Get Mystery Box with random crypto!

Ethio Fm 107.8

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiofm107dot8 — Ethio Fm 107.8 E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiofm107dot8 — Ethio Fm 107.8
የሰርጥ አድራሻ: @ethiofm107dot8
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.32K
የሰርጥ መግለጫ

በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

3

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 96

2022-09-06 12:19:45 ከኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፍትህ ሚኒስቴር በሀሰተኛ ሰነዶች ዙሪያ የተሰጠ የዜና መግለጫ:-

ሰዎች የማይገባቸውን ጥቅም ለማግኘት በማሰብ ወይም የማይገባቸውን አገልግሎት ከመንግስት ወይም መንግስታዊ ካልሆኑ ተቋማት ለማግኘት የተለያዩ እውነተኛ ያልሆኑ መረጃዎችን የያዙ ሰነዶችን ሲያቀርቡ ይስተዋላሉ፡፡
በተለይም ሀሰተኛ የማንነት መታወቂያ፣ የጋብቻ ፣ የልደት፣ የሞት፣ የትምህርት እና የስራ ምስክር ወረቀቶች፤ የውክልና ምስክር ወረቀት፣ የህክምና ማስረጃዎች፣ የባንክ ሲፒኦ፣ ቼኮች፣ የአሽከርካሪ ፈቃድ፣ የፍርድ ግልባጭ ወዘተ በስፋት ጥቅም ላይ ከሚውሉ ወይም በሀሰት ከሚዘጋጁ የሰነድ አይነቶች የተወሰኑት ናቸው፡፡

እኚህን እና ሌሎች ሀሰተኛ ሰነዶችን ማዘጋጀትና መገልገል በሀገር ኢኮኖሚ እንዲሁም በዜጎች መብትና ጥቅም ላይ ከፍተኛ ጉዳት የሚያደርስ የወንጀል ድርጊት ነው፡፡

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፍትህ ሚኒስቴር የወንጀል ህጉን ከማስከበር እና የህግ የበላይነትን ከማረጋገጥ አኳያ እያከናወናቸው ካሉ በርካታ ተግባራት መካከል አንዱ ሀሰተኛ ሰነድን አዘጋጅተው ወይም ተገልግለው በሚገኙ ሰዎች ላይ የህግ ተጠያቂነትን ማስፈን ነው፡፡ በዚህም መሰረት ሀሰተኛ ሰነዶችን ባዘጋጁ እና በተገለገሉ አያሌ ሰዎች ላይ ክስ በመመስረት እንዲቀጡ ማድረግ ችሏል፡፡
ይሁንና ከጊዜ ወደ ጊዜ ሰነዶቹ የሚዘጋጁበት መንገድ እየዘመነ መምጣቱ በመንግስት ተቋማት አገልግሎት አሰጣጥ ሂደት ውስጥ የሚስተዋለው ቸልተኝነቶች ተጨምሮበት ወንጀሉ ከመቀነስ ይልቅ እየተበራከተ እንዲመጣ አድርጎታል፡፡
በዚህም ምክንያት ብዙዎች የማይገባቸውን ጥቅም አግኝተዋል፤ በመንግስት እና የህዝብ ጥቅም ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል፡፡
ከቅርብ ጊዜ ወደዚህ ደግሞ ህግን በሚያውቁ የሕግ ባለሙያዎች ሳይቀር ሀሰተኛ ሰነዶች ጥቅም ላይ እየዋሉ መሆኑን ከወራቶች እና ከቀናት በፊት ክስ መስርተን ወደ ፍርድ ቤት ያቀረብናቸው ጉዳዮች ዋቢ ናቸው፡፡ ይህ መሆኑ ጉዳዩ ምን ያህል አሳሳቢ እየሆነ መምጣቱን ያመላክታል፡፡

በመሆኑም ፍትሕ ሚኒስቴር፡-

•የማይገባቸውን ጥቅም ለማገኘት ሀሰተኛ ሰነዶችን በማቅረብ አገልግሎት ሰጪ ተቋማትን የሚያታልሉ ግለሰቦች ከዚህ አይነት ድርጊታቸው እንዲቆጠቡ፤
• በሀሰት የተዘጋጁ ሰነዶችን በዝግጅት ሂደት ላይም ይሁን ለአገልግሎት መቅረቡን ያየ ወይም ያወቀ ማንኛውም ግለሰብ በአቅራቢያ ለሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ የበላይ ኃላፊ ጥቆማ እንዲሰጥ፤

• ተቋማት ለተገልጋይ የሚሰጡት አገልግሎት በትክክልም ለሚገባው የተሰጠ መሆኑን የሚያረጋግጡበትን አስተማማኝ ዘዴ እንዲያለሙ እና እንዲተገብሩ፤
• የፍትሕ ተቋማት (የዐቃቤ ሕግ ተቋማችንን ጨምሮ) የሚቀርቡላቸውን ጥቆማዎች እና ክሶች በተገቢው በማስተናገድ ሀሰተኛ ሰነድ መርገጫ እንዲያጣ የማድረግ ኃላፊነታችውን እንዲወጡ፤

• ተቋማት ሀሰተኛ ሰነዶችን በመፍጠር፣ ወይም በመስጠት ወይም ሰነዶችን በተገቢው የማጣራት ኃላፊነታቸውን ሳይወጡ ከወንጀለኛ ጋር የሚያብሩ ሰራተኞች ላይ ተገቢውን የክትትል ስርዓት ዘርግቶ እርምጃ በመውሰድ ከፍትሕ ጎን እንዲቆሙ ይጠይቃል፡፡

ጳጉሜ 01 ቀን 2014 ዓ.ም

ምንጭ፡-የኢፌዲሪ ፍትሕ ሚኒስቴር

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን
1.7K views09:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-06 10:18:19
2.1K views07:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-05 10:23:23 የዛሬው የኢትዮ ማለዳ ዜናዎቻችን 30-12-14

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።

Telegram https://t.me/ethiofm107dot8

Twitter https://twitter.com/EthioFM

YouTube https://www.youtube.com/channel/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos

Facebook https://www.facebook.com/onelovebroadcast

Website https://ethiofm107.com/

ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 6321 ላይ ይላኩልን።

ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።
974 views07:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 20:11:28
አትሌት ኮማንደር ደራርቱ ቱሉ የ2014 ዓ.ም የበጎ ሰው ልዩ ተሸላሚ በመሆን ዛሬ ተሸልማለች።

10ኛው የዓመቱ በጎ ሰው ዕውቅና እና ሽልማት መርሃ ግብር በዛሬው እለት በኢንተርሌግዥሪ ሆቴል ተካሂዷል።

በመርሃ ግብሩ ላይም አትሌት ደራርቱ ቱሉ በስፖርቱ ዘርፍ አመራር ባስመዘገበችው የላቀ ውጤት የበጎ ሰዉ የዓመቱ ልዩ ተሸላሚ ለመሆን በቅታለች።
1.8K views17:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 18:56:55
10ኛው የዓመቱ በጎ ሰው ዕውቅና እና ሽልማት መርሃ ግብር ዛሬ ተካሂዷል፡፡

በተለያዩ ዘጠኝ ዘርፎች የአመቱ የበጎ ሰው ሽልማት አሸናፊዎች ተለይተዋል።

1. በመምህርነት ዘርፍ ዶክተር ውብሸት ዠቃለ

2. በበጎ አድራጎት ዘርፍ ወይዘሮ ክብራ ከበደ

3. በቅርስና ባህል ሸህ መሐመድ አወል ሃምዛ

4. በኪነጥበብ ፊልም ዳይሬክቲንግ ዓለምፀሐይ በቀለ

5. በዲያስፖራ ዘርፍ ዶክተር ርብቃ ጌታቸው ኃይሌ

6. ንግድና ሥራ ፈጠራ ዘርፍ ሰኢድ መሐመድ

7. በመንግሥታዊ የሥራ ኃላፊነት አቶ ግርማ ዋቄ

8. በሚዲያ ዘርፍ አቶ ሰለሞን ገብረሥላሴ

9. በሳይንስ ዘርፍ ኢሜሪቲስ ፕሮፌሰር ረዳ ተክለሐይማኖት

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን

ነሐሴ 29 ቀን 2014 ዓ.ም
2.3K views15:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-03 13:30:57

1.9K views10:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-03 13:02:48
ሉናር ኢንተርናሽናል ኮሌጅ በተለያዩ የድኅረ ምረቃ መርሃ ግብሮች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች በዛሬው እለት አስመርቋል።

ኢንተርናሽናል ኮሌጁ በመደበኛ መርሃ ግብር በኹለተኛ ዲግሪ ያስተማራቸውን 366 ተማሪዎች ነው በስካይላይት ሆቴል ያስመረቀው።


የኮሌጁ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ታሪኩ አቶምሳ የኮሌጃችን ስኬት የሚመዘነው በተማሪዎች ስኬት መሆኑን ገልጸው፣ የኮሌጁም ዓላማ ተማሪዎቹ አገርን የሚያገለግሉ፣ በጎ ተፅዕኖ መፍጠር የሚችሉ ማድረግ ነው ብለዋል።

ለተማሪዎች ባስተላለፉት መልዕክትም ለምርቃት መብቃት አንዱ ስኬት ቢሆንም በቀጣይ ለሚኖር ጉዞ መጀመሪያ ነው ብለዋል ።

በዚህ ጊዜ አገራችን ተወዳዳሪ ሆና በራሷ የምትተማመን አገር እንድትሆን መሥራት ይገባልም ነው ያሉት።

በዝግጅቱ ላይ በከፍተኛ ማዕረግ ለተመረቁ 31 ተማሪዎች ሽልማት ተሰጥቷል። እንዲሁም ኮሌጁ ለመጀመሪያ ጊዜ ባካሄደው ዓመቲዊ የተማሪዎች የምርምር አውደ ጥናት ላይ አሸናፊ ለሆኑ አምስት ጥናታዊ ፅሑፍ አቅራቢዎች የምስክር ወረቀት እና የገንዘብ ሽልማት ተበርክቷል።

በምርቃት ዝግጅቱ ላይ ሦስት ተማሪዎች ከየትምህርት ክፍላቸው እጅግ ከፍተኛ ነጥብ በማምጣት የወርቅ ሜዳልያ ሲቀበሉ፤ ከሴት ተማሪዎች ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገበች ተማሪም የዋንጫ ሽልማትን ተቀብላለች። በተጨማሪም ከሦስቱም የትምህርት ክፍሎች የላቀ ከፍተኛ ውጤት ላመጣ ተማሪም የዋንጫ ሽልማት ተበርክቷል።

የሉናር ኢንተርናሽናል ኮሌጅ የ2014 ኹለተኛ ዲግሪ ተመራቂዎች ለኮሌጁ ኹለተኛ ዙር ተመራቂዎች ሲሆኑ፤ በቢዝነስ አድሚንስትሬሽን፣ በፋይናንስ እና ኢንቨስትመንት እንዲሁም በፕሮጀክት ማኔጅመንት ትምህርታቸውን የተከታተሉ ናቸው።

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን

ነሐሴ 28 ቀን 2014 ዓ.ም
2.1K views10:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-03 12:23:27

1.9K views09:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-03 11:52:43
የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ በዲቦራ ፋውንዴሽን የተገነባውን መዋዕለ ህጻናት በዛሬው ዕለት መርቀዋል፡፡

በለገጣፎ ከተማ የተገነባው መዋዕለ ህጻናቱ፥ ዘጠኝ የመማሪያ ክፍሎች እና ሌሎች የአስተዳደር ቢሮዎች ያሉት መሆኑ ተገልጿል፡፡

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን

ነሐሴ 28 ቀን 2014 ዓ.ም
442 views08:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-03 11:47:51
የጎንደር ዩንቨርስቲ በተለያዩ የትምህርት መርሐ ግብሮች ያሰለጠናቸውን ከ5 ሺህ በላይ ተማሪዎችን እያስመረቀ ነው።


የጎንደር ዩንቨርስቲ በዛሬው ዕለት በተለያዩ የትምህር መርሃ ግብር ያሰለጠናቸውን 5ሺህ 5 መቶ 27 ተማሪዎችን በማስመረቅ ላይ ይገኛል ።

በምረቃ ስነስርዓቱ ላይ የዩንቨርስቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር አስራት አፀደወይን የዘንድሮ ተመራቂዎቹ ወቅታዊውን ችግር ተቋቁመው ለዚህ በመብቃታቸው ልዩ ያደርጋቸዋል ብለዋል።

ተመራቂዎቹ ኢትዮጵያ የገጠማትን ችግር ከመፍታት አኳያ ትልቅ የቤት ስራና ኃላፊነት እንዳለባቸው ዶክተር አስራት አሳስበዋል ።

አንድነታችን የድላችን ምንጭ ነው ያሉት የዩንቨርስቲው ፕሬዚዳንት ፣ ሁላችንም ለኢትዮጵያ ሠላምና ደህንነት በጋራ ልንረባረብ ይገባል ብልዋል ።

ተመራማሪዎቹ በመደበኛ፣ በተከታታታ፣በሁለተኛና በሶስቸኛ ዲግሪ መርሃግብር ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ ናቸው ተብሏል።


የጎንደር ዩንቨርስቲ ከ3 መቶ 20 በላይ የትምህርት መርሐግብሮች እንዳሉት ተነስቷል ።

በተጨማሪም 10ሺህ 5 መቶ 86 መምህራንና ሥራተኞች እንዳሉትም ፕሬዝዳንቱ አስታውቀዋል ።

የጎንደር ዩንቨርስቲ ከ 67 አመት በፊት በጤናው ዘርፍ ስራ መጀመሩ የሚታወስ ነው።


በአባቱ መረቀ

ነሐሴ 28 ቀን 2014 ዓ.ም
498 views08:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ