Get Mystery Box with random crypto!

Ethio Fm 107.8

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiofm107dot8 — Ethio Fm 107.8 E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiofm107dot8 — Ethio Fm 107.8
የሰርጥ አድራሻ: @ethiofm107dot8
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.32K
የሰርጥ መግለጫ

በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

3

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 98

2022-09-01 13:30:45
ቴሌ ብር ከ73 አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ጋር በትስስር እየሰራ ይገኛል ።

ቴሌ ብር አገልግሎቱን መስጠት ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ከ73 አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ጋር በትስስር እየሰራ መሆኑን የቴሌ ብር መተግበሪያ ቺፍ ኦፊሰር አቶ ብሩክ አዳነህ ተናግረዋል ።

የቴሌ ብር መተግበሪያ አገልግሎቱን መስጠት የጀመረው ከ15 ወራት በፊት መሆኑ ተገልጿል ።

ከዛም ጊዜ አንስቶ 67.2 ሚሊዮን ደንበኞችን ማፍራት የቻለ ሲሆን ፤46 ቢለየን ብር ዝውውር ማድረግ መቻሉን አቶ ብሩክ ጨምረው ገልፀዋል ።

ቴሌ ብር የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ስራቸውን ቀልጣፈና ፈጣን ከማድረግ ባለፈ፤ ማህበረሰቡን ያስመረሩ ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል ትልቅ እድልን መፍጠር ችሏል ።

ከምን በላይ ከሰነዶች ጋር ተያያዣነት ያላቸውን አገልግሎቶችን ከእጅ ንክኪ ነፃ በማድረግ ከሙስና የጠራ አሰራር እንዲፈጠር ሆኗል ።

ይህንንም ተግባር አጠናክሮ ለማስቀጠል ኢትዮ ቴሌኮም ከሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ አገልግሎት ጋር በትስስር ለመስራት የዉል ስምምነት አድርገዋል ።

ይህም ኢትዮ ቴሌኮም በትስስር አብሮ የሚሰራቸውን የአገልግሎት ተቋማት 74 ያደርሰዋል ።

በውል ስምምነቱ ላይ የተገኙት የኢትዮ ቴሌኮም ስራአስኪያጅ ወ/ሮ ፍሬሕይወት ታምሩ ተቋሙ ባጭር ጊዜ ውስጥ እያሳየ የመጣውን አገልግሎን የማዘመን ስራን አድንቀዋል ።

አሁንም ሰዎችን የሚያጉላሉ እና የሚያሰለቹ አሰራሮችን ለመቅረፍ በንቃት እንሰራለን ብለዋል።

በሃገራችን የቴሌ አገልግሎት 99.1 አንድ መቶ ተደራሽ ማድረግ መቻሉን አንስተዋል።

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን
ነሐሴ 26 ቀን 2014 ዓ.ም
948 views10:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 13:22:17 ‹የመሰረተ ልማት ዝርፊያ አስተማማኝ የሃይል አቅርቦት ለህብረተሰቡ ማድረስ እንዳንችል ፈተና ሆኖብናል›› የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል አገልግሎት ድርጅት

የኤሌክትሪክ አገልግሎት ህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ መላኩ ታየ ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንደተናገሩት በአገራችን አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ሀይል አቅርቦት ለማዳርስ በተለይም መጭዉን የአዲስ አመት በአል ምክኒያት በማድረግ ሃይል መቆራረጥ እንዳይኖር 24 ሰአት በሚሰራ ቡድን ተዋቅረን እየሰራን እንገኛለን ብለዋል፡፡

ሃላፊዉ አሁን ያለዉ የደምበኞች የሃይል አጠቃቀም እጅጉን እየሰፋና እያደገ መምጣቱ ጋር ተያይዞ ነባሩ ኔትዎርክ የሚፈለገዉን ያህል አቅርቦት ተደራሽ ማድረግ እንዳልተቻለ ተናግረዋል ፡፡

ለሃይል መቆራረጡ እንደምክኒያት ያነሱት የኔትወርኩ ማርጀት ፤ በመንገድ ትራፊክ የሚደርስ አደጋ፤ የመሰረተ ልማት ስርቆትና የመንገዶች ባለስልጣን ለመሰረተ ልማት ግምባታ በሚል በሚፈርሱ መንገዶች ምክንያት የሚነኩ ገመዶች የሃይል መቆራረጥ ያስከትላሉ ብለዋል፡፡

አቶ መላኩ በነዚህ ምክኒያቶች የሚፈጠረዉን የሃይል መቆራረጥ ለመጠገን በተለያዩ አካባቢዎች የኤሌክትሪክ ሃይል በፈረቃ ለማቋረጥ እንገደዳለን ፤ ለደረሱትም ጉዳቶች ከሚመለከታቸዉ አካላት ጋ በጋራ እየሰራን እንገኛለን ሲሉም አንስተዋል፡፡

በተለይም በበአላት ወቅት ህብረተሰቡ ቤቱን ለማስጌጥ እና ከፍተኛ የሀይል ፍጆታ ያላቸዉን የኤሌክትሪክ መገልገያዎችን ስለሚጠቀም ነባር በሆነዉ ኔትወርክ ላይ ከፍተኛ የሆነ መጨናነቅ ስለሚያጋጥ ማህበረሰቡ የሃይል አቅርቦትን ያገናዘበ ሃይል ቆጣቢ መገልገያዎችን እንዲጠቀሙም አሳስበዋል፡፡

በመጨረሻም ከበአሉ በፊት የሃይል መጨናነቅ እንዳያጋጥም የቅድመ ክፍያ አገልግሎት ያለሰልፍ በዘረጋናቸዉ ዘመናዊ የክፍያ ስርአት እንደ ፖስ ማሽን፤ ሞባይል ባንኪንግ በመሳሰሉት አገልግሎት ማግኘት እንደሚቻል ተናግረዋል፡፡

ቤዛዊት አራጌ
ነሐሴ 26 ቀን 2014 ዓ.ም
1.1K viewsedited  10:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 08:54:46 የዛሬው የኢትዮ ማለዳ ዜናዎቻችን 26-12-14

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።

Telegram https://t.me/ethiofm107dot8

Twitter https://twitter.com/EthioFM

YouTube https://www.youtube.com/channel/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos

Facebook https://www.facebook.com/onelovebroadcast

Website https://ethiofm107.com/

ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 6321 ላይ ይላኩልን።

ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።
2.0K views05:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 17:41:54

2.8K views14:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 17:34:28
ቼልሲ ፎፋናን አስፈርሟል፡፡

የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ፈረንሳዊውን የመሃል ተከላካይ በ70 ሚ.ፓ ለሰባት ዓመት በሚዘልቅ ውል በእጁ አስገብቷል፡፡

ለፈረንሳይ ከ21 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን የሚጫወተው ፎፋና ሰን ኤቲዬን ለቅቆ ሌስተር ሲቲን የተቀላቀለው በ2020 ነበር ፡፡

በኪንግ ፓወር ቆይታው በ37 የፕሪምየር ሊግ ጨዋታዎች ላይ ተሰልፎ ተጫውቷል ፡፡
በ2021 -22 የውድድር ዘመን እግሩ ላይ ባጋጠመው ጉዳት ተሳትፎው በሰባት የፕሪምየር ሊግ ጨዋታዎች ብቻ ተገድቧል ፡፡
‹‹ ያለፉት ሁለት ቀናት ለእኔ ልዩ ትርጉም ነበራቸው ፡፡
በጣም ደስ ብሎኛል ፡፡
ዛሬ ከቡድኑ ጋር ልምምድ ሰርቼያለሁ፡፡ ለደጋፊዎች እና ለክለቡ ለመጫወት ጓጉቼያለሁ ›› ብሏል ፎፋና ፊርማውን ካኖረ በኋላ ፡፡

በአቤል ጀቤሳ

ነሐሴ 25 ቀን 2014 ዓ.ም
2.8K views14:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 16:45:08
2.7K views13:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 09:00:19 የዛሬው የኢትዮ ማለዳ ዜናዎቻችን 25-12-14

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።

Telegram https://t.me/ethiofm107dot8

Twitter https://twitter.com/EthioFM

YouTube https://www.youtube.com/channel/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos

Facebook https://www.facebook.com/onelovebroadcast

Website https://ethiofm107.com/

ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 6321 ላይ ይላኩልን።

ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።
3.3K views06:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 08:29:37
የቀድሞው የሶቪየት ህብረት መሪ ሚካኤል ጎሮቫቾቭ አረፉ።

ቀዝቃዛው የዓለም ጦርነት በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታ አስችለዋል የሚባሉት ጎርቫቾቭ በ91 ዓመታቸው ነው ያረፉት።

ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በጎርቫቾቭ ሞት ማዘናቸውን ገልፀዋል።

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን

ነሐሴ 25 ቀን 2014 ዓ.ም
410 views05:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 00:13:37

1.4K views21:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 18:50:22

2.2K views15:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ