Get Mystery Box with random crypto!

Ethio Fm 107.8

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiofm107dot8 — Ethio Fm 107.8 E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiofm107dot8 — Ethio Fm 107.8
የሰርጥ አድራሻ: @ethiofm107dot8
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.32K
የሰርጥ መግለጫ

በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

3

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 94

2022-09-23 14:14:48

2.7K views11:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-23 13:00:57
ሩሲያ ከዩክሬን በነጠቀቻቸዉ አራት ግዛቶች ህዝበ ዉሳኔ ማካሄድ ጀመረች፡፡

የሩሲያ ጦር ከዩክሬን በነጠቃቸዉ አራት ግዛቶች ህዝበ ዉሳኔ መጀመሩን የአገሪቱ መንግስት አስታዉቋል፡፡

ህዝበ ዉሳኔዉ የሚካሄደዉ በ ሉሃንስክ፤ ዶኔስክ፤ በኬርሶንና በዛፖርዢያ ግዛቶች ነዉ፡፡

ሂደቱ እስከ ቀጣይ ሳምንት ማክሰኞ ድረስ እንደሚቀጥልም ሞስኮ አስታዉቃለች፡፡

ምዕራባዉያኑ ግን ህዝበ ዉሳኔዉን ለይስሙላ የሚደረግ ሲሉ አጣጥለዉታል፡፡

ሩሲያ ከስምንት አመት በፊት ከዩክሬ በወሰደችዉ ክረሚያ ግዛት ተመሳሳይ ህዝበ ዉሳኔ አድርጋ ማጠቃለሏ የሚታወስ ነዉ፡፡

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።

Telegram https://t.me/ethiofm107dot8

Twitter https://twitter.com/EthioFM

YouTube https://www.youtube.com/channel/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos

Facebook https://www.facebook.com/onelovebroadcast

Website https://ethiofm107.com/

ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 6321 ላይ ይላኩልን።

ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።


በአባቱ መረቀ
መስከረም 13 ቀን 2015 ዓ.ም
2.9K views10:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-23 12:41:52
በደቡብ ክልል አማሮ ልዩ ወረዳ ታጣቂዎች በከፈቱት ተኩስ አምስት ሰዎች ተገደሉ፡፡

በትላንትናዉ እለት የሸኔ የሽብር ቡድን በወረዳው ባደረሰው ጥቃት አምስት ሚሊሻዎች መሞታቸውን ኢትዮ ኤፍ ኤም ሰምቷል፡፡
የአማሮ ልዩ ወረዳ የፖሊስ አዛዥ ረዳት ኢንፔክተር አራርሶ ነጋሽ ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንደተናገሩት፣ በአካባቢው በተደጋጋሚ እየተከሰተ ያሉትን ግድያዎች በመፈጸም ላይ ያሉት ከምዕራብ ጉጂ ገላና ወረዳ የሚነሱ የሸኔ ታጣቂዎች ናቸው፡፡

ትላንት የተከሰተው የጸጥታ ችግርም ጠንሳሾቹ እነርሱ መሆናቸው የገለጹት አራርሶ ነጋሽ፣ በወረዳው አሁንም ከፍተኛ የጸጥታ ችግር መከሰቱን ተናግረዋል፡፡

በትላንትናው እለት ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተውጣጡ አካላት በወረዳው ከዚህ በፊት የተከሰተውን የጸጥታ ችግር በተመለከተ ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ለመምከር እያቀኑ በነበረበት ጊዜ ነው ጥቃቱ የደረሰው፡፡
በአካባቢው ከፍተኛ “የታጣቂዎች ክምችት” እንዳለ ከነዋሪዎች መስማታቸውንና ይህንኑም ዛሬ ወደ አካባቢው የተንቀሳቀሰው የደቡብ ክልል ልዩ ኃይል እና የፌደራል ፖሊስ አባላት ማረጋገጣቸውን ነግረዉናል።

በሔኖክ ወ/ገብርኤል
መስከረም 13 ቀን 2015 ዓ.ም
2.8K views09:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-11 18:09:27
454 views15:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-10 19:21:27
ሜድሮክ በ50 ቢሊየን ብር ለሚገነባው ዘመናዊ መንደር በዛሬው እለት የመሰረተ ድንጋይ ተቀመጠ።

የሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በመቻሬ ሜዳ በ50 ቢሊየን ብር በ250 ሺህ ካሬ ሜትር መሬት ላይ ለሚያስገነባው ዘመናዊ የመሀመዲያ መንደር ነው የመሰረተ ድንጋይ ያስቀመጠው፡፡


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ የመሰረተ ድንጋዩን አኑረዋል፡፡

ለመዲናዋ አዲስ ውበትን ይጨምራል የተባለው ይሄው ዘመናዊ የመንደር ግንባታ ከአምስት እስከ ሰባት አመት ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሏል።

50 ቢሊዮን ብር ወጭ ይጠይቃል የተባለው ይህ ዘመናዊ መንደር እጅግ ዘመናዊ ሞል፣ የግብይት ማዕከላት፣የአረንጓዴ ቦታን፣አዲሱ ሆቴል፣ ቪላዎች፣ ፣ ሱፐር ማርኬት፣ አፓርትመንት፣ ለእግረኛ ምቹ የሆኑና መንገዶችና ሎሎችም መሰረተ ልማቶችን ያሟላና በአለምአቀፍ ስታንዳርድ መሰረት የሚገነባ መሆኑን ሰምተናል።

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን

ጳጉሜ 05 ቀን 2014 ዓ.ም
2.6K views16:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-09 18:39:00
ፋሲል ከነማ የብሩንዲውን ቡማሙሩ 3 ለ 0 አሸነፈ::


ፋሲል ከነማ በ2022/23 የአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ቅድመ-ማጣሪያ የብሩንዲውን ቡማሙሩ 3 ለ 0 አሸንፏል።

ዛሬ በባህር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም በተደረገው የሁለቱ ክለቦች ጨዋታ ዓለምብርሃን ይግዛው፣ ፍቃዱ ዓለሙና ታፈሰ ሰለሞን ለፋሲል ከነማ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል።

ፋሲል ከነማ ከቡማሙሩ ጋር የመልስ ጨዋታውን መስከረም 6 ቀን 2015 ዓ.ም የሚያደርግ ይሆናል፡፡


ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን

ጳጉሜ 04 ቀን 2014 ዓ.ም

ለወቅታዊና ታማኝ መረጃዎች የቴሌግራምና የዩቲዩብ ቻናላችንን ይከታተሉን!
Telegram https://t.me/ethiofm107dot8
YouTube https://www.youtube.com/.../UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos
3.4K views15:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-09 15:22:27

3.0K views12:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-09 13:25:32
ሰሜን ኮሪያ የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ባለቤት መሆኗን በይፋ አወጀች::

የአገሪቱ መሪ ኪም ጆንግ ኡን ፕዮንግያንግ የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ባለቤት ሆናለች ብለዋል፡፡
የአገሪቱ መሪ ኪም ጆንግ ኡን ውሳኔውን የማይቀለበስ ሲሉ ገልጸውታል። ኒውክሌር ካለመታጠቅ ጋር በተያያዘ ምንም ዓይነት ድርድር ሊኖር እንደማይችልም ገልጸዋል።

በአዲሱ ሕግ መሠረት ሰሜን ኮሪያ ራሷን ለመከላከል በሚል ቀድሞ የኒውክሌር ጥቃት የመፈጸም መብት እንዳላት ይደነግጋል።
ፒዮንግያንግ በተደጋጋሚ ማዕቀብ ቢጣልባትም ከ2006 እስከ 2017 ባለው ጊዜ ስድስት የኒውክሌር ሙከራዎችን አድርጋለች።

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ውሳኔዎችን በመጣስ ወታደራዊ አቅሟን ማሳደጓን ቀጥላለች።
የጦር አቅሟን በማሳደግ ከጎረቤቶቿ በተጨማሪ አሜሪካን ማጥቃት የሚያስችሉ መሣሪያዎችን እንደታጠቀችም መረጃዎች ያመለክታሉ።

በአባቱ መረቀ
ጳጉሜ 04 ቀን 2014 ዓ.ም

ለወቅታዊና ታማኝ መረጃዎች የቴሌግራምና የዩቲዩብ ቻናላችንን ይከታተሉን!
Telegram https://t.me/ethiofm107dot8
YouTube https://www.youtube.com/.../UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos
3.2K views10:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-09 09:44:05 የዛሬው የኢትዮ ማለዳ ዜናዎቻችን 04-13-14

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።

Telegram https://t.me/ethiofm107dot8

Twitter https://twitter.com/EthioFM

YouTube https://www.youtube.com/channel/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos

Facebook https://www.facebook.com/onelovebroadcast

Website https://ethiofm107.com/

ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 6321 ላይ ይላኩልን።

ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።
3.0K views06:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-09 09:35:15 ዛሬ የአገልጋይነት ቀን ነዉ!

በዚህም መሰረት፡-

• የአዲስ አበባ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ኃይል ልማት ቢሮ እንዳለዉ
በዛሬው ዕለት የመንግስትና የግል ድርጅት ኃላፊዎች የፅዳት ባለሙያዎችን ተክተው የጽዳት ስራ ይሰራሉ፡፡

በሁሉም ዘርፍ የተሰማሩ የመንግስት እና የግል ድርጅት ኃላፊዎች በሚመሩት ተቋም ወይም የስራ ዘርፍ ዝቅተኛ የተባለውን ኃላፊነት ተክተው ለግማሽ ቀን አገልግሎት የሚሰጡበት ዘመቻ እንደሚያካሂድ የከተማዋ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ኃይል ልማት ቢሮ አማካሪ ወ/ሮ መቅደስ ተስፋዬ ተናግረዋል።

የአገልጋይነት ቀን በአዲስ አበባ ከተማ “አገልጋይነት ከእኔ ይጀምራል” በሚል መሪ ቃል የከተማዋ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ኃይል ልማት ቢሮ አስተባባሪነት ዛሬ እየተከበረ ነው።


• የመንግስትና የግል ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎችም ለግማሽ ቀን በነፃ እና ትህትናን በተላበሰ መንገድ ለተሳፋሪዎች አገልግሎት የሚሰጡበት እንዲሁም የግል መኪና አሽከርካሪዎችም ትራንስፖርት ለሚጠብቁ ሰዎችን አገልግሎት የሚሰጡበት እንደሆነ ተናግረዋል።

• የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ፥ “የአገልጋይነት ቀን”ን ምክንያት በማድረግ ነው የነጻ ትራንስፖርት አገልግሎት እንደሚሰጥ የገለጹት፡፡

በዚህም አዳዲስ የሚሰማሩ አውቶቡሶችን ጨምሮ ፣ ሸገር የብዙኃን ትራንስፖርት አገልግሎት ድርጅትና አንበሳ የከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት ከጠዋቱ 12 ሰዓት እስከ ምሽቱ 3 ሰዓት ድረስ በነፃ አገልግሎት እንደሚሰጡ ገልጸዋል፡፡
• የአገልጋይነት ቀንን ምክንያት በማድረግ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች በመስቀል አደባባይ የፅዳት መረሃ-ግብር በማካሄድ ላይ ናቸዉ፡፡

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን
ጳጉሜ 04 ቀን 2014 ዓ.ም

ለወቅታዊና ታማኝ መረጃዎች የቴሌግራምና የዩቲዩብ ቻናላችንን ይከታተሉን!

Telegram https://t.me/ethiofm107dot8
YouTube https://www.youtube.com/channel/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos
2.7K viewsedited  06:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ