Get Mystery Box with random crypto!

Tofik Bahiru

የቴሌግራም ቻናል አርማ fiqshafiyamh — Tofik Bahiru T
የቴሌግራም ቻናል አርማ fiqshafiyamh — Tofik Bahiru
የሰርጥ አድራሻ: @fiqshafiyamh
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 6.13K

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2023-04-19 19:53:59 Tofik Bahiru pinned «ዘካቱል‐ፊጥር ወደ ሀገርቤት መላክ ======================= በሻፊዒያ መዝሀብ መሰረት የገንዘብ ዘካንም ሆነ ዘካቱል‐ፊጥርን ከወጀበበት ሀገር ወደ ሌላ ሀገር መውሰድ አይፈቀድም። ይኸውም ከወጀበበት ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ዘካውን ማዛወር የሚያስፈቅድ አሳማኝ ምክንያት እስከሌለ ድረስ ነው። የዚህ ሃሳብ አስረጂ የሙዐዝ ኢብኑ ጀበል [ረዲየላሁ ዐንሁ] ሐዲስ ነው። ሰይዲና ሙዐዝ ወደ የመን በተላኩ ጊዜ…»
16:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-19 08:15:54 ዘካቱል‐ፊጥር ወደ ሀገርቤት መላክ
=======================
በሻፊዒያ መዝሀብ መሰረት የገንዘብ ዘካንም ሆነ ዘካቱል‐ፊጥርን ከወጀበበት ሀገር ወደ ሌላ ሀገር መውሰድ አይፈቀድም። ይኸውም ከወጀበበት ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ዘካውን ማዛወር የሚያስፈቅድ አሳማኝ ምክንያት እስከሌለ ድረስ ነው።
የዚህ ሃሳብ አስረጂ የሙዐዝ ኢብኑ ጀበል [ረዲየላሁ ዐንሁ] ሐዲስ ነው። ሰይዲና ሙዐዝ ወደ የመን በተላኩ ጊዜ ነቢዩ [ﷺ] እንዲህ አሏቸው: ‐
«ከኃብታሞቻቸው ተወስዶ ለድኾቻቸው የሚካፈል ምፅዋት (ዘካ) እንዳለባቸው አሳውቃቸው።» ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።

በዚያ ላይ የገንዘቡ ምንጭ የሆነው ሀገር ድኾች በዘካው ላይ ተስፋ ጥለው በጉጉት እየጠበቁ ሳለ ዘካውን ወደሌላ ቦታ መውሰድ መከፋት ይፈጥራል ተብሎ ይታመናል። የሚኖርበት ሀገር ድኾች በዘካ ሰጪው ላይ መጥፎ ስሜት እንዲያድርባቸውም ያደርጋል።

ነገርግን በዘካው ሀገር ላይ ዘካ የሚገባው ሰው ከታጣ ወይም የሰውየው ዘካ ከሀገሩ ባለ መብቶች ፍላጎት በላይ ሆኖ ከተገኘ ወይም ዘካውን የሚያከፋፍለው የሀገር መንግስት ከሆነ ዘካን ከባለ ዘካው ሀገር (በለዱል‐ዉጁብ) ወደ ሌላ አካባቢ መውሰድ ይቻላል።

ይህ ሀሳብ ከሻፊዒዮቹ በተጨማሪ ከማሊኪዮቹ በብዛት የተዘገበ መዝሀብ ነው። ኢብኑ ቁዳማ "አል‐ሙግኒ" በተሰኘው መፅሀፋቸው ላይ እንደጠቀሱት ኢማም አሕመድም ሶላት ማሳጠር የሚፈቀድበት ርቀት ያክል ዘካን ማዘዋወር ይከለክላሉ።
* * *
ኢማም ሐሰን አል‐በስሪይ፣ ኢማም አን‐ነኸዒይ እና ሐነፊዮቹ ደግሞ ዘካን ከወጀበበት ሀገር ወደ ሌላ ሀገር ማዘዋወር በቀላሉ የሚጠላ (ከራሃቱ አት‐ተንዚህ) ነው ይላሉ። ይህንን ያሉበት ምክንያት የባለ ዘካውን ጎረቤቶች መብት በማሰብ ነው።

ነገርግን በእነዚህ የዐሊሞች ቡድን መሰረት ሰውየው ዘመዶቹን አስቦ ከገንዘቡ ሀገር ዘካውን ያዛወረ ከሆነ ከቶውንም አይጠላም ባይ ናቸው። እንደውም እንደነርሱ ከሆነ ተገቢው ለዘመዶቹ መላክ ነው። "ሙጅመዕ አዝ‐ዘዋኢድ" በተሰኘው መፅሀፍ ላይ በተከታዩ ሐዲስ የአላህ መልክተኛ [ﷺ] እንዲህ ማለታቸው ተዘግቧል: ‐
«የዝምድና ቅጠላውን (ድጋፉን) የሚሹ ዘመዶች ያሉትን ሰው ምፅዋት አላህ አይቀበልም።»

በሌላ ሐዲስም የአላህ መልክተኛ [ﷺ] እንዲህ ይላሉ: ‐
«ሶደቃ ለምስኪን ሲሰጥ ምፅዋት ብቻ ነው። ለዘመድ ሲሰጥ ግን ምፅዋት እና ዝምድና መቀጠልም ነው።»

በተጨማሪም ነቢዩ [ﷺ] የዐረብ ዘላኖችን (አዕራቦች) ዘካ ሰብስበው ለመዲና ሙሀጂር እና አንሷሮች ያካፍሉ እንደነበር በሰፊው ተዘግቧል።

እንደውም በተጠቀሰው እና በሌሎችም መረጃዎች የተደገፈውን የሐነፊዮቹን ሃሳብ ከቀደምቶቹም ሆነ ከቅርቦቹ (ሙተኣኺር) ሻፊዒዮች መካከል በርካቶች ተጠቅመውበታል። አል‐ቀልዩቢይ "አልሓሺያ ዐላ ሸርሒል‐ሚንሃጅ" በተሰኘው መፅሐፋቸው ላይ እንዲህ ይላሉ: ‐

«…ሁለተኛው ሃሳብ: ‐ «ዘካን ከቦታው ማዛወር ይፈቀዳል፤ ያብቃቃል» ይላል። ከሻፊዒይ አንጋፋ ባልደረቦች (አስሓብ) በርካቶች ይህንን ሃሳብ መርጠዋል። ኢብኑ ሶላሕ፣ ኢብኑል‐ፈርካሕ እና ሌሎችም ከነርሱ ይጠቀሳሉ።
ሸይኻችን (ጀላሉዲን አል‐መሐሊይ) ሸይኻችን [ኢማም] ረምሊይን ዋቢ አድርገው እንደጠቀሱት: ‐ «ሰውየው ለግሉ በዚህ ሃሳብ መስራት ይችላል። ልክ እንደዚሁ በማናቸውም ህግጋት ላይ የሚታመኑትን ኢማሞች ተከትሎ መስራት ይችላል። ድጋፍ ባለው ሃሳብ (ሙዕተመድ) መሰረት እንደ አል‐አዝረዒይ፣ ሱቡኪይ፣ አል‐ኢስነዊይን እና ሌሎቹንም መከተል ይፈቀድለታል።»

በመሆኑም በተለይም ከሀገር ውጪ ሆነው ዘካቸውን ወደ ሀገር ቤት መላክ የሚሹ ሰዎች ይህንን መዝሀብ ቢከተሉ መልካም ነው የሚል ጥቆማ እንሰጣለን። በተለይም ሀገራችን አሁን ላይ እያሳለፈችው ባለው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ውጥንቅጥ አንፃር ለወገን የመድረስ እና ህይወትን የመታደግ ያክል ስለሚሆን ጉዳዩ አሳሳቢ ይሆናል። ከሀገራችን ችግረኞች የቀደመ ተገቢነት ያለው ሌላ አካል ይኖራል ተብሎም አይገመትም።
በተረፈው መጠኑን ሰውየው በሚኖርበት ሀገር ተመን መሰረት ዘካውን ያሰላዋል እንጂ ዘካውን ማዛወር በፈለገበት ሀገር ዋጋ አያሰላውም።
ኢማም ነወዊይ [ረሒመሁላህ] "አል‐መጅሙዕ" በተሰኘው መፅሐፋቸው ላይ እንዲህ ብለዋል: ‐
«ከፊል ገንዘቡ በአንድ ሀገር ላይ ሆኖ ከፊሉ በሌላ ሀገር ቢሆን እንኳን ያለ ምንም (የሻፊዒዮች) ልዩነት ዘካቱል‐ፊጥሩን የሚሰጠው እርሱ በአካል ባለበት ሀገር ነው።»
አላሁ አዕለም!
http://t.me/fiqshafiyamh
1.1K viewsedited  05:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-19 02:24:28 ኢላሂ!
ያዘዝከንን ትተናል፤
የከለከልከንን ተዳፍረናል፤
ለነውራችን ምክንያት አናቀርብም።
ቢሆንም ባሮችህ ነን፤ ለባሮችህ ደግሞ በንፁህ ችሮታህ የምህረት በርህን ከፍተሃል።
ያ ረቢ ማረን!
1.3K viewsedited  23:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-18 17:45:47 «ረመዳንን አላህ ለሰዎች በሙሉ የውድድር ጊዜ አድርጎታል። በዒባዳ ይሽቀዳደሙበታል።…
አንዳንዶቹ ቀዳሚ ሆነው ተገኙና ፍላጎታቸውን አሳኩ።
አንዳንዶቹ ደግሞ ወደ ኋላ ቀሩና ከሰሩ።
የሚደንቀው ፈጣኖቹ ባሸነፉበት እና ሰነፎቹ በከሰሩበት ቀን የሚስቅ እና የሚጫወት ሰው መኖሩ ነው።
በአላህ አስጠነቅቃችኋለሁ!
በአላህ አስጠነቅቃችኋለሁ!
ከቀዳሚዎቹ እንድትሆኑ ታትራችሁ ሥሩ።
ከከሳሪዎች እንዳትሆኑ!»
ሐሰኑል በስሪ [ረሒመሁላህ]
1.6K views14:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-18 14:41:17 የዘንድሮ (2015 ዓ. ል.) ዘካቱል‐ፊጥር ስንት ነው?
====================
ዘካቱል ፊጥር ቀድሞ የተደነገገው በአህል ነው። የአንድ ሰው የዘካ ድርሻ አንድ ቁና እህል ይሆናል። ከዒድ ሶላት አስቀድሞ ድኾች በእለቱ እንዳይቸገሩና ከሌሎች ጋር ዒዱን በደስታ እንዲያሳልፉ የተደነገገ ነው።
መጠኑ የተደነገገው በስፍር ነው። ኢብኑ ሶብ‐ባግ እንደሚሉት: ‐ «ዓሊሞቹ በክብደት ያሰሉት ለማቀራረብና የስፍሩን መጠን ለማሳየት ነው።» ድንጉግ መሰረቱ ስፍር እስከሆነ ድረስ ተመሳሳይ ስፍር ያላቸው እእህሎች አንዱ ከሌላው ጋር የተለያየ ክብደት ሊኖረው እንደሚችል ግልፅ ነው። ተምር፣ ስንዴ፣ በቆሎ [ወዘተ] ተመሳሳይ ክብደት ላይኖራቸው ይችላል።
ይሁንና አንድ ቁናን በርካቶቹ ከ2.4 ኪሎ ግራም ጋር አቀራርበውታል። ብዙ የሀገራት የፈትዋ ኮሚቴዎች በ2.5 (ሁለት ኪሎ ተኩል) ያስቡታል።

የእኛ ሀገር መደበኛ (የአብዝሃኛው) ቀለብ ስንዴ ነው። ስለዚህ ዘካቱል‐ፊጥር ለአንድ ሰው 2.5 ኪሎ ስንዴ ብለን እንይዘዋለን።

በዋጋው የመስጠት ጉዳይ ከታቢዒዮች ዘመን ጀምሮ እስካሁን አከራካሪ ነው። እህሉን እንጂ ዋጋውን መስጠት የማይፈቀድ መሆኑን የሚያምኑ ዐሊሞች አብዛኞቹ ናቸው። የሳዳቶቻችን ሻፊዒዮች መዝሀብም ይኸው ነው። ነገርግን በተለያየ ምክንያት በሀገራችን እና በሌሎች በርካታ ሻፊዒያ በዝ ሀገራት ውስጥ ሳይቀር የኢማም አቡ ሐኒፋን እና መሰሎቻቸውን መዝሀብ በመከተል በወረቀት ገንዘብ ተተምኖ ይከፈላል። ከሻፊዒዮቹ ታላቁ ረምሊይ ሳይቀር "የፈታዋ" መድብላቸው ላይ አቡ ሐኒፋን መከተል እንደሚቻል አሳውቀዋል።

ውዝግቡን ወደ ኋላ አድርገን በዋጋ ስንተምን እንዲህ እንላለን: ‐
ደካማው ወንድማችሁ ባጣራሁት መሰረት በአዲስ አበባ የአንድ ኪሎ ስንዴ ዋጋ 70 ብር ነው። ስለዚህ የ2.5 ኪሎው 175 ብር ይመጣል። አንድ መቶ ሰባ አምስት ብር የአንድ ሰው ዘካ ነው። ከራሱ አልፎ ለሌሎቹ ቤተሰቦቹ ዘካ የሚያወጣ ሰው ይህንኑ ተከትሎ በነፍስ ወከፍ 175 ብር ይሰጣል።
ዘካችሁን በእውቀት እንድትፈፅሙና ለባለመብቶች በፍጥነት እንድታደርሱ አደራ እላለሁ!
አላህ ይቀበለን!
http://t.me/fiqshafiyamh
1.9K viewsedited  11:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-18 00:21:09 ኢላሂ!
ወገብ የሚያጎብጥ የኑሮ ሸክም እና የዲን ጉዳይ ያላቸው ወዳጆች በኛ ተስፋ አድርገው በዱዓ አደራ ብለውናል።
ያ ረቢ! በኛ ከበጃ ሳይሆን በነርሱ ተስፋ ይሁንብህ አታዋርደን!
ያልታሰበ ሪዝቅህን፤
የማያልቅ ምህረትህን፤
የማይዋዥቅ ዓፊያህን፤
የተደላደለ ኑሮ ስጣቸው። ያሰቡትንም ሆነ ያላሰቡትን ጉዳያቸውን ፈፅምላቸው። የቀልባቸውን ጭንቀት ገላግላቸው።
አሚን!
1.8K views21:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-18 00:14:46 ስለ ዘካቱል‐ፊጥር ህግጋት የፃፍኩትን መጣጥፍ ሚንበር ቲቪ ለአንባቢ በሚመች መልኩ እንደዚህ አሳምረው ለጥፈውታል። አላህ ይቀበለን። በረካ ይሁኑ። አላህ ይቀበላቸው!
1.7K viewsedited  21:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-17 20:27:28 ዘካቱል‐ፊጥር
(ተጨማሪ ሃሳብ)
===========
⇉ ዘካቱል‐ፊጥሩን ለባለሱቅ ወይም ለሆነ ሰው ሰጥቶ "እገሌ ከመጣ ፊጥራዬን ስጠው።" አለው። ነገርግን ባለሱቁ ወይም ተወካዩ ዘካውን ሳይሰጥ ከእለቱ አሳለፈው። ከዚህ ቀደም እንዳልነው ባለሱቁ የወኪልን ብይን ይይዛል።

የተወከለበትን ዘካ ከእለቱ በማቆየቱ ወንጀለኛ ይሆናል። ዘካ ሰጪውም ቀን እያለፈ መሆኑን ወይም ሰውየው ቸላተኛ መሆኑን እያወቀ ካሳለፈ ወንጀለኛ ይሆናል። ዘካውን ሳይሰጥለት ጭራሽ ከተወው ደግሞ ከራሱ መክፈል ይኖርበታል።

⇉ ፊጥራ የወጀበበት ሰውዬ ዘካውን ሲሰጠው ድኻው ደግሞ አንተ ዘንድ አስቀምጥልኝ አለውና ቀኑ አለፈበት ልክ እንደዚሁ ይታያል። ዘካ አውጪው በማዘግየቱ ይጠየቃል። ምክንያቱም ለድኻው እስካላስረከበ እንደሰጠ አይታሰብም። ድኻው ከፈለገ መልሶ በአደራ መልክ ማስቀመጥ ይችላል። ከዚያም ባሻው ገዜ ከሰውየው ላይ ይወስዳል።

⇉ በዘካ አውጪው እና በድኻው መካከል የገባው ሰው የድኻው ተወካይ ከሆነ ነገሩ ይለያል። በዚህ መሰረት ድኻው "የእገሌን ፊጥራ ተቀበልልኝ" ብሎ ሰው ላከ ወይም ዘካ አውጪው ዘካ የምሰጥልህ ሰው ላክልኝ አለውና አንድን ሰው ላከ ተቀባዩ የድኻው ወኪል ስለሆነ እጁም እንደ ድኻው እጅ የሚቆጠር ይሆናል። ስለዚህ አንዴ እርሱ እጅ ከገባ በኋላ ከብዙ ጊዜ በኋላ ለድኻው ቢሰጥም ዘካ አውጪውን የሚመለከት ምንም ጥያቄ የለም። ለወኪሉ በመስጠት ጫንቃውን አፅድቷል!
አላሁ አዕለም!
1.7K views17:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-17 19:36:22 ያ ረቢ!
አባቶቻች፣ እናቶቻችን፣ ወዳጆቻችንን፣ የ"ላኢላሃ ኢለላህ'' ወገኖቻችንን በአፈራቸው ውስጥ አኑረናል። ከስራዎቻቸው ጋር ተገናኝተዋል። በዘሩት አዝመራ ተይዘዋል። እንደኛ አይላወሱም። ያጎደሉትን አይክሱም። ላጠፉት ነገር ምህረት አይጠይቁም። በቀብር እንድናኖራቸው ያዘዝከን አንተ ነህ።

ያ ረቢ! ቀብራቸውን ብርሃን አድርግላቸው። በደስታና በእረፍት ሙላላቸው። በፀጥታ እና በሰላም ክበባቸው። በይቅርታ እና በእዝነትህ ተመልከታቸው!
ኢላሂ ያ አላህ!
1.4K views16:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-17 04:31:03
ሶላቱ ተሳቢሕን እንድትሞክሩት ላስታውሳችሁ። ዝርዝሩን በተከታዩ ሊንክ ማግኘት ይችላሉ:

https://t.me/fiqshafiyamh/1078

አላህ ተውፊቅ ይስጠን። በመልካም ዱዓችሁ አስቡን!
569 viewsedited  01:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ