ ሌሊት ፀሀይ በምትጠልቅበት ሰዓት ዘካቱል‐ፊጥር ግዴታ ከሚሆንባቸው ሰዎች መካከል ሆኖ የተገኘ ዘካውን የመስጠት ግዴታ ይኖርበታል። ፀሀይ ከጠለቀች በኋላ ወዲያው ቢሞትም ግዴታው እንዳለ ነው። በተቃራኒው ፀሀይ ከመጥለቋ ከደቂቃዎች በፊት የሞተ ሰው ዘካ የለበትም።
:
አቡ ሐኒፋ እና ማሊክ በበኩላቸው ግዳጁ የሚጀምረው ንጋት ከቀደደ አንስቶ ነው ባይ ናቸው። ምክንያቱም ዘካቱል‐ፊጥር የተደነገገበት ምክንያት ዒዱ ነው። ስለዚህ እንደማናቸውም የዒድ ቀን ድንጋጌዎች፣ እንደ ኡድሒያ፣ እንደ ጁሙዐ ሶላት ድንጋጌዎች… ከእለቱ ቀድሞ ግዴታ ይሆንም።…
:
የሚሰጥበት ጊዜ
===========
ዘካውን የዒድ ሶላት ከመሰገዱ አስቀድሞ ማውጣት ይወደዳል። ሻፊዒዮች ዘንድ በዒዱ ቀን ፀሀይ እስከምትጠልቅ ድረስ መስጠት ግን ይፈቀዳል። አብዝሀኞቹ ዐሊሞች ደግሞ ከሶላት በኋላ ማውጣት ይጠላል ብለዋል። አንዳንድ ዐሊሞች ከሶላት በኋላ አዘግይቶ መስጠት ሐራም ነው ይላሉ። እለቱን ማሳለፍ ግን ያለ ልዩነት ሐራም ነው። ነገርግን ቀኑ ቢያልፍም ዘካው ከሰውየው ጫንቃ ላይ አይነሳም። ጫንቃውን ከድሆች ሐቅ ለማፅዳት መቼም ቢሆን ዘካውን መክፈል አለበት። ከዚያም ማዘግየቱ የአላህ ሐቅን መጣስ በመሆኑ አላህን ምህረት መለመን አለበት።
:
አቡ ሰዒድ አል‐ኹድሪ [ረዐ] እንዲህ ብለዋል: ‐ "በአላህ መልክተኛ [ﷺ] ዘመን በዒዱል‐ፊጥር ቀን አንድ ቁና እህል እንሰጥ ነበር።"
ከኢብኑ ዑመር [ረዐ] እንደተዘገበው የአላህ መልክተኛ [ﷺ]: ‐ "ዘካቱል‐ፊጥር ሰዎች ለሶላት ከመውጣታቸው አስቀድሞ እንዲሰጥ አዘዋል።"
የዘካው ዓላማ ድሆች ከሀብታም ጎረቤቶቻቸው ጋር የዒዱን ቀን በደስታ እንዲያሳልፉ ከመሆኑ አንፃር በጠዋት ከሶላት በፊት መስጠቱ ተገቢ ነው።
:
ዘካውን ሳይሰጥ የዘገየው በአሳማኝ ምክንያት ከሆነ ግን ችግር የለውም። ለምሳሌ: ‐ ሰውየው የሚሰጠው ነገር በሌላ ቦታ ላይ እያለ የዘካው ጊዜ ከደረሰበት፣ ዘካ የሚቀበል ተገቢ አካል ሳያገኝ በመቅረቱ ካዘገየው፣ የዒዱ አዋጅ በድንገት ተነግሮ ከሶላት በፊት ዘካ ለማውጣት የሚመች ጊዜ በማጣቱ፣ ሌላ ሰው ዘካውን ያወጣልኛል ብሎ ተዘናግቶ ባለበት ሰውየው ከረሳው ወ.ዘ.ተ. ዘካውን ያለ ምንም ችግር ከዒድ በኋላም መስጠት ይችላል። ምክንያቱም በነዚህ ሁኔታዎች በሙሉ ሰውየው ምክንያታዊ ነው።
:
ማስቀደም
======
ሻፊዒዮቹ ዘንድ ከረመዳን አንደኛው ቀን ጀምሮ ግዴታ ከመሆኑ አስቀድሞ ዘካውን መስጠት ይፈቀዳል። ምክንያቱም ዘካው በሁለት ምክንያቶች የተደነገገ ዘካ ነው። አንደኛው ጾም ሲሆን ሌለኛው ፊጥር ነው። ረመዳን አንድ ሲል አንዱ ምክንያት ተገኝቷል። ስለዚህ ዘካውን ከረመዳን አንድ ጀምሮ መስጠት ይቻላል።
ኢማም ማሊክ እና አሕመድ ዘንድ ደግሞ ከሁለት ቀን አስቀድሞ መስጠት ይቻላል። አንዳንዶቹ ሦስት ቀን ማስቀደም ይፈቀዳል ይላሉ። ሐንበሊዮች በከፊሉ ከረመዳን አጋማሽ ጀምሮ አስቀድሞ መስጠት ይቻላል ይላሉ። ነገሩ ሰፊ ነው። የፈለጉትን ዐሊም ሀሳብ ተንተርሶ መፈፀም ይቻላል።
824 views13:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-14 12:22:14
ወንድሜዋ! ሞኝ አትሁን!
አለኝ ያልከው ሁሉ አይጠቅምህም!
እዚህ ያኖርከው አንጋፋ ፍቅር ሲቀር!
እዚህ ያለው… "ወንድሞቼ ናፈቁኝ!" በሚል ተቆርቁሮ "ሰውየው ከወደደው ጋር ነው!" ብሎ ያበቃ አትራፊ ፍቅር ነው!
1.0K views09:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-14 02:47:57 «አዩሃል‐ወለድ»፣ ከገፅ 68‐72
ኢማም፣ ሸይኹል‐ኢስላም፣ ሑጀቱል‐ኢስላም፣ በረከቱል‐አናም፣ አቡ ሓሚድ አል‐ገዛሊይ
ክፍል 9
1.1K views23:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 07:29:39 Tofik Bahiru pinned an audio file
04:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 00:52:40 «አዩሃል‐ወለድ»፣ ከገፅ 64‐68
ኢማም፣ ሸይኹል‐ኢስላም፣ ሑጀቱል‐ኢስላም፣ በረከቱል‐አናም፣ አቡ ሓሚድ አል‐ገዛሊይ
ክፍል 8
610 views21:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-12 03:50:11 አንተ የእሳት ጌታ፤
እሳትህን ቻይ አይደለንም፤
ኃያሉ ቁጣህን አንችልም፤
አላሂ! ጫንቃችንን ከእሳት ነፃ አድርግልን!
اللهم أعتق رقابنا من النار أجمعين!
1.1K viewsedited  00:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-12 01:28:25 «አዩሃል‐ወለድ»፣ ከገፅ 61‐64
ኢማም፣ ሸይኹል‐ኢስላም፣ ሑጀቱል‐ኢስላም፣ በረከቱል‐አናም፣ አቡ ሓሚድ አል‐ገዛሊይ
ክፍል 7
1.1K views22:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 23:42:27 ኢላሂ!
ከኃጢኣቴ በኋላ እድሜዬ ያልተገታው በትእግስትህ ሰበብ ነው! የወንጀሌ ፍርድ የዘገየው ቻይ በመሆንህ ምክንያት ነው!
ኢላሂ ወ መውላዬ!
ያጠፋሁትን ለመካስ የሚበቃ እድሜ እንኳን ካልቀረኝ ጥፋቴን አምኜ መለፈፌን ቁጠርልኝ!
1.1K views20:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ