Get Mystery Box with random crypto!

Tofik Bahiru

የቴሌግራም ቻናል አርማ fiqshafiyamh — Tofik Bahiru T
የቴሌግራም ቻናል አርማ fiqshafiyamh — Tofik Bahiru
የሰርጥ አድራሻ: @fiqshafiyamh
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 6.13K

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 10

2023-03-30 23:19:43 ኢላሂ!
የተበደለን ሁሉ እርዳ።
የተጨነቀን ሁሉ ፈርጅ።
የተራበን ሁሉ አብላ።
የታመመን ሁሉ አሽር።
አሚን!
https://t.me/fiqshafiyamh
972 views20:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-30 14:08:28 ኢማም ኢብኑል‐ጀውዚይ እንዲህ ብለዋል: ‐
«እድሜ ተጓዥ፣ እንደውም በራሪ ነፋስ ነው!
ሳይቸኮልብህ ቸኩል!
ቀን ያልወጣለት ስንት ሌሊት አለ!
የዱንያ ሀገር ሰው ሆኖ አምሽቶ የአኺራ ሰው ሆኖ ያነጋ ስንት ሰው አለ!»
:
ዱንያ ላይ የተጀመረ ነገር ሁሉ ማለቅም ጀምሯል። ረመዳን ሲሶውን ይዞ ሄዷል። ቀሪዎቹ ቀናትም ታዛቢዎች ናቸው። ምን እንደምንሰራ ይመለከታሉ። እንቅስቃሴያችንን ይዘግባሉ። አኺራ ላይ አወዳሽ ወይም ወቃሽ ሆነው ይቀርባሉ! የረመዳንን ትዝብት እንፍራ!
http://t.me/fiqshafiyamh
1.2K viewsedited  11:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-30 05:04:50 የጾም ህግጋት
በተውፊቅ ባህሩ
(ክፍል ሃያ)
============
ቀዷ እያለበት የሞተ
============
ጾም እያለበት የሞተ ሰው የተለያዩ ሁኔታዎች አሉት: ‐
⚀ በአሳማኝ ሸሪዓዊ ምክንያት ጾም አፍርሰው ቀዷ ማውጣት የሚያስችል ምንም አይነት ክፍተት ሳያገኙ በዚያው የሞቱ ሰዎች ምንም ዓይነት ቀዷም ሆነ ቤዛ መክፈል አያስፈልጋቸውም።

⚁ በሸሪዓዊ ፍቃድ ሰበብ ኖሮት ረመዳንን ሳይጾም ቀርቶ ቀዷ ማውጣት እየቻለ ቀዷውን ሳያወጣ ቀርቶ በዚያው የሞተ ሰው፤

⚂ ያለ አሳማኝ ምክንያት ጾሙን ፈትቶ ኖሮ በማንኛውም መልኩ ‐ቀዷ ማውጣት ችሎ በዳተኝነትም ይሁን በአሳማኝ ምክንያት ቀዷ መክፈል ሳይችል ቀርቶ‐ በዚያው የሞተ ሰው።…
እነዚህ ሁለቱ ሰዎች ቀዷ ሳያወጡ መቅረታቸው ማካካሻ የሚፈልግ እንደ ክፍተት የሚታይ ተግባር ነው።

ስለዚህ ትተውት ካረፉት ንብረት ላይ ተቀንሶ ባለባቸው ቀን ልክ ቤዛ ይከፈልላቸዋል። ቤዛው ለየእለቱ አንድ እፍኝ ወይም አምስት መቶ ግራም እህል ነው።

ቲርሚዚይ በዘገቡት ሐዲስ የአላህ መልክተኛ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል: ‐ «የወር ጾም እያለበት የሞተ ሰው ለእያንዳንዱ ቀን አንድ ምስኪን ያበሉለታል።» ቲርሚዚይ ሐዲሱን ዘግበውታል፤ በዐብዱላህ ኢብኑ ዑመር (ረዲየላሁዐንሁ) ላይ የቆመ "መውቁፍ" ሐዲስ መሆኑ ተመራጭ ነው ብለዋል።
ኢማም አል‐ማወርዲይ በዚህ ጉዳይ ላይ የዐሊሞች ሙሉ ስምምነት እንዳለ ጠቅሰዋል።

ለድኾች የሚሰጠው እህል አብዝሃኛው የሀገሩ ሰው የሚመገበው የእህል ዓይነት መሆኑ ወሳኝ መስፈርት ነው።

በቀድሞው የኢማም ሻፊዒይ ሃሳብ መሰረት የሟቹ ቤተሰብ "ወልይ" በእህሉ ፈንታ መጾምም ይችላል። በእርግጥ በአዲሱ ሃሳባቸው ላይ ሻፊዒይ የሟችን ቀዷ በጾም መክፈል መፈቀዱን በተከታዩ ሐዲስ ሶሒሕ መሆን እና አለመሆን ላይ አንጠልጥለው ትተውታል። ሐዲሱ ቡኻሪና ሙስሊም የዘገቡት ነው። የአላህ መልክተኛ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል: ‐
«ጾም እያለበት የሞተ ሰው ወልዩ ይጾምለታል።»
በእርግጥም ሐዲሱ ሶሒሕ ሆኖ በመገኘቱ የሻፊዒይ አዲሱ (አል‐ቀውሉል‐ጀዲድ) መሠረትም በጾም መክፈል ይቻላል ማለት እንችላለን።

ወ‌ል‌ዩ‌ የ‌ሟ‌ች‌ን‌ ቀ‌ዷ‌ የ‌መ‌ክ‌ፈ‌ል‌ ግ‌ዴ‌ታ‌ አ‌ለ‌በ‌ት‌?

ይህ በሚከተለው አስተውሎት የሚቃኝ ነጥብ ነው: ‐
ሟች ትቶት ያለፈው ኃብት ካለ ወልዩ ከሁለቱ አማራጮች አንዱን የማድረግ ግዴታ አለበት: ‐ እህል ማብላት ወይም መጾም።
ሟቹ ትቶት ያለፈው ኃብት ከሌለው ግን ወልዩ ከሁለቱ ነገሮች አንዱን ማድረግ ይወደድለታል፤ መጾም ወይም ማብላት።

ይህ አማራጭ የተሰጠው ሟቹ ሙስሊም ሆኖ ከሞተ ብቻ ነው። ሟች ከኢስላም አፈንግጦ (ሙርተድ ሆኖ) ከሞተ ግን ወልዩ ቀዷውን የሚከፍልለት በማብላት ብቻ ነው። መጾም አይፈቀድም።
ይህ ኢማም ረምሊይ "ኒሃየቱል‐ሙሕታጅ" የተሰኘው መፅሐፋቸው ላይ የተናገሩት እና ኢብኑ ሐጀር "ቱሕፋ" ላይ ያመላከቱት ሃሳብ ነው።

የ‌ት‌ኛ‌ው‌ ወ‌ል‌ይ‌?
ለሟች ቀዷ የሚከፍለው ወልይ ወራሽ ባይሆንም ሁሉም ዘመድ ነው። እዚህ ላይ ወልይ ሲባል በገንዘብ ጉዳዮች ላይ ወልይ ተብለው የሚጠሩት ሟች ገንዘቡን ማስተዳደር በማይችልባቸው ተጨባጮች ኃላፊነት የሚሰጣቸው አባት እና አያት ብቻ አይደሉም። በውርስ ስፍራ ላይ "ዐሶባ" ተብለው የሚጠሩት ሁሉም በጾታ ወንዶች የሆኑት ጠቅላይ ወራሾችም አይደሉም። በዚህ ቦታ ላይ ''ወልይዋ'' ሴትም ልትሆን ትችላለች።

ሙስሊም በዘገቡት ሐዲስ አንዲት ሴት የአላህን መልክተኛ [ﷺ] «እናቴ የስለት ጾም እያለባት ሞተች። እኔ ልጹምላት ወይ?» በማለት ጠየቀች። እርሳቸውም: ‐ «ለእናትሽ ፁሚላት።» በማለት መለሱ።
"አል‐መጅሙዕ" የተሰኘው መፅሐፋቸው ላይ ኢማም ነወዊይ እንዲህ ብለዋል: ‐ «ይህ ሐዲስ [ከላይ ባለፉት ሐዲሶች ውስጥ] ወልይ ሲባል የገንዘብም ሆነ የውርስ ወልይን ለማለት እንዳልሆነ ያረጋግጣሉ። ምክንያቱም ሴት የዐሶባም ሆነ የገንዘብ ወልይነት የላትም።»

«ሴትየዋ ወራሽ ትሁን ወይም አትሁን የአላህ መልክተኛ ማብራሪያ አለመጠየቃቸው ደግሞ ገየዳዩ አጠቃላይ እና ገደብ የለሽ መሆኑን ያስረዳል። ለሟች ጿሚ የሆነው ሰው ወራሽም ይሁን ሌላ ከግምት እንደማይገባ ያሳብቃል።» ይህ ኢማም ረምሊይ ያሉት ነው።

ወ‌ል‌ዮ‌ች‌ በ‌ጋ‌ራ‌ ቢ‌ጾ‌ሙ‌
ሰላሳ የሟች ቤተሰቦች በጋራ በአንድ ቀን ቢጾሙ ይበቃቸዋል። ይህ "አል‐መጅሙዕ" የተሰኘው መፅሀፋቸው ላይ ኢማም ነወዊይ የፈተሹት ሀሳብ ነው። ከነወዊይ ውጪ ያሉ ሌሎች ዐሊሞች ደግሞ ሰውየው የእስልምና ሐጅ፣ የስለት ሐጅ እና የቀዷእ ሐጅ ቢኖርበት እና ሦስት ሰዎች ተቀጥረው በአንድ አመት የሐጅ ክንውን ውስጥ በአንድ ጊዜ ቀዷውን ቢከፍሉለት ከሚሰጠው ብይን ጋር አመሳስለውታል። ኢማም ኢብኑ ሐጀር፣ አል‐ኸጢብ እና አር‐ረምሊይ የደገፉት ሃሳብ ይኸው ነው።

ቀ‌ዷ‌ው‌ን‌ ባ‌ዳ‌ መ‌ክ‌ፈ‌ል‌ ይ‌ች‌ላ‌ል‌?
በሁለት ሁኔታዎች ከሟች ጋር የስጋ ዝምድና የሌለው ባዳ ቐዷውን መክፈል ይችላል: ‐
⚀ ሟች ባዳ የሆነው እገሌ የተባለው ሰው እንዲጾምለት ከተናዘዘ፤
⚁ የአዕምሮ ጤና ያለው፣ ለአቅመ አዳም የደረሰ ወልይ ባዳው ቀዷውን እንዲከፍልለት ከፈቀደ።
ከሁለቱ ሁኔታዎች ውጪ በራስ አነሳሽነት ባዳ የሆነ ሰው ለሟች ቀዳ ሊከፍል አይችልም፤ አያብቃቃውም። ምክንያቱም ይህንን የሚፈቅድ የሐዲስ መረጃ አልመጣልንም።

ባዳ የሆነ ሰው ያለማንም ፍቃድ ለሟች ሐጅ ቢያደርግለት ይበቃዋል። ቀዷውም ይከፈልለታል። ስለዚህ የጾም ቀዷንም ባዳ ያለማንም ፍቃድ ቢጾም ያብቃቃል ልንል ስለሚቻል ጉዳዩ ጥናት የሚፈልግ አስቸጋሪ ነገር ነው በማለት ኢማም አል‐አስነዊይ ተናግረዋል። ይህን እንዴት ታዩታላችሁ? ሊባል ይችላል።

ነገርግን ግርታውን የሚያስወግድ መልስ አለን። ሐጅ በጥብቅ ሁኔታ ከገንዘብ ጋር ቁርኝት ያለው ዒባዳ ነው። ስለዚህ የገንዘብ እዳን ከመክፈል ጋር ተመሳስሎ እናገኘዋለን። የማንኛውንም ሰው የገንዘብ እዳ ያለማንም ፍቃድ መክፈል እንደሚቻል ደግሞ በልሂቃን ዘንድ የታመነ ነው። ጾም ግን ንፁህ ወይም የገንዘብ ንክኪ የሌለው አካላዊ ዒባዳ ነው። ስለዚህ «ጾምን ከሐጅ ጋር ማመሳሰል አይቻልም» ይሉናል፤  አል‐ኸጢብ አሽ‐ሺርቢኒይ [ረሒመሁላህ]።
https://t.me/fiqshafiyamh
1.2K views02:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-29 19:41:16 «አዩሃል‐ወለድ»
ኢማም፣ ሸይኹል‐ኢስላም፣ ሑጀቱል‐ኢስላም፣ በረከቱል‐አናም፣ አቡ ሓሚድ አል‐ገዛሊይ
ክፍል 3
1.1K viewsedited  16:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-29 06:55:37 የጾም ህግጋት
በተውፊቅ ባህሩ
(ክፍል አስራ ዘጠኝ)
=========
በጾም ቀን ጉዞ
=========
በረመዳን ጾመኛ ሆኖ ካነጋ በኋላ ጉዞ የወጣ ሰው በዚያን ቀን መካከል ጾሙን መፍታት አይችልም። ምክንያቱም የእለቱ ጾም በከፊል ቋሚ ወይም ነዋሪ በሆነበት ሀገሩ ሌላኛው ክፍል ደግሞ በጉዞው ላይ አርፏል። አንዱ ጾምን ግዴታ የሚያደርግ ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ጾም መፍታትን የሚያስፈቅድ ሁኔታ ነው። ስለዚህ ጾምን ግዴታ ለሚያደርገው፣ ማፍጠርን እርም የሚያደርገውን የቋሚ ነዋሪነት ሁኔታን እናስቀድማለን። ማፍጠር አይፈቀድለትም።

ይህ ልክ በመርከብ ላይ ሆኖ በመኖሪያ ሀገሩ ሶላት የጀመረ ሰው ዓይነት ሁኔታ ነው። በሶላት ውስጥ ሆኖ መርከቧ ሀገሩን ለቃ ሄደች። በዚህ ዓይነት ሁኔታ ላይ ሰውየው ሶላቱን ሞልቶ መስገድ እንዳለበት ምንም ዓይነት የልሂቃን ልዩነት የለም። ኢጅማዕ ነው።

ምክንያታቸው ያስቀደምነው ዓይነት ነው። ሶላቱ ቋሚ ነዋሪነት እና ጉዞን በአንድ ላይ የያዘ ሶላት መሆኑ ነው። ስለዚህ ወደ ጥንቃቄ የሚያመዝነው የነዋሪነት ሁኔታውን ከጉዞው አብልጠን ዋጋ እንሰጠዋለን። ይህም በሁሉም የአምልኮ ተግባራት ላይ የሚያገለግል እውነታ ነው። ስለዚህ ጾም ከጀመረ በኋላ ጉዞ የወጣ ሰው እለቱን በጉዞ ሰበብ ማፍጠር አይችልም።

ይህ የአብዛኞቹ ልሂቃን እምነት ነው። ከአራቱ መዝሃብ ዐሊሞች የሦስቱ መንገድም ይኸው ነው።
:
ነገርግን ጃቢር ኢብኑ ዐብዲላህን (ረዲየላሁዐንሁማ) በመጥቀስ ሙስሊም ስለዘገቡት ሐዲስ ምን ትላላችሁ የሚል ጥያቄ ሊነሳ ይችላል: ‐ «የአላህ መልክተኛ [ﷺ] መካ የተከፈተበት ዓመት ላይ በወርሃ ረመዳን ወደ መካ አቀኑ። "ኩራዐል‐ገሚም" የተሰኘው ቦታ እስከሚደርሱ ጾመኛ ነበሩ። ሰዎችም ጾመዋል። ከዚያም ውሃ የተሞላ ኩባያ አስመጥተው ሰዎች በግልፅ እንዲመለከቱ ከፍ አድርገው አሳዩ። ከዚያም ውሃ ጠጡ።»

ዐሊሞች ለዚህ ጥያቄ መልስ አላቸው። እንዲህ ይላሉ: ‐ «የአላህ መልክተኛ [ﷺ] ጾመኛ ሆነው ጉዞ በወጡበት እለት አላፈጠሩም። ምክንያቱም "ኩራዑል‐ገሚም" ከመዲና የሰባት ቀን መንገድ እና ከዚያ በላይ የምትርቅ ስፍራ ናት። ስለዚህ ሐዲሱ ጾመኛ ሆኖ ጉዞ በጀመረበት ‐ጉዞና ቋሚ ነዋሪነት በአንድ ላይ ባረፉበት እለት‐ ጾምን ማፍረስ ይፈቀዳል ለማለት ማስረጃ አይሆንም።

ኢማም ነወዊይ "ሸርሑ ሙስሊም" ላይ እንዲህ ብለዋል: ‐ «ይህንን ሐዲስ መረጃ ለማድረግ የሚፈልግ ሰው ሃሳብ እጅግ የሚያስገርም እና እንግዳ የሆነ ሃሳብ ነው!»

በእርግጥ በጠቀስነው ሁኔታ ላይ ያለ ሰው ማፍጠር ይችላል የሚለው ሃሳብ የኢማም አሕመድ እና የሙዘኒይ እምነት ነው። ነገርግን "አልሓዊ" በተሰኘው መፅሐፍ ላይ እንደተጠቀሰው ኢማም አል‐ሙዘኒይ ከዚህ ሃሳባቸው ተመልሰዋል። እንደውም «ይህንን ቃሌን ወዲያ ጣሉት!» ብለዋል እየተባለ ይነገራል። ደግሞም የኢማም አል‐ማወርዲይ ድርሰት የሆነው "አልሓዊ"፣ "ሙኽተሶሩል‐ሙዘኒይ" የተሰኘው የኢማም አል‐ሙዘኒይ መፅሐፍ ማብራሪያ (ሸርሕ) ነው!
አላሁ አዕለም!
https://t.me/fiqshafiyamh
1.3K viewsedited  03:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-28 22:31:32
ሰባተኛው ሌሊት መሆኑ ነው?!…
ኢላሂ! ረመዷናችንን የዓፊያ ረመዳን አድርገው። ካንተ ከሚቆርጠን ነገር ሁሉ ዳግም ላንገናኝ ቁረጠን። ኃጢኣት ካንተ የሚጋርደን ሒጃብ ነው። በምህረትህ ሒጃባችንን ግለጠው።…
* * *
ኢላሂ! ከኃጢኣት እስር፣ ከነፍሱ ምርኮ የዳነ ያንተን ከራማ፣ የፍቅርህን ስጦታ ያገኛል።… ከፍቅርህ በኋላና በፊት ደግሞ ከጀነት በቀር ምን አለ?!…
ኢላሂ! ይህንኑ ፃፍልን!
* * *
ረመዳን የተሸከመውን የችሮታ ክምር በእኛ ላይ አኑረው። የዘልዓለም አዝመራችንን የምናጭድበት፣ የእድሜ ልክ ትርፋችንን የምናካብትበት ፀደይ አድርግልን።…
አሚን!
https://t.me/fiqshafiyamh
1.6K viewsedited  19:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-28 12:17:07 «አዩሃል‐ወለድ»
ኢማም፣ ሸይኹል‐ኢስላም፣ ሑጀቱል‐ኢስላም፣ በረከቱል‐አናም፣ አቡ ሓሚድ አል‐ገዛሊይ
ክፍል 2፤ የደራሲው መቅድም ቀጣይ
1.3K viewsedited  09:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-28 09:53:33 በ͟ሱ͟ጁ͟ድ͟ ወ͟ቅ͟ት͟ ቁ͟͟ር͟͟ኣ͟͟ን͟͟ን͟͟ በ͟መ͟ሬ͟ት͟ ላ͟ይ͟ ማ͟ኖ͟ር͟

መስሐፍን (የታተመ የቅዱስ ቁርኣን ቅፅ) ማክበር ግዴታ ነው። አላህ እንዲህ ብሏል: ‐

{ذَٰلِكَ وَمَن يُعَظِّمْ شَعَائِرَ اللَّهِ فَإِنَّهَا مِن تَقْوَى الْقُلُوبِ}

«(ነገሩ) ይህ ነው፡፡ የአላህንም የሃይማኖት ምልክቶች የሚያከብር ሰው እርሷ ከልቦች የኾነች ጥንቃቄ ናት፡፡»

ኢማም ኢብኑ ሐጀር አል‐ሀይተሚይ "አልፈታዋ አል‐ፊቅሂያ" በተሰኘው መፅሐፋቸው ቅፅ 2፥ ገፅ 6 ላይ እንዲህ ይላሉ: ‐
«ቁርኣንም ሆነ ማንኛውም የተከበረ ስም ‐ለምሳሌ: ‐ የአላህ ስም፣ የነቢይ ስም‐ ያለበት ፅሁፍን ማክበር፣ ማላቅ እና ማክበድ ግዴታ ነው።»
:
ሱጁድ ስናደርግ ወይም በሌላ ሁኔታ ውስጥ ስንሆን በመሬት ላይ አለማስቀመጥ መስሐፍን ከማክበር መገለጫዎች መካከል አንዱ ነው። ይልቁንስ ከመሬት ከፍ ያለ ማስቀመጫ ፈልጎ ከላይ ያድርገው። ወይም አጠገቡ ላለ ሰው ያቀብለው።

መስሐፍን መሬት ላይ ማስቀመጥ ከሻፊዒዮች ኢማም አል‐መይዳኒይ፣ ከማሊኪዮች ደግሞ ኢማም ዒለይሽ ሐራም ነው በማለት ፈትዋ ሰጥተውበታል።

አቡዳዉድ አል‐ሷሒፍ በተሰኘው መፅሐፋቸው ላይ ከዑመር ኢብኑ ዐብዱል‐ዐዚዝ እንደዘገቡት: ‐ «የአላህ መልክተኛ [ﷺ] አላህ የተጠቀሰበትን መፅሐፍ መሬት ላይ ተጥሎ አገኙ። ከዚያም «ይህንን እንዲህ ያደረገ ማን ነው?» አሉ። «ሂሻም ነው።» አሏቸው። እርሳቸውም «ይህንን ባደረገ ሰው ላይ የአላህ ርግማን ይሁን። አላህ የሚወሳበትን ፅሁፍ ያለ ቦታው አታድርጉ።» አሉ።»

በእርግጥ ታቢዒይ የሆኑት ዑመር ኢብኑ ዐብዲል‐ዐዚዝ ሶሐባ ሳይጠቅሱ በቀጥታ ነቢዩን [ﷺ] ዋቢ አድርገው በመዘገባቸው ሐዲሱ "ሙርሰል" ነው። ስለዚህ ድክመት አለበት። ነገርግን መግቢያችን ላይ የጠቀስነው አንቀፅን የመሰሉ ጥቅል መልእክት ካዘሉ መረጃዎች ጋር አጣምረን ጥንቃቄ እንድናደርግ ይገፋፋናል።

አንዳንድ ሰዎች በተለይም በተራዊሕ ወይም በተሀጁድ ጊዜ ሱጁድ ማድረግ ሲሹ በአንድ እጃቸው መስሐፉን ይዘው መሬት ላይ እያስቀመጡ ሲሰግዱ ይስተዋላል። ይህ አይነት ተግባር በአንድ በኩል ከሰባቱ የሱጁድ አካላት መካከል አንዱ የሆነው እጅ መሬት ላይ በትክክል እንዳያርፍ ስለሚያግድ ሱጁዱን ውድቅ ሊያደርግ ይችላል። በዚያ ላይ ሙስሐፍን ማዋረድና በመሬት ላይ መጎተት ሊንፀባረቅበት ይችላል።

ያላከበርነው ቁርኣን አያከብረንም! ቁርኣን ያዋረደው ደግሞ ምንም ነገር አያከብረውም! በአካላዊ ገፅታችን ክብር ላልሰጠነው ቁርኣን በቀልባችን እንሰጠዋለን ማለት ውሸት ነው! ስለዚህ ወዳጆች ጥንቃቄ አይለየን!
1.6K viewsedited  06:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-27 22:42:33 የጾም ህግጋት
በተውፊቅ ባህሩ
(ክፍል አስራ ስምንት)
======================
በእርጅና ምክንያት መጾም የማይችል
=======================
መጾም የማይችል የጃጀ ሽማግሌ ወይም ባልቴት በተለያዩ ሁኔታዎች ይቃኛል: ‐
⚀ አዕምሮው በደህና ሆኖ አካሉ በመድከሙ ምክንያት መጾም ከተሳነው ጾም ግዴታ አይሆንበትም። ነገርግን ለእያንዳንዱ ቀን አንድ እፍኝ እህል ለድኾች በመስጠት ቤዛ መክፈል አለበት። አላህ እንዲህ ብሏል: ‐

[وَعَلَى الَّذِينَ يُطِيقُونَهُ فِدْيَةٌ طَعَامُ مِسْكِينٍ ]

«በእነዚያም ጾምን በማይችሉት ላይ ቤዛ ድኻን ማብላት አለባቸው፡፡»

⚁ የአዕምሮ ጤናው ከእርጅና ጋር ስተጓጎለ ከሆነ ጾም መጾምም ሆነ ቤዛ መክፈል ግዴታ አይሆንበትም። ምክንያቱም ይህን ሰው በዒባዳ ተገዳጅ (ሙከልለፍ) የሚያደርገው ዋናው መስፈርት (የአዕምሮ ጤናማነት) አልተገኘም።

⚂ አዕምሮው እየመጣ የሚሄድ ከሆነ፣ አንዴ እንደመደበኛ ሰው ማመዛዘን ሲችል በሌላ ጊዜ ደግሞ የሚዘባርቅ ከሆነ ደግሞ ጤነኛ አዕምሮ ለሚኖረው ቀን ብቻ ቤዛ የመክፈል ግዴታ ይሆንበታል። ይህ ግዴታ የሚሆነውም ቀኑን በሙሉ ‐ከፈጅር እስከ መግሪብ‐ ጤናማ ሆኖ ካሳለፈ ብቻ ነው።
አላሁ አዕለም!
https://t.me/fiqshafiyamh
1.4K viewsedited  19:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-27 21:23:02 «አዩሃል‐ወለድ»
ኢማም፣ ሸይኹል‐ኢስላም፣ ሑጀቱል‐ኢስላም፣ በረከቱል‐አናም፣ አቡ ሓሚድ አል‐ገዛሊይ
ክፍል 1፤ መግቢያ እና የደራሲው መቅድም
1.3K viewsedited  18:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ