2022-09-23 13:00:57
ሩሲያ ከዩክሬን በነጠቀቻቸዉ አራት ግዛቶች ህዝበ ዉሳኔ ማካሄድ ጀመረች፡፡
የሩሲያ ጦር ከዩክሬን በነጠቃቸዉ አራት ግዛቶች ህዝበ ዉሳኔ መጀመሩን የአገሪቱ መንግስት አስታዉቋል፡፡
ህዝበ ዉሳኔዉ የሚካሄደዉ በ ሉሃንስክ፤ ዶኔስክ፤ በኬርሶንና በዛፖርዢያ ግዛቶች ነዉ፡፡
ሂደቱ እስከ ቀጣይ ሳምንት ማክሰኞ ድረስ እንደሚቀጥልም ሞስኮ አስታዉቃለች፡፡
ምዕራባዉያኑ ግን ህዝበ ዉሳኔዉን ለይስሙላ የሚደረግ ሲሉ አጣጥለዉታል፡፡
ሩሲያ ከስምንት አመት በፊት ከዩክሬ በወሰደችዉ ክረሚያ ግዛት ተመሳሳይ ህዝበ ዉሳኔ አድርጋ ማጠቃለሏ የሚታወስ ነዉ፡፡
ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።
Telegram https://t.me/ethiofm107dot8
Twitter https://twitter.com/EthioFM
YouTube https://www.youtube.com/channel/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos
Facebook https://www.facebook.com/onelovebroadcast
Website https://ethiofm107.com/
ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 6321 ላይ ይላኩልን።
ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።
በአባቱ መረቀ
መስከረም 13 ቀን 2015 ዓ.ም
2.9K views10:00