Get Mystery Box with random crypto!

Ethio Fm 107.8

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiofm107dot8 — Ethio Fm 107.8 E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiofm107dot8 — Ethio Fm 107.8
የሰርጥ አድራሻ: @ethiofm107dot8
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.32K
የሰርጥ መግለጫ

በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

3

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 99

2022-08-30 18:46:47
በ5ተኛው ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ በተከታታይ ጨዋታዎች ከኋላ እየተነሱ ነጥብ መሰብሰብ ችለው የነበሩት ቅዱሳኑ ጉዞዋቸው በቀይ ሰይጣኖቹ ተገትቷል በዛሬውም እለት በቅዱሱ መድረካቸው በተከታታይ ጨዋታዎች ቀይ ካርድን እንደገጸበረከት እየተቀበሉ ያሉትን ሰማያዊዎቹን ቼልሲዎች ያስተናግዳሉ ምን እንጠብቅ?

ራሂም ስተርሊንግ በ3ተኛ ክለብ ቆይታውም እንደ ቀደሙት ያሸበርቅ ዘንድ በሰማያዊዎቹ ቤት ጉዞውን አሀዱ ብሏል ተጫዋች ቢጎድልባቸውም ያለ አሰልጣኝ ቢገቡም በዘንድሮው የውድድር ዘመን የተሻለውን ቼልሲን የተመለከትነው በኪንግ ፓወሩ ሁለተኛ አጋማሽ ነበር ከ3፡00 ጀምሮ ሬዲዮኖቻችሁን በ107.8 ላይ ጠምዝዙ!!

በቲፎዞ ግብግብ ቼልሲን ወግኖ የሚመጣውን ደጋፊ ውረዱበት!
ሽሙጥ፣ ፈተላ፣ ብሽሽቅ በስፋት ይፈቀዳል ከፉትቦል ላይቭ ጋር አብረን እንመልከት!
2.1K viewsedited  15:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 14:37:45

2.5K views11:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 14:37:21 አሸዋ ቴክኖሎጂ ሶሊዩሽን የአቅርቦት እና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ጀመረ

አሸዋ ቴክኖሎጂ ሶሊዩሽንስ አ.ማ ከተሰማራባቸው አስራ አንድ የቴክኖሎጂ ዘርፎች መካከል በድረገጹ የሚሰጠውን የምርት አቅርቦት እና ሎጀስቲክስ አገልግሎት በዛሬው እለት አስጀምሯል፡፡

ዲጂታል ኢትዮጲያ 2025 ራዕይን ተግባራዊ ለማድረግ የሚደረገውን የመንግስት ጥረት እያገዘ መሆኑን የድርጅቱ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ዳንኤል በቀለ ተናግረዋል፡፡

አሸዋ ቴክኖሎጂ ሶሊዩሽንስ በአሁኑ ሰአት ከ1600 በላይ አቅራቢዎችን በመያዝ ፤ ከ5 ሺህ በላይ ምርቶችን ashewa.com በተሰኘው ድረገጹ ላይ እያገበያየ ነው፡፡

በዛሬው እለት ስራ ያስጀመረው የምርቶች አቅርቦት እና ሎጀስቲክስ አገልግሎት የኑሮ ውድነትን እና ገበያን ለማረጋጋት ሚና ይኖረዋል የተባለ ሲሆን ቀላል እና አስተማማኝ በሆነ መንገድ የገጠሩን ማህበረሰብ ከከተሜው ጋር በቢዝነስ ለማስተሳሰር የተዘጋጀ መሆኑ ተመላክቷል፡፡

በቀጣይ አንድ ወር በአገልግሎቱ ከ15 ሺህ በላይ ከሆኑ ነጋዴዎች ፤ ከ10 ሺህ በላይ ለሆኑ ደንበኞች ከ5 ሺህ በላይ ምርቶችን በማቅረብ ለመስራት ታቅዷል፡፡

ድርጅቱ በአሁኑ ሰአት አገልግሎቱን የሚሰጠው በአዲስ አበባ ሲሆን ለምርቶች ማከማቻ የሚሆኑ ሶስት መጋዘኖችን እንዳዘጋጀ የዴሊቨሪ እና ፈጣን መልእክት አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ ገ/ማርያም አለሙ ለኢትዮ የንግድ እና ኢንቨስትመንት መድረክ ተናግረዋል፡፡ በቀጣይ የመጋዘኖቹን ቁጥር ወደ 8 ለማሳደግ መታቀዱን ጠቁመዋል፡፡

በዚህ ስርአት ምርቶችን የሚገዙ ደንበኞች የሚፈልጉትን ምርት በመረጡት የተሽከርካሪ አይነት ካሉበት እንዲደርሳቸው የሚደረግ ሲሆን ምርቱን ከገዙ በኋላ ባሉት ሰባት ቀናት ውስጥ ተመላሽ ማድረግ ወይም ቅያሪ ቢፈልጉ እንደሚስተናገዱ አቶ ገ/ማርያም ተናግረዋል፡፡

በሌላ በኩል ምርቶቻቸውን መሸጥ የሚፈልጉ ነጋዴዎችም በተዘጋጁት መጋዘኖች እስኪሸጡ ድረስ ማስቀመጥ ይችላሉ፡፡

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን
ነሐሴ24 ቀን 2014 ዓ.ም
2.4K views11:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 12:33:11

2.5K views09:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 12:25:54
የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አባል መሆን ግዴታ ሊሆን ነው።


የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አባል መሆን ከዚህ በፊት በፍቃደኝነት ላይ የተመሠረተ የነበር ሲሆን አሁን በወጣ አዲስ አዋጅ ግዴታ ሆኗል።


የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አባል መሆን ግዴታነት በፌደራል ደረጃ በሚመሠረተው ምክር ቤት የሚወሰን መሆኑን የኢትዮጵያ የጤና መድህን አገልግሎት የፕሮግራም ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ሙሉቀን አርጋው ተናግረዋል።


የጤና ወጪ ከአመት አመት ጭማሪ እያሳየ መሄዱን ያነሱት ዶክተር ሙሉቀን፣ ለአገልግሎቱ ተጠቃሚነት ተገቢ የሆነ ሰው አባል የመሆን ግዴታ አለበት ነው ያሉት።

አባል ለመሆን ማንኛውም ሰው የመመዝገቢያ ክፍያ እና የአባልነት መዋጮ መክፈል እንደሚኖርበት ያነሱት ዶክተር ሙሉቀን፣ እንደየ ደረጃው የገንዘብ መጠኑ የተለያየ መሆኑንም አስረድተዋል።

ለገጠር 375፣ ለገጠር ከተሞች 500፣ ለትልልቅ ከተሞች 665 እና ለአርብቶ አደር አከባቢዎች ደግሞ 325 ብር መሆኑን ገልጸዋል።

መክፈል የሚችል ከሆነ እራሱ እንደሚከፍል እንዲሁም መክፈል የማይችል ህብረተሰብ ግን ተመርጦ ፣ተለይቶ በወረዳ እና በክልል መንግስት ወጪው የሚሸፈን ይሆናል ተብሏል።

በዚህም በአመቱ ለጤና መድህን ከከፈሉ ተጠቃሚዎች 3.1 ቢሊየን ብር መሰብሰቡን ገልጿል።


የመክፈል አቅም ከሌላቸው እና መንግስት ከሚደጉማቸው ተጠቃሚዎች ደግሞ ከ 712 ሚሊየን ብር በላይ መሰብሰቡንም ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ ገልፀዋል።

የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን ከመደበኛው ክፍለ ኢኮኖሚ ውጪ የሚገኙ ከ80 በመቶ በላይ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን የያዘ ነው።


በእስከዳር ግርማ

ነሐሴ 24 ቀን 2014 ዓ.ም
2.5K views09:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 12:18:51
ቦርንመዝ ስኮት ፓርከርን አሰናበተ፡፡


አዲሱ የውድድር ዘመን ከተጀመረ የተከናወኑት አራት ጨዋታዎች ብቻ ናቸው፡፡

ቦርንመዝ ግን ቅዳሜ ለት ቡድኑ በሊቨርፑል 9-0 የተሸነፈበትን መንገድ ገምግሞ ስኮት ፓርከርን ለማሰናበት ወስኗል፡፡

የ41 ዓመቱ ፓርከር ከሽንፈቱ በኋላ ቡድኑ በፕሪምየር ሊግ ተሳታፊ ለመሆን በቂ ድጋፍ እንዳልተደረገለት ጠቅሶ በውጤቱ አለመገረሙን ተናግሯል፡፡

የፕሪምየር ሊጉን የመጀመሪያ ጨዋታ ቢያሸንፍም ሶስት ተከታታይ ጨዋታዎችን ተረትቷል፡፡

‹‹ እንደ ቡድን እና ክለብ መሻሻላችንን መቀጠል ይኖርብናል፡፡

ክለቡ ባስቀመጠው ስትራቴጂ መሰረት ዘላቂነት ያለው ዕድገት ማሳየት ይኖርብናል ›› በማለት የክለቡ ባለቤት ማክሲም ዴሚን ተናግረዋል፡፡


በአቤል ጀቤሳ

ነሐሴ 24 ቀን 2014 ዓ.ም
2.3K views09:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 09:55:27
በዛሬው የቸገረን ነገር ፕሮግራም ላይ ከ4:30-6:00 በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከፕሮፌሰር ሀረገወይን አሰፋ እና ከልጃቸው ጋዜጠኛ ሔርሜላ ሀረጋዊ ከአዘጋጁ ጋዜጠኛ ሳሙኤል ፍቅሬጋ ቆይታ ያደርጋሉ።

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።

Telegram https://t.me/ethiofm107dot8

Twitter https://twitter.com/EthioFM

YouTube https://www.youtube.com/channel/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos

Facebook https://www.facebook.com/onelovebroadcast
Website https://ethiofm107.com/

ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 6321 ላይ ይላኩልን።

ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።
2.7K viewsedited  06:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 09:00:49 የዛሬው የኢትዮ ማለዳ ዜናዎቻችን 24-12-14

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።

Telegram https://t.me/ethiofm107dot8

Twitter https://twitter.com/EthioFM

YouTube https://www.youtube.com/channel/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos

Facebook https://www.facebook.com/onelovebroadcast
Website https://ethiofm107.com/

ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 6321 ላይ ይላኩልን።

ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።
2.9K views06:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 13:39:28

3.5K views10:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 11:16:59
የዘንድሮው የጳጉሜ ፌስቲቫል በእንጦጦ ፓርክ ይካሄዳል፡፡

“ጳጉሜ የአፍሪካ ወርቃማ ወር” በሚል መሪ ቃል ከጳጉሜ አንድ እስከ ጳጉሜ 5 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ በእንጦጦ ፓርክ እንደሚካሄድ ታውቋል።

የጳጉሜ አብ ሀገር አቀፍ ፌስቲቫል በሰጠው መግለጫ፣ ፌስቲቫሉ በእንጦጦ ፖርክና በመላው አዲስ አበባ በደማቅ ሁኔታ እንደሚከበር አስታውቋል።

ፌስቲቫሉ ኢትዮጵያ ያላትን ተፈጥሯዊ ሀብቶቿን ለአለም አቀፉ ማህበረስብ ለማድረስ ትልቅ ጠቀሜታ እንዳለውም ተነስቷል።

ጳጉሜ አንድ የሰላምና የፍቅር ቀን፣

ጳጉሜ ሁለት የባህልና የአፍሪካ ቀን
ጳጉሜ ሦስት የአፍሪካ ለልጆች ክብረ በዓል ወይንም የዝናብ ላይ ሩጫ በሚል እንደሚከበርም ሰምተናል።

እንዲሁም ጳጉሜ አራት እንነግድ በጳጉሜ ፣ጳጉሜ አምስት ደግሞ የጳጉሜ ውቦች በሚል እንደሚከበር ተነግሯል።
ለአምስት ቀናት በሚቆየው በዚህ ፌስቲቫል ላይ፣ ባዛሮች፣ ስፖርታዊ ውድድሮች፣የሙዚቃ ድግስ፣ የባህል ቁንጅና ውድድሮች እና የምግብ ዝግጅት እንደሚከናወኑ አዘጋጆች አስታውቀዋል።

በአባቱ መረቀ
ነሐሴ 23 ቀን 2014 ዓ.ም
3.6K viewsedited  08:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ