Get Mystery Box with random crypto!

ፈትህ አባቦራ መስጂድ

የቴሌግራም ቻናል አርማ fethababora — ፈትህ አባቦራ መስጂድ
የቴሌግራም ቻናል አርማ fethababora — ፈትህ አባቦራ መስጂድ
የሰርጥ አድራሻ: @fethababora
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.06K

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 10

2023-04-25 12:04:38 የሙስሊም ልቅና!

ከአቡ ሁረይራ (رضي ﷲ عنه) ተይዞ: ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦

﴿كُلُّ الْمُسْلِمِ عَلَى الْمُسْلِمِ حَرَامٌ ؛ دَمُهُ، وَمَالُهُ، وَعِرْضُهُ﴾

“ሁሉም ሙስሊም በሙስሊም ላይ ደሙን፣ ገንዘቡን፣ ክብሩን መንካት የተከለከለ ነው።”

ሙስሊም ዘግበውታል: 2564



https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
118 views09:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-25 09:47:20
#በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ
#አሱለሳዒ 5 #ሸዋል 1444 ሂ
124 views06:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-25 09:47:03
108 views06:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-25 09:46:46 የሚመለከተው የመንግሥት አካል እና መጅሊስ ለ3 ዓመታት ቸል ያሉት የጉንችሬ ሙስሊም ተማሪዎች ጉዳይ

ሂደቱ እንዲህ ነው...
በደቡብ ክልል ጉራጌ ዞን በእኖር ወረዳ እና በጉንችሬ ከተማ ዙሪያ ባሉ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ከ3 አመታት በላይ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ያለምንምን እክል ኒቃብ ለብሰው በመማር ትምህርታቸውን ሲከታተሉ እንደነበር ይታወቃል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ከ2014 የትምህርት ዘመን ጀምሮ ከዚህ ቀደም ታይቶ በማይታወቅ መልኩ አዲስ ቅርጽና ይዘት ያላቸው እና ሙስሊሙን ከትምህርት ገበታ ለማራቅ በማቀድ ኒቃብ መልበስን መከልከል መነሻ ያደረጉ ችግሮች መከሰት ጀምረዋል።ሙስሊም ተማሪዎች ትምህርታቸውን በትኩረት ተከታትለው ወጤታማ ሆነው ሀገራቸውን እንዳያገለግሉ የሚያደርጉ እርምጃዎች ሲወሰዱ ቆይተዋል። ለአብነትም:-
◎ በ 2015 መጀመሪያ አካባቢ ኒቃብ ለባሽ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች በጥበቃ ኒቃብ ለብሳችሁ መግባት አትችሉም በሚል ከበር እንዲመለሱ እና እንዲገለሉ ተደርጓል። ይህ አልበቃ ብሎ (እገዜ) አካባቢ ኒቃብ ለባሽ ሴት ተማሪዎችን ኒቃብ ለብሳችኋል በሚል ዞን ድረስ በማስመጣት እና ለእስር በመዳረግ እንዲንገላቱ ተደርጓል።
◎በቀን 10/03/2015 ጉንችሬ መሰናዶ ትምህርት ቤት ላይ የሙስሊሞችን ኒቃብ ለብሰው መማርን በሚቃወሙ ሌሎች ተማሪዎች አማካኝነት የቃጠሎ እና የፕላዝማ ንብረት ዝርፊያ ሙከራ ተፈጽሞ ሳለ ምንም እርምጃ ባለመወሰዱ ምክንያት ዳግም በቀን 23/03/2015 የቃጠሎው ወንጀል ሊፈጸም ችሏል። በዚሁ ጉዳይ ላይ ከወላጆች ጋር በተደረገ ውይይት ይህን ወንጀል የፈጸሙት ልጆቻቸው መሆኑን በማመን ኃላፊነት እንደሚወስዱ ቃል ገብተው የነበረ ቢሆንም አስከ አሁኑ ድረስ ምንም መፍትሄ ሳይበጅለት ቀርቷል።
◎በ ጋርባዶ ትምህር ቤት የአካባቢውን ማህበረሰብ ጭምር በመቀስቀስ ገጀራ ይዞ በመውጣት እልቂት ለመፈፀም ሙከራ ተደርጓል።
◎ሙስሊም ወንድ ወጣቶችን በማሳደድ በማሽማቀቅ ከ42 እና 55 ኪ/ሜ በላይ ተወስደው እንዲታሰሩ ቀለብና ልብስ እንዳያገኙ ተደርጓል።
◎በቀን 18/05/2015 ጉንችሬ ከተማ 02 ቀበሌ የሚገኘው አል አቅሳ መስጅድ የቃጠሎ ሙከራ ተድርጎበታል።
◎ከዚህም ባሻገር በደል እየደረሰባቸው ላሉ ተማሪዎች ድጋፍ ያደርግ የነበረው የማህበረሰቡ አካል ከአካባቢው ደንብሮ እንዲጠፋ በልዩ ሃይል ማስፈራራት እንዲሁም በድብደባ ሴቶች እና ሽማግሌዎች እንዲቆስሉ እንዲታሰሩ ተደርጓል።
◎በተጨማሪም ሙስሊሙ ማህበረሰብ ላይ አድማ በማድረግ፣ ለሙስሊም መሸጥም ሆነ መለወጥ በመከከል ሙስሊሙ ማህበረሰብ ላይ አድማ ለማድረግ ተሞክሯል።
◎ምንም እንኳን ከአካባቢ ሽማግሌዎችና ነዋሪዎች ጋር በተደጋጋሚ በተደረገ ውይይት የወረዳውን፣ የዞኑን እና የነዋሪዎቹን ነባራዊ ሁኔታ በማገናዘብ ተማሪዎች በነበሩበት ሁኔታ ኒቃብ ለብሰው እንዲማሩ እና ት/ቤቱም እንዲከፈት ተወስኖ የነበረ ቢሆንም ውሳኔው ተፈጻሚ ሊሆን አልቻለም።
◎ይህ በእንዲህ እንዳለ በጉንችሬ እና በ እገዜ ትምህርት ቤት ከሁሉም ሃይማኖቶች የተውጣጡ ከ 1800 በላይ ተማሪዎች የተመዘገቡ ቢሆንም በአሁኑ ሰዓት በትምህርት ገበታ ላይ ተገኝተው እየተማሩ ያሉት ከ 300 የማይበልጡ ተማሪዎች ብቻ ናቸው። የተቀሩት ኒቃብ ካላወለቃችሁ አትማሩም ስለተባሉ ከትምህርት ገበታ ተገፍተዋል..
በአካባቢው ላይ እየተከሰቱ ያሉትን ችግሮች ለመፍታት መንግሥት እና መጅሊስ እንቅስቃሴ እንዲያደርጉ በተደጋጋሚ የአካባቢው ሙስሊም ነዋሪዎች ያመለከቱ ቢሆንም ጉዳዩ ሳይፈታ ቸል በመባሉ የዛሬውን ክስተት ሊወልዱ ችለዋል።

ኡሰታዝ ነስሩ ኸድር


https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
110 views06:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-25 09:33:30 "ዐብደሏህ ኢብን መስዑድ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) (አንድ ቀን) ዙህርን አምስት ‹‹ረከዓ›› ስገዱ፡፡ (ተከታዮቻቸውም)፡- ‹‹በሶላቱ ላይ ጭማሪ ተደረገን? በማለት ጠየቁ፡፡ ‹‹ምን ሆነ?›› አሉ ነቢዩ፡፡ ‹‹አምስት ‹‹ረከዓ›› እኮ ነው የሰገድነው፡፡›› የሚል ምላሽ አገኙ፡፡ ካሰላመቱ በኋላ ሁለት የ‹‹ሰህው›› (መርሳት) ‹‹ሱጁድ›› አደረጉ፡፡
(ቡኻሪ ዘግበውታል) - ቡኸሪ ዘግቦታ"
==========================================
ይህን ሐዲስ ያገኙውት ከ ኢትዮ ቢላል ሃዲስ አፕ ነዉ ።



https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
99 views06:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-24 20:28:31 «በጉንችሬ:-ሰላም በሚሰበክበት ወቅት ብጥብጥ የሚቸረችሩ አመራሮች ሀይ ሊባሉ ይገባል!!!

2000 የጉንችሬ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ከትምህርት ቤት በግፍ ከተባረሩ ሰነባብቷል።

ይህ እየሆነ ያለው መንግስት ለሰላም ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ባለበት ወቅት ነው።ይህ እየሆነ ያለው መንግስት ለሀገሪቷና ለዜጎቿ በማሰብ ችግሮችን ሁሉ በሰላም ለመፍታት በከፍተኛ ቁርጠኝነት እየሰራ በሚገኝበት ወሳኝ ወቅት ነው!!!ለምን?

ይህ ወቅት ሰላማችንን የምናፀናበት ከመሆኑ አንፃር የሁላችንን ርብርብና ድጋፍን ይሻል።ድጋፍና ርብርባችን የሚገለፀው ሰላም የሆኑ አካባቢዎች ሰላማቸውን በማስቀጠል፤ግጭት ያለባቸው አካባቢዎችን ደግሞ በመንግስታችን እና በተደራዳሪ ወገኖች በኩል ለሰላም የሚደረገውን ድርድር በመደገፍ የሰላም ዘብ መሆናችንን በማሳየት ነው።

በተለይ በየትኛውም ደረጃ የሚገኙ የመንግስት የስራ ኃላፊዎችና አመራሮች ሰላምን ከማፅናት አንፃር ከፍተኛ ሀላፊነት አለባቸው።

ወቅቱ የሚፈልገው ይህ ሆኖ ሳለ በጉራጌ ዞን በጉንችሬ እየሆነ ያለው 2000 (ሁለት ሺ) ሙስሊም ሴት ተማሪዎችን ከትምህርት ቤት የማባረር ከመንግስታችን እና ከህዝባችን የሰላም ፍላጎት አቅጣጫ በተቃራኒ ሰላም የሆነውን አካባቢ ወደ ሁከትና ብጥብጥ እንዲገባ የሚያደርግ/ያደረገ ሴራ ነው።

2000 ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በሀይማኖታቸው የታዘዘውን መጎናፀፊያ ከከፍተኛ 2ኛ ደረጃ እስከ ዩኒቨርሲቲ ድረስ ሲጎናፀፋበት ለአመታት ሲለብሱት እንደነበረ ሁሉ ያን ማድረጋቸው ከትምህርት ገበታቸው እንዲባረሩ ምክንያት ሲሆን እውነተኛ ኦርተዶክሶች ከጎናቸው ይቆማሉ!!!እንጂ ከታች እንደሚታዩት (ጥቂቶች) በደስታ ከግፈኞች ጋር በመሰለፍ (ኦርቶዶክሱን ይወክላሉ ብዬ ባላስብም) ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤታቸው እንዳይገቡ በዚህ መልኩ የህዝብ ትምህርት ቤተ ደጃፍን ዘግታችሁ መቆማችሁ ተገቢ አይደለም።መተጋገዝና መከባበር እንጂ መገፋፋቱ ለሀይማኖታችንም ለሀገራችንም አይጠቅምም።ሁላችንም ቆም ብለን እናስተውል።

የጉራጌ ዞን አስተዳደርና ሰላምና ፀጥታ፣የጉንችሬ ትምህርት ቢሮና አስተዳደር ከ2000 በላይ ሙስሊም ሴት ተማሪዎችን ከትምህርት ገበታቸው ስታባርሩ ምን አስባችሁ ነው???

የመንግስታችንን እና የህዝቡን የሰላም አቅጣጫ ተከትላችሁ ሰላምን ለማፅናት¿ወይስ ሌላ ተልኮ ተቀብላችሁ ሁከትና ብጥብጥ እንዲፈጠር ነው ዓላማችሁ?

ይህ ከሆነ ዓላማችሁ የብልፅግና ሳይሆን ሀገርን የማደኅየት፣ማኀይምነትን የማንሰራፋት ጎዳናንን መርጣችሀልና ሀይ ባይ ያስፈልጋቹሀል።

እየተራመዳችሁበት ያለው ጎዳና ለሰላሙ አጋዥ አለመሆናችሁን ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ በመሆኑ አሳዳሪ መንግስት ካላችሁ በጊዜ ልጓም እንደሚያበጅላችሁ ተስፋ አደርጋለሁ።

ከሁሉ በፊት ግን ችግሩን በሰላም እራሳችሁ ብትፈቱት እናተም ሀገርም ታተርፋለች።»


ሙሐመድ አባተ ከአዲስ አበባ መጅሊስ


https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
156 views17:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-24 17:46:30
በጉንችሬ ከተማ ሙስሊሞች ላይ ጥቃት መሰንዘሩን ተከትሎ ከትላንትና ጀምሮ ግጭት መፈጠሩን የአካባቢው ማኅበረሰብ ለሀሩን ሚዲያ ገለጸ
...
ሀሩን ሚዲያ፥ ሚያዝያ 16/2015
...
በጉንችሬ ከተማ ሙስሊሞች ላይ ከትላንት ማታ ምሽት ጀምሮ ጥቃት መሰንዘሩን የአካባቢው ማኅበረሰብ ለሀሩን ሚዲያ ገለጸ። እስካሁን ከ6 በላይ ሙስሊሞች ጉዳት ደርሶባቸው ህክምና ማግኘታቸው የተገለጸ ሲሆን ከጥቃቱ በኃላ ሁኔታው ተባብሶ ወደ ግጭት መሸጋገሩን የአካባቢው ማኅበረሰብ ገልጾልናል። በዚህም ጥቃቱን ከሰነዘሩ ሰዎችም 3 ሰው ላይ ጉዳት መድረሱንና ህክምና ተደርጎላቸው መመለሳቸው ታውቋል።
...
ጉዳዩን ፌዴራል ፖሊስ ካረጋጋ በኃላ ዛሬ ጠዋት አንዳንድ ጽንፈኛ አካላት የመሳርያ ጥቃት በመክፈታቸው ሳቢያ እንደገና ግጭት መቀስቀሱን የገለጹልን ነዋሪዎች ህዝበ ሙስሊሙ ጥቃቱን ለመመከት ሰልፍ በማድረግ ላይ በነበረበት ወቅት ፌዴራል ፖሊስ ሰልፉን መበተኑንና የተወሰኑ ወንድሞችን ማሰሩን ገልጸውልናል። አሁን ላይ ውይይት እየተደረገ ሲሆን ከተማው መረጋጋቱ ተገልጿል። በጥቃቱ በርካታ ንብረት መውደሙ የታወቀ ሲሆን በቤተ እምነት ላይ ግን ጥቃት ደርሷል በሚል የሚናፈሰው ወሬ ሀሰት መሆኑን አስተያየት ሰጭዎቻችን ገልጸዋል።
..
ሀሩን ሚዲያ



https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
170 views14:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-23 21:22:25 ከዝንግዎች ላለመሆን…

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦

﴿من قرأ عشرَ آياتٍ في ليلةٍ لم يُكتَبْ من الغافلينَ.﴾


“በሌሊት (በምሽት) አስር የቁርዓን አንቀፆችን ያነበበ ከዝንግዎች ተደርጎ አይመዘገብም።”

ሲልሲለቱ አሶሂሃ: 2/242


https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
63 views18:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-23 14:08:47
ዑርዋህ ኢብኑ ሙሐመድ በጊዜው የኡመያዊያን ኸሊፋ ሱለይማን ኢብኑ ዐብዲል መሊክ ለየመን አስተዳዳሪ ተደርጎ የተሾመ አሚር ነበር። የመን እንደደረሰም ነዋሪዎቿን ሰበሰበና እንዲህ አላቸው ፦

«የየመን ሰዎች ሆይ! ይህ መጓጓዥያ ፈረሴ ነው ፣ እነዚህ ደግሞ ቀስቴ፣ ሰይፌና ሙስሀፌ (ቁርኣን) ናቸው። ከነዚህ ውጭ ከየመን ይዤ ከወጣሁ ሌባ ነኝ ማለት ነው»

ሶስት ኸሊፋዎች ሲፈራረቁ ሹመቱን እያፀደቁለት ለ20 አመታት የመንን አስተዳደረ።በመጨረሻም ሂሻም ኢብኑ ዐብዲልመሊክ ከቦታው እንዲነሳ አደረገው።20 አመታት ያስተዳደራትን የመን ለቆ ሲወጣ ሰይፉን፣ቀስቱንና ሙስሐፉን ብቻ ይዞ ነበር የወጣው።

ታላቅነትን የሰሩት በዚህ መልክ ነበር!

እርሱም ልጁም ታዋቂና ታማኝ የሐዲስ አስተላላፊዎች ነበሩ። አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸው ።

አከስማዒል ኑሩ



https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
106 viewsedited  11:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-23 09:05:04
109 views06:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ