Get Mystery Box with random crypto!

ፈትህ አባቦራ መስጂድ

የቴሌግራም ቻናል አርማ fethababora — ፈትህ አባቦራ መስጂድ
የቴሌግራም ቻናል አርማ fethababora — ፈትህ አባቦራ መስጂድ
የሰርጥ አድራሻ: @fethababora
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.06K

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2023-06-07 21:50:53
በዛሬው እለት በየኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼህ ሐጂ ኢብራሂም የተመራ ልዑክ ከኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት በአቶ ሽመልስ አብዲሳ የተመራ የኦሮሚ ክልል የሥራ ሀላፊዎች ጋር በሸገር ከተማ ስለፈረሱት መስጂዶች ጉዳይ ከቀኑ 9:00 እስክ ምሽት 2:00 ሰዓት ድረስ አምስት ሰዓታት የፈጀ ሰፊ ዉይይት አድርገናል። በዉይይቱ ማጠቃለያ ላይ በተደረሰባቸው ነጥቦች ላይ በነገው እለት ጠዋት 4:00 ሰዓት ላይ በፌደራል እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ጋዜጣዊ መግለጫ ይሰጣል። መግለጫውን ለመዘገብ ሁሉም ሚዲያዎች በስፍራው እንድትገኙ ጥሪ ተላልፏል።

ustaz ahmedin jebel

https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
179 viewsedited  18:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-07 17:52:26
172 views14:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-07 17:52:11 በአላህ ስም እጅግ በጣም አዛኝ እጅግ በጣም ሩህሩህ በሆነው
በኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች ላይ እየደረሰ ያለውን ግድያ እና የእምነት ቤቶችን
የማውደም ሂደት በመቃወም በአውሮፓ ካሉ ኢትዮጵያዊያን ሙስሊም ማህበራት
የተሰጠ የአቋም መግለጫ
በአስቸኳይ የሚወጣ
ጁን 06፣ 2023
በተለያዩ የአውሮፓ አገሮች የምንገኝ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ-ኢትዮጲያ ሙስሊሞች በትውልድ
አገራችን ያለውን ነባራዊ ሁኔታ አስመልክቶ ውይይት በማድረግ የገመገምን ሲሆን በተለይም መንግስት
ከባለፈው ረመዳን (አፕሪል 2023) ወር መግቢያ ጀምሮ በርካታ የህብረተሰብ ክፍሎችን መጠለያ አልባ
ያደረገ የቤቶች ፈረሳ ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ የእስልምና እምነትን እና የእምነቱ ባልተቤቶችን ክብር
ባራከሰ መልኩ መስጂዶችን እና ቅዱስ መጻህፍቶቻችንን ያወደመበት ሂደት እጅጉን አዛንኖናልም፤
አስቆጥቶናልም።
መንግስት በተዋረድ እስከ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ድረስ ያሉ የሙስሊሙ
ወካይ ድርጅቶች ችግሩን በውይይት ለመፍታት ያቀረቡትን ተከታታይ አቤቱታ ትኩረት በመንፈግ
ባለፉት ሁለት ጁመዓዎች ላይ ያለምንም ትንኮሳ የመንግስት የጸጥታ ሃይሎች በአንዋር መስጊድ
በተሰባሰቡ ምዕመናን ላይ ባካሄዱት የሽብር ዘመቻ የበርካታ ወጣቶች ህይወት ተቀጥፏል። በዚህም
የአገራችን እና የህዝባችን እጣ ፈንታ ከመቸውም በላይ አሳሳቢ ሁኔታ ላይ መድረሱን ተገንዝበናል።
ከዛሬ አምስት አመት ገደማ አገኘን ላልነው ለውጥ ሙስሊሙ ህብረተሰብ ያደረገው እልክ አስጨራሽ
ትግል መሸጋጋገሪያ ሆኖ እንዳገለገለ የሚካድ አይደለም። ሆኖም ግን ለዝህባችን ሰላምን፣ እድገትን እና
ነጻነትን ያመጣል ብለን ያመነው ሂደት ራሱ ለዜጎች ኑሮ መመሳቀል እና መሰረታዊ ለሆነው ሰላም ማጣት
ምክንያት መሆን የለበትም ብለን እናምናለን። ለልማት የሚደረግ የትኛውም እንቅስቃሴ እና የሚወሰድ
እርምጃ ቅድሚያ ለዜጎች ደህንነት እና መብት መከበር ሊሰጥ ይገባል። በነጻነት የማምለክ እና
እምነታቸውን ማደራጀትና ማስፋፋት ደግሞ የዚህ መሰረታዊ የዜጎች መብት አካል ነው። ስለዚህ
በየትኛውም መልኩ በልማት ስም መስጂዶችን በማን አለብኝነት እስከ ማፍረስ የተሄደበት አካሄድና
የዜጎችን የማምለክና በሰላም የመቃወም መብትን በመጣስ ዉድ ህይወትን እስከመቅጠፍ የተወሰደው
እርምጃ ፍጹም ተቀባይነት የሌለው ነው።ስለሆነም
1. በልማት ስም በሸገር ከተማ እየተደረገ ያለው የመስጂድ ፈረሳ በአስቸኳይ እንዲቆም።
2. መንግስት ይህን አይነት ዜጎችን ከፍተኛ ለሆነ ምስቅልቅል የዳረገ እርምጃውን ቆም ብሎ እነዲያጤንና
አስፈላጊውን ማስተካከያ እንዲያደርግ።
3. የሸገር ከተማ አስተዳደር የእምነት ቦታዎችን እስከማውደም የሄዴበትን ሂደት መንግስት
ከሚመለከታቸው የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤቶች ጋር በመተባበር እንዲመረምር እና ዘለቄታ
ያለው የመፍትሄ አርምጃዎችን በአስቸኳይ እንዲወስድ።

4. በአንዋር መስጊድ ተሰብስበው የመስጊድ ማፍረስ ዘመቻውን ተቃውመዋል በሚል መንግስት
ለወሰደው የህይወት መጥፋት፣ የአካል መጉደል እና የንብረት መውደም በአጠቃላይ በሙስሊሙ
ህብረተሰብ ላይ ለከፈተው የሽብር ዘመቻ ሃላፊነቱን እንዲወስድ። በድርጊቱ ላይ ተሳታፊ አካላትን
በመለየት እርምጃ እንዲወስድ። በእስር ላይ የሚገኙ ንጹሃንን በአስቸኳይ እንዲለቅ።
5. መንግስት የእምነት ጉዳይ የዜጎች ቀይ መስመር መሆኑን በመገንዘብ ወደፊት በልማትም ይሁን ለሌላ
ጉዳይ ሃይማኖትን እና የእምነት ቦታዎችን የሚመለከት እርምጃ ከመውሰዱ በፊት ከሚመለከታቸው
የእምነቱ ተከታዮችና ድርጅቶቻቸው ጋር መግባባት ላይ እንዲደርስ እናሳስባለን።
ለአገራችን ልማትና እድገት ያለን ቀና አስተሳሠብ፣ ለስኬቱም እና ለቀጣይነቱ የምናደርገው ርብርብ
እንዳለ ሆኖ በእምነታችን ላይ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ የሚደረግ የትኛውም እርምጃ ቀይ መስመራችን
መሆኑን እየገለጽን አሁን ያለውን የመንግስት አስፈሪ እና አገራችንን እና ህዝባችንን ልንወጣ
ወደማንችለው አሮንቃ ዉስጥ የሚከት ሂደት ይቀለበስ ዘንድ የሚጠበቅብንን ሃላፊነት ለመወጣት
ዝግጁነታችንን እንገልጻለን። ለዚሁም ያግዝ ዘንድ ከሁሉም አገር ማህበራት የተውጣጣ ልዩ ኮሚቴ
በማቋቋም ክትትል የምናደርግ መሆኑንም ጨምረን እናሳውቃለን።
አላሁ (ሱወተ) አገራችንንና ህዝባችንን ይጠብቅልን።
“እርሱ (አላህ) ረዳታችን ነው፤ በአላህ ላይ ምዕመናን ይመኩ” (አል - ተውባ 09፡51)
አላሁ አክበር!
ፈራሚ ሙስሊሞች ማህበራት
• ኢቅራእ ተቋም - ዩናይትክ ኪንደም
• ሰላም ኢትዮ-ጀርመን አንድነት ማህበር
• ነጃሺ የኢትይጵያዊያን ሙስሊሞች ማህበር በስዊድን
• ሰንሰለት ፋውንደሽን - ኔዘርላንድ
• ሉቅማን ኢትዮጵያ - ቤልጂየም
• ኢትይጵያዊያን ሙስሊሞች ማህበር በፊንላንድ
• ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች ማህበር በኖርዌይ
• ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች ማህበር በስዊዘርላንድ
• ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች ማህበር በአውስትሪያ



https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
171 views14:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-07 14:36:27
155 views11:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-07 14:36:04 የአዲስ አበበ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት
በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በኢማሞች ህብረት የተሰጠ የአቋም መግለጫ

በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በሸገር ከተማ እየተፈፀመ የሚገኘዉን የመስጅድ ፈረሳ በመቃወም በአዲስ አበባ ከተማ በታላቁ አንዋር እና ኑር መስጅዶች ህዝበ-ሙስሊሙ ድምፅ በማሰማቱ ምክንያት በተከሰተዉ ችግር በሰዉ ሕይወት እና አካል ላይ ጉዳት ደርሷል፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘ ብዙ ዜጎች በህግ ጥላ ስር ይገኛሉ፡፡
በሸገር ከተማ እየተካሄደ የሚገኘዉ የመስጆዶች ፈረሳ ፍፁም ተገቢ ባለመሆኑ የምናወግዝ መሆኑን እየገለፅን የሚመለከተው አካል አፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጥ የኢማሞች ሀብረት ጥያቄውን ያቀርባል፣
በተጨማሪም የኢማሞች ሀብረት በሸገር ከተማ እየተፈፀመ የሚገኘዉን የመስጅድ ፈረሳ እና ከዚህ ጋር በተያያዘ በምዕመናን ላይ የተወሰደዉን ተገቢ ያልሆነ እርምጃ በፅኑ እያወገዘ የሚከተሉትን ባለ 5 ነጥብ የአቋም መግለጫ አዉጥቷል፡፡
1. ከዛሬ ቀን ጀምሮ እስከ ዙልቂዕዳ ወር መጨረሻ ድረስ በሁሉም መስጅዶች ቁኑት እና ዱዓ አንዲደረግ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፣
2. በሁሉም መስጂዶች የፊታችን ጁሙዓ የኩጥባ ይዘት በሠላም፣ በአንድነት እና በሰብር ላይ እንዲያተኩር እና ህብረተሰባችን ይበልጥ በሚረዳው በአማርኛ ቋንቋ ዳዕዋ እንዲደረግ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡
3. በነገዉ እለት ሐሙስ ዙልቂዕዳ 19 ፤ 1444 ዓ.ሂ ሙስሊሙ ማህበረሰብ በመፆም፤ በሰደቃ፣ በዱዓ እና በኢስቲግፋር ወደ አላህ በመቃረብ እና አላህ የተፈጠረውን ችግር እንዲያነሳልን እንዲለምን ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡
4. በተፈጠረዉ ችግር ሕይወታቸዉ ያለፈ እና የተጎዱ ቤተሰቦችን ሙስሊሙ ማህበረስብ የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ባዘጋጀው የባንክ ቁጥሮች እንዲረዳ ጥሪያችንን እያስተላለፍን፡፡
5. በመጨረሻም የጁምዓ ሰላታችን በሠላም ተሰግዶ አንዲጠናቀቅ እና ሙስሊሙ ማህበረሰብ በሰላም ወደ ቤቱ እንዲመለስ ጥሪያችንን እያቀረብን አላህ ሱብሃነሁ ወተዓላ የመጣውን በላእ እንዲያነሳልን እና እንዲመልስልን እንለምነዋለን፣

አላሁ አክበር !!!



https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
159 viewsedited  11:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-16 19:33:28
ሀሜት
በኡስታዝ አቡ ሀይደር አገላለፅ
አጠር ያለች አስተማሪ ቪዲዮ
78 views16:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-16 13:34:58 የዚህች አለም ደስታ…

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦

﴿ثلاثُ خِصالٍ من سعادَةِ المرْءِ المسلِمِ في الدنيا: الجارُ الصالِحُ، والمسْكَنُ الواسِعُ، والمركَبُ الهَنِيءُ.﴾

“ሶስት ሙስሊም የሆነ በዚህኛው አለም ደስታን ከሚያገኝበት ነገሮች (ባህሪያት) ውስጥ ነው። እነሱም፦ እነሱም፦ መልካም ጎረቤት፣ ሰፋ ያለ ቤትና ጥሩ መመጎጎዣ ናቸው።”

ሶሂህ አልጃሚ: 3029



https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
97 views10:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-16 06:26:53
#በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ
#አሱለሳዒ 26 #ሸዋል 1444 ሂ
112 views03:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-16 06:21:46 "ኢብን መስዑድ (ረ.ዐ) እንዳወሱት አንድ ግለሰብ አንዲት ሴትን ሳመ፤ (ሚስቱ አይደለችም) ወደ ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) በመምጣትም የሰራውን ገለጻላቸው (በፈጸመው ድርጊት በመጸጸት)፡፡ አላህ (ሱ.ወ) ይህንን አንቀጽ አወረደ፡- ‹‹ሶላትንም በቀን ጫፎች (ጥዋትና ከቀትር በኋላ)፤ ከሌሊትም ክፍሎች ፈጽም፤ መልካም ሥራዎች ኃጢአቶችን ያስወግዳሉና፤ ....›› (11፡114) ሰውየውም ጠየቀ፡- ‹‹የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ይህ ትእዛዝ ለኔ ብቻ ነውን?›› (ተመሳሳይ ጥፋት ለሚፈጽሙ) መላው ህዝቦቼ ነው፡፡›› በማለት መለሱ፡፡
(ቡኻሪ ዘግበውታል) - ቡኸሪ ዘግቦታ"
==========================================
ይህን ሐዲስ ያገኙውት ከ ኢትዮ ቢላል ሃዲስ አፕ ነዉ ።



https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
103 views03:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-15 11:38:56 #ሐጅ!

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦

﴿الحَجُّ المَبْرُورُ ليسَ له جَزاءٌ إلّا الجَنَّةُ﴾

“ከወንጀል የራቀና ተቀባይነት ያለው ሐጅ (አል-ሐጅ አል-መብሩር) ምንዳው ጀነት ቢሆን እንጂ ሌላ አይደለም፡፡”

 ቡኻሪ (1773) ሙስሊም (1349) ዘግበውታል



https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
126 views08:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ