Get Mystery Box with random crypto!

ፈትህ አባቦራ መስጂድ

የቴሌግራም ቻናል አርማ fethababora — ፈትህ አባቦራ መስጂድ
የቴሌግራም ቻናል አርማ fethababora — ፈትህ አባቦራ መስጂድ
የሰርጥ አድራሻ: @fethababora
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.06K

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 56

2023-01-31 21:45:11 የጉራጌው ይለያል
==============
ጉንችሬ ላይ ያለው ጽንፈኝነት ጎጃምና ጎንደር ላይ ያለውን የሚያስንቅ እየሆነ ነው።

መጀመሪያ እነርሱ ኒቃብና ጂልባብ ከተፈቀደላቸው ለኛም ነጠላ ለብሰንና የሞኣ አንበሳ ልሙጡን ባንድራ አሠርተን እንድንገባ ይፈቀድልን አሉ። አላማቸው ይሄማ አይፈቀድላችሁም፤ በቃ እነርሱም እናንተም መልበስ የለባችሁም ተብለው የሚከለከሉ መስሏቸው ነበር። ግን ተፈቀደላቸው። በዚህ አካሄድ እኩይ አላማቸውን ማሳካት ስላልቻሉ ጂልባብና ኒቃብ ከለበሱ ሙስሊሞች ጋር አንማርም ብለው ክላሱን ለቀው ወጡ።

ይህ ቪድዮ ነጠላ ለብሰው ክላሱን ለቀው እየተሳደቡ ሲወጡ የሚያሳይ ነው።


ይሄው አሁን ላይ የክልሉ፣ የዞኑና የወረዳው አስተዳደር ደግፏቸው ከ90% በላይ የሆነውን የት/ቤቱን ሙስሊም ተማሪ ከትምህርት አባረው እነርሱ ብቻቸውን እየተማሩ ይገኛሉ። ጭራሽ ቀስ በቀስ መስጅድ ወደማቃጠል ሙከራም አደጉ። ቀጣይ ምን እንደሚያደርጉ አብረን የምናየው ይሆናል። ከፌዴራል እስከ ክልል ያለ የመንግስት አካል እስካሁን በዝምታ ላይ ነው። ምን እስከሚፈጠር እንደሚጠብቅ ማወቅ አልተቻለም።

እጅግ በጣም አሳፋሪ የድንቁርናና የጽን'ፈኝነት ጥግ!

አሁንም ቢሆን የሚመለከተው የመንግስት አካል ቸልተኝነቱን ወደ ጎን በመተው ከሙስሊሞች የጸዳች ጉራጌን ለመመስረት ያለመ የሚመስለውን አደገኛ የጠርዘኝነት አካሄድ ወደ ሌሎች የሃገሪቱ ክፍሎች ሳይዛመት በጊዜ ሊቀጨው ይገባል። ሳይቃጠል በቅጠል!


ሙራድ ታደሰ

https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
137 viewsedited  18:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-31 21:44:23 የጉንችሬ ፅንፈኞች «የሂስድ ተቃውሞ» ሲያደርጉ።
ሰው እንዴት «ይከልከሉልኝ» ብሎ ያምፃል።
በነገራችን ላይ ከ800 ሙስሊም ተማሪ በላይ ከትምህር ተፈናቅሏል። በርካታ ሙስሊሞች ታስረዋል። ፅንፈኛው ኃይል ከአክቲቪስትም ከባለስልጣንም የተቀናጀ ኔት ወርክ እንዳለው እስር ሸሽተው የመጡት ወንድሞች ምስክር ናቸው።
የጉራጌ ሙስሊም ሆይ እንዴት ነህ?
ለፖለቲካ ብለህ ለህቶችህ ስቃይ ለወንድሞችህ መገፋት ድምፅ የማትሆነው ጉራጌ ሙስሊም ሆይ ሰላም ነህ ወይ?
114 views18:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-31 21:11:28
121 views18:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-31 21:08:53 እውነታ 1

በወለድ ነፃ የባንክ ሲስተም የሀገራችን ባንኮች እስካሁን ወደ 170 ቢሊዮን ብር ሰብስበዋል ። ከዚህ ውስጥ ዘምዘሜ ባንክና ሂጅራ ባንክ የሰበሰቡት ገንዘብ 2 % የሚሆነውን ብቻ ነው ። አስቡት ሙስሊሙ ማህበረሰብ በራሱ ባንኮች ውስጥ የሚያስቀምጠው ሁለት ፐርሰንቱን ብቻ ነው ። ያውም ከወለድ ነፃ የሚያስቀምጡትን ብቻ ካን ማለት ነው ።በወለድ የሚያስቀምጡትንም ሙስሊሞች ከግምት ውስጥ ካስገባን ደግሞ 1 % እንኳ ላይሞላ ይችላል ። ይህ ክሽፈት ነው !

እውነታ 2

አቢሲኒያ ባንክ ባለፉት አራት ወራት ወይንም በሩብ አመቱ ከ 3 ቢሊዮን ብር በላይ በወለድ ነፃ ሰብስቧል ። ይህ አቢሲኒያ በ አራት ወር ብቻ ከሙስሊሙ የሰበሰበው ገንዘብ የሂጅራ ባንክ ከተመሰረተ ጀምሮ ከሰበሰበው ከሁለት እጥፍ በላይ ሲበልጥ ዘምዘም ከሰበሰበው ጋር ደግሞ እኩል መጠን አለው ።

እውነታ 3

የሂጅራ ባንክና የዘምዘም ባንክ አጠቃላይ ድምር የደንበኞች ብዛት ከነርሱ ሗላ ከተመሰረተው ከአማራ ባንክ የደንበኞች ብዛት አይበልጥም ። ያ ማለት የዘምዘምና ሂጅራ ባንክ ደንበኞች ቢደመሩ የአማራ ባንክ ደንበኞች ብዛትን አይበልጡም ወይንም ያንሳሉ !!

እውነታ 3

አማራ ባንክ የሰበሰበው የገንዘብ መጠን ዘምዘምና ሂጅራ የሰበሰቡት የገንዘብ መጠን አንድ ላይ ቢደመር ራሱ በሁለት እጥፍ ይበልጣል ። የሁለቱ ባንኮች የድፖሲት መጠን አንድ ላይ ቢደመር የአማራ ባንክ ድፖዚትን ግማሹን አያክልም !!

ይሄ ኢስላማዊ ባንክ ካልተመሰረተልኝ እያለ ሲጮህ ለነበረው ሙስሊሙ ማህበረሰብ ማፈሪያ ነው ።

ህዝባችን ሲከለክሉት መጮህ እንጅ ሲያገኝ መጠቀም አይችልበትም ። አሁን ዘምዘምና ሂጅራን መንግስት ሊዘጋቸው ነው ቢሉ " ዋ ኢስላማ " እያለ መንገድ ካልዘጋሁ ህንፃ ካልወገርኩ ይላል ። ግና ለመጠቀም ያለው ወኔ የሟሸሸ ነው ።

የተቋምን ጥቅም የተረዳ ኡማ የሚኖረን መቼ ይሆን !??

Seid mohammed alhabeshi




https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
205 views18:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-31 17:45:24
የአፋር ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት ከመጪው ሳምንት አጋማሽ አንስቶ አገልግሎቱን የሚሰጠው በአፋርኛ ቋንቋ መሆኑን አስታወቀ

አምባ ዲጂታል፤ ማክሰኞ ጥር 23፣ 2015 ― የአፋር ክልላዊ መንግሥት ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከመጪው ሳምንት ረቡዕ የካቲት 1፣ 2015 አንስቶ አገልግሎት የምሰጠው በአፋርኛ ቋንቋ መሆኑን እወቁት ብሏል፡፡ 

የአፋር ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት፤ ለተገልጋዮች በለጠፈው ማስታወቂያ እንደገለጸው፤ ከቀጣዩ ሳምንት አጋማሽ አንስቶ አገልግሎቱን በአፋር ቋንቋ መስጠት የሚጀምረው ‹‹ሕገ መንግሥቱ ባረጋገጠው መሠረት ክልሎች በራሳቸው የሥራ ቋንቋ እንዲሰሩ በሰጠው መብት መሠረት›› እንደሆነ አስታውቋል፡፡ 

ከዚህ ቀደም አገልግሎቱን በአማርኛ ቋንቋ ሲሰጥ የቆየው ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ፤ ለፍርድ ቤቱ ዳኞች ሥልጠና በማዘጋጀት ፍ/ቤቶች ሥራቸውን በአፋርኛ ቋንቋ እንዲጀምሩ ውሳኔ አሳልፈፏል ነው የተባለው፡፡ 

የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይህንኑ ተከትሎ ተገልጋዮች የፍርድ ቤት ቅሬታ፣ ቃለ መሐላ፣ ማመልከቻ፣ የእግድ ጥያቄ እና የይፈጸምልኝ ጥያቄ ይዘው ሲቀርቡ በአፋርኛ አዘጋጅተው ማቅረብ እንዳለባቸው ገልጧል፡፡



https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
141 viewsedited  14:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-18 11:20:25 የሀረሪ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ  ም/ቤት 2ተኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ የአንድ መቶ ሚሊዮን ብር በጀት በማፅደቅ ተጠናቀቀ።
...
ሀሩን ሚዲያ፥ ጥር 10/2015
...
በሀርላ ሆቴል ሲካሄድ የነበረው  የሀረሪ  ክልላዊ መንግስት እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት 2ተኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ  አንድ መቶ ሚሊዮን ብር አመታዊ በጀት በማፅደቅ ተጠናቋል። በጉባዔው ረቂቅ የክልሉ መጅሊስ ሕግ  ቀርቦ በጉባዔው አባላት ሰፊ  ውይይት ተደርጎበት የፀደቀ ሲሆን በቀጣይም የክልሉ  መጅሊስ ሕግ ሆኖ  ያገለግላል ።
..
ጉባዔው  የሶስት የኦዲትና ቁጥጥር አባትን ሹመት ያፀደቀ ሲሆን  በተጨማሪ የሀረሪ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ  ምክር ቤትን እንዲያገለግሉ ለሀጂ መሀመድ ሀሺም ፣ ለአባገዳ አህመድ ዩሱፍ ፣ ለሀጂ ነስረዲን አሊ ፣ ለሼይኽ መሀመድ ቃዲ እና ለሀጂ አህመድ ኢብሮሽ  የግልግል ሸንጎ አባትን ሹመት አፅድቋል።
...
የሀረሪ ብሔራዊ  ክልላዊ  መንግስት  የእስልምና ምክር ቤቱን  ስራ  ዘመኑን የዋጀ እንዲሆን  እና የክልሉን ሙስሊም ተጠቃሚነት  ለማረጋገጥ   11 አባላት ያሉት የአማካሪዎች ቦርድ አባላትን ማለትም፦

1ኛ.አቶ ተወለዳ አብዶሽ
2ኛ.አቶ ያሲን አብዱላሂ
3ኛ.ዶ/ር አብዱላሂ ወዚር
4ኛ. ኡስታዝ ረመዳን ተማም
5ኛ.አቶ ሀምዛ ሽመልስ
6ኛ.አቶ መሀመድ አብዱረህማን
7ኛ. ሼህ አብዱረህማን መሀመድ
8ኛ. አቶ ሙስጠፋ መሀመድ
9ኛ.አቶ ፊላ አህመድ
10ኛ.ሼህ አልዪ መሀመድ
11ኛ.ሼህ ጀማል መሀመድን በመምረጥ ጉባዔውን  አጠናቋል።

መረጃው የኢ/እስ/ጉ/ጠ/ም/ቤት ነው።

ሀሩን ሚዲያ



https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
22 views08:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-18 10:31:10 #ውሸትን ተጠንቀቁ!

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
﴿يا مَعشرَ التُّجّارِ ! إياكُم والكذبَ﴾

“እናንተ ነጋዴዎች ሆይ! ውሸትን ተጠንቀቁ!”

ሲልሲለቱ አሶሂሃ: 1793



https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
34 views07:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-18 07:03:52
#በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ
#አልዓርቢዓዐ 25 #ጀማዱል አኽር 1444 ሂ


https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
59 viewsedited  04:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-18 07:03:29 "ረሱል(ሰ.ዐ.ወ)<የተራበን መግብ የተጠማን አጠጣ ሰዎች መልካም እንዲሰሩና ከመጥፎም እንዲከለከሉ እዘዝ ይህን
ማድረግ ካልቻልክ ምላስህ መልካም ይናገር አለዝያ ዝም በል ! >>
(ቡኻሪ ዘግበውታል) - ቡኸሪ ዘግቦታ"
==========================================
ይህን ሐዲስ ያገኙውት ከ ኢትዮ ቢላል ሃዲስ አፕ ነዉ ።



https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
54 views04:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-17 21:10:45 ከሰሞኑ ሙስሊሞች ላይ ጥቃት በደረሰበት የሀድያ ዞን ጭንጎ ወረዳ ታላቅ ኮንፈረንስ በዛሬው እለት መካሔዱ ተገለጸ
...
ሀሩን ሚዲያ፥ ጥር 9/2015
...
❐  በኮንፈረሱ ከ4,000 እስከ 5,000 የሚሆን ሰው ተገኝተዋል ተብሎ ይገመታል።

❐  ከክልል እስከ ወረዳ ድረስ ያሉ የመንግስት መስሪያ ቤትችን የሚወክሉ ልዑካንም ጉዳቱን ለመታዘብ በቦታው ተገኝተው ነበር።

❐  ሀሩን ሚዲያ ክስተቱን ከመነሻው ጀምሮ የተከታተለ ሲሆን ሙሉውን ፕሮግራም ወደናንተ የሚያደርስ ይሆናል።

ከሰሞኑ ሙስሊሞች ላይ ጥቃት በደረሰበት የሀድያ ዞን ጭንጎ ወረዳ ታላቅ ኮንፈረንስ በዛሬው እለት መካሔዱ ተገለጸ። ጉዳዩን በተመለከተ የፌዴራል መጅሊስ ልዑካን ቡድን አባላት በቦታው በመገኘት ሲከታተሉ የቆዩ ሲሆን በዛሬው እለት በቦታው ታላቅ ኮንፈረንስ በማካሔድ ከህዝቡ ጋር ውይይት አድርገዋል። በውይይቱም ህዝቡ የደረሰበትን በደልና ግፍ ለልዑካን ቡድኑ እና ለመንግስት አካላት የገለጸ ሲሆን አጥፊዎቹ ላይ ተመጣጣኝ እርምጃ እንዲወሰድም ጠይቋል።
...
በኮንፈረንሱ ከመንግስት በኩል የተገኙ የዞኑ ፀጥታ ቢሮ ሀላፊ ሳምኤል ሽጉጤ፣
የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ፣ የክልሉ ፀጥታ ቢሮ የግጭት አፈታት ባለሙያ እንዲሁም የወረዳው ፀጥታ ሀላፊ የተገኙ ሲሆን በመጅሊስ በኩል ከፌዴራል መጅሊስ ልዑካን በተጨማሪ የክልሉ እስልምና ጉዳይ ከፍተኛ ም/ቤት፣ የዞኑ መጅሊስ ሰብሳቢና ስራ አስፈፃሚወች እንዲሁም የሀገር ሸማግሌዎች ተገኝተዋል።
...
በውይይቱ ላይ የተገኙት የመንግስት ኃላፊዎች አስፈላጊውን ማጣራት ከተደረገ በኋላ በአጥፊዎቹ ላይ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ የገለጹ ሲሆን የክልሉ እና የዞኑ ከፍተኛ የመንግስት አመራሮች የሀይማኖት ጉባኤ ተወካዮች የፌደራል እና የክልል መጅሊስ ተወካዮች የሚያደረጉት ውይይት እስከ ነገ እንደሚቀጥል ለማወቅ ተችሏል። በውይይታቸው  መጨረሻ በጋራ መግለጫ እንደሚሰጡ ለሀሩን ሚዲያ ገልጸዋል።
...
ሀሩን ሚዲያ



https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
https://t.me/fethababora
92 views18:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ