2023-05-11 09:12:23
"አቡዘር (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉ
ሰዎች መልዕክተኛውን (ሶ.ዐ.ወ)፦
«የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ሀብታሞች ምንዳውን ሁሉ አግበሰበሱት እኛ እንደምንሰግደው ይሰግዳሉ፣ እኛ እንደምንፆመው ይፆማሉ፣ በተጨማሪም በትርፍ ገንዘባቸው ምፅዋት በመለገስ (እኛ ልንፈጽመው ያልታደልነውን) ሰናይ ተግባር ይፈፅማሉ።» አሏቸው። «አላህ የምትመጸውቱት ነገር (ሀብት) አልገሳችሁምን?» እያንዳንዱ «ተስቢህ» ሶደቃ ነው። እያንዳንዱ «ተክቢር» ሶደቃ ነው። እያንዳንዱ «ተሕሚድ» ሶደቃ ነው። እያንዳንዱ «ተህሊል» ሶደቃ ነው። በመልካም ነገር ማዘዝ ሶደቃ ነው። ከመጥፎ ነገር መከልከል ሶደቃ ነው። ከናንተ አንዳችሁ ወሲባዊ ተራክቦ መፈጸም ሶደቃ ነው። በማለት መልዕክተኛው (ሶ.ዐ.ወ) ተናገሩ። «አንዳችን ወሲባዊ ስሜቱን ስላረካ ምንዳ ያገኛልን?» ስሉ ጠየቁ (ሰዎቹ)። «ስሜቱን በሐራም ሁኔታ ቢያረካ ወንጀል አይሆንበትምን? ይህ እንደሆነ ሁሉ በሃላል ማርካቱ ምንዳ ያስገኝለታል" አሉ መልዕክተኛው።"
(ሙስሊም ዘግበውታል)
- ሙስሊም ዘግቦታ"
==========================================
ይህን ሐዲስ ያገኙውት ከ ኢትዮ ቢላል ሃዲስ አፕ ነዉ ።
https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
36 views06:12