Get Mystery Box with random crypto!

ፈትህ አባቦራ መስጂድ

የቴሌግራም ቻናል አርማ fethababora — ፈትህ አባቦራ መስጂድ
የቴሌግራም ቻናል አርማ fethababora — ፈትህ አባቦራ መስጂድ
የሰርጥ አድራሻ: @fethababora
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.06K

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2023-05-15 09:43:21 በደል ያጠፋል፣ ፍትህ ይክሳል!

ሀገራችን ባለፉት አመታት ካሳለፈችው አስከፊ ጦርነት ተላቃ በጦርነቱ ሳቢያ የተመሰቃቀሉ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፓለቲካዊ እንቅስቃሴዎችን ለማስተካከል ብዙ ሸክም ይጠብቃታል::

ይህ ከባድ ሸክም በመንግስት ላይ ብቻ ሳይሆን ይበልጡኑ በህዝቡ ላይ ጫናው የበረታ ነው:: በኑሮ ውድነት፣ በብልሹ አሰራር እና በፖለቲካ ሴራዎች ህይወትን መግፋት ከባድ እየሆነበት ላለው ህዝብ አግባብነት በሌላቸው ውሳኔዎች እና የግል ፍላጎቶች ዜጎች እንዲማረሩ እየተደረገ ይገኛል:

መንግስት ለዜጎቹ ጥላ እና ከለላ መሆን ሲገባው መጠለያ እና ከለላ ነሺ ከሆነ፣ በመግባባት እና በመተማመን መፈታት የሚገባቸውን የማህበረሰብ ችግሮች ኃይልን ብቻ ታሳቢ ባደረገ መልኩ ለመፍታት ከተሞከረ፣ አቅመ ደካሞችን እና ድሆችን አቅፎ ከችግራቸው ለማላቀቅ ከመልፋት ይልቅ በችግር ላይ ችግር በእነሱ ላይ መጨመር አማራጭ ተድርጎ ከተያዘ፣ የዜጎች በሰላም ወጥተው የመግባት መብታቸው አደጋ ውስጥ ከወደቀ፣ በፈለጉት የሀገሪቷ ቦታዎች ተዟዙሮ የመኖር እና የመስራት ህጋዊ መብቶች ከተነፈጉ፣ ከህግ አግባብ ውጪ በታጣቂዎች እና በመንግስት የፀጥታ ሀይሎች የሚወሰዱ የዘፈቀደ እስር እና ግድያዎች መበራከት፣ የእምነት ተቋማት እየተደፈሩ በግብረሀይል የሚወድሙ ከሆኑ፣የሀይማኖት ነፃነትን በሚጋፋ መልኩ ሀይማኖታዊ አለባበሶችን የሚገድቡ አመራሮች እዚህም እዛም መኖራቸው፣ በህዝብ እና በመንግስት መካከል ያለው የመተማመን ስሜት እንዲጠፋ እና እንዲሸረሸር ያደርጋል::

ዜጎች የሚደርስባቸውን በደል እና ግፍ ለማስቆም ስሞታቸውን ሲያሰሙ ጆሮ ዳባ ልበስ ብሎ መጓዝ፣ የበላይ አመራሮች እና ሀላፊዎችም የህዝብን እሮሮ አድምጠው የማስተካከያ እና የእርምት እርምጃ እንዲወሰድ አፋጣኝ አቅጣጫ ከመስጠት ይልቅ ዳተኛ መሆናቸው ሀገሪቷን ለሚመራው መንግስትም ትልቅ ዕዳ ይዞ መምጣቱ አይቀርም::

በደል መጨረሻው ውርደት እና ጨለማ ነው:: ከግለሰብ አንስቶ እስከ ማህበረሰብ በጅምላ የሚፈፀሙ በደሎች እና ግፎች ድምር ውጤታቸው በበዳዮች ላይ ኪሳራን እንጂ አይጨምርላቸውም::

ጌታችን አላህ ሱወ በቅዱስ ቃሉ ይህን ይለናል

"አላህንም በደለኞች ከሚሠሩት ግፍ ዘንጊ አድርገህ አታስብ፡፡ የሚያቆያቸው ዓይኖች በእርሱ እስከሚፈጡበት ቀን ድረስ ብቻ ነው" (ሱረቱል ኢብራሂም:42)

ስልጣን ህዝብን ማገልገያ መሳሪያ ነው:: ይህን ትልቅ ሃላፊነት የተረከበ አመራር ሃላፊነቱን ለመወጣት ቃለመሀላ ሲፈፅም ለህዝብ ታማኝ ሆኜ በቅንነት ላገለግል ቃል እገባለው ያለውን መዘንጋት የለበትም::ሃላፊነቱን በመረከቡ ትልቅ ተጠያቂነትም ይኖርበታል:: ከታችኛው የመንግስት መዋቅር ሲያጠፋ የላይኛው አመራር ተጠያቂነትን እንዲሰፍን ካላደረገ ህዝብን ወደ ምሬት ማስገባቱ አይቀርም::

ህዝብን በእኩልነት እና በፍትህ ማስተዳደር በበደል የጎበጡ ትከሻዎችን እና የቆሰሉ አካሎችን ይጠግናል:: በደልን የሚጠየፍ መሪ ከተጠያቂነትም ይድናል:: ሁሉም ባለድርሻ አካላት ባሉበት የሀላፊነት ደረጃ እኩልነትን፣ ፍትህን እና አገልጋይነትን መርሃቸው አድርገው ሊጓዙ እንደሚገባ ለማሳሰብ እወዳለሁ


Ustaz abubeker ahmed

https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
134 views06:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-15 07:46:05
#በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ
#አልስነይን 25 #ሸዋል 1444 ሂ
124 views04:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-15 07:41:38 "ዓኢሻ (ረ.ዐ) እንዳወሳችው የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡- ‹‹አንዲት ሴት ከቤቷ ምግቦች ‹‹ሶደቃ›› ስትሰጥ ያለአንዳች ማባከንና ማበላሸት ወጭ ባደረገችው ሽልማት (አጅር) አላት፡፡ ባሏም ምንዳ አለው የስራው ውጤት በመሆኑ፡፡ የዕቃ ቤት ኃላፊው (ሰራተኛው) በተመሳሳይ ሁኔታ (ምንዳ) ይኖረዋል፡፡ የአንዱ ሽልማት የሌላውን ሽልማት (ምንዳ) አይቀንስም፡፡››
(ቡኻሪ ዘግበውታል) - ቡኸሪ ዘግቦታ"
==========================================
ይህን ሐዲስ ያገኙውት ከ ኢትዮ ቢላል ሃዲስ አፕ ነዉ ።


https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
119 views04:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-15 04:54:44 #Update

የቱርክ ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ እጅግ ብርቱ ፉክክር እየተደረገበት ይገኛል።

እስካሁን 90.61 በመቶ የድምፅ ቆጠራ የተካሄደ ሲሆን ፕሬዜዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ምንም እንኳን ያገኙት ድምፅ ከ50 በመቶ ቢወርድም ምርጫውን እየመሩ ናቸው።

እስካሁን ባለው ቆጠራ ኤርዶጋን ፤ 49.86 በመቶ ድምፅ ያገኙ ሲሆን ተቀናቃኛቸው ክላችዳሮግሉ 44.38 በመቶ ድምፅ አግኝተዋል።

አንድ ተወዳደሪ ለማሸነፍ በመጀመሪያ ዙር ከ50 በመቶ በላይ ድምጽ ያስፈልገዋል።

ተወዳዳሪዎች 50 በመቶውን ድምፅ ማለፍ ካልቻሉ ፤ ከሁለት ሳምንት በኋላ በሁለተኛ ዙር ምርጫ ይገናኛሉ።
135 views01:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-14 22:53:30 89% ተቆጥሯል!
50.1% ኤርዶጋን እየመራ ይገኛል! ፐርሰንቱ ከ50 ፐርሰንት ከወረደ ከ15 ቀናት በኋላ 2ኛ ዙር ምርጫ ይካሄዳል! አካሄዱ እንደዛ ይመስላል!
163 views19:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-14 22:41:20
Almost 35 % ቆጠራ ይቀራል ኦርዶአን 51.33 % ላይ ሲሆን በተፎካካሪው መካከል ያለውም የቁጥር ልዩንት እየጨመረ ሲሆን በ 3 ሚሊየን ህዝብ እየመራ ይገኛል። ይህ ማለት በዚሁ ከቀጠለ ከ 2ሚሊየን በታች ያልተቆጠረ ህዝብ ሲቀር ማሸነፉን ያረጋግጣል ማለት ነው።
167 views19:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-14 22:08:52
79% ተቆጥሯል። ኦርዶአን 50.5 % አግኝቷል። ቅድም በስህተት 22 ሚለየን ያልኩት መሆን ያለበት 26.9 ሚለየን መሆን ሲኖርበት ከዚህ በኃላ ተጨማሪ 5 ሚለየን ማግኘት አለበት። በዚህ ከቀጠለ ምርጫው ሳይደገም አይቀርም
169 views19:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-14 21:57:44
70.44 % ተቆጥሯል ከዚህ ውሰጥ ኦርዶአን 51. 06% ያገኘ ሲሆን ከጠቅላላው 52.5 ሚለየን መራጭ 19.1 አግኝቷል። ከዚህ በኃላ 22 ሚለየን ከደረሰ ፕሬዚደንት መሆኑን ያረጋግጣል። ስለዚህ የቀረው 2.8 ሚለየን ህዝብ ነው ማለት ነው። መልካም ድል
161 views18:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-14 21:50:44
75% ድምፅ አካባቢ ተቆጥሯል 20.2 ሚለየን ህዝብ የመረጠው ሲሆን ከዚህ በኃላ ከሚቆጠረው 12.5 ሚለየን ድምፅ 1.8ሚለየን የህዝብ ድምፅ ካገኘ በ50+ ድምፅ አሸናፊ ይሆናል ኢንሻአላህ
150 views18:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-14 19:22:58
፨  ከአጠቃላይ ድምፅ 16.2 % ተቆጥሯል
፨ ኤርዶጋን በ 55.46 % ይመራል
፨ ከማል ኪሊችዳሮግሉ በ 38.57 % ይከተላል

ትንቅንቁ እየጋለ ሲሆን የተወሰነ የውጤት መጥበብም ይስተዋላል ። ከተቆጠረው 9.2 ሚሊዮን ህዝብ 5 ሚሊዮኑ ኤርዶጋንን መርጧል ። ይቀጥላል !
157 views16:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ