Get Mystery Box with random crypto!

Ethio Fm 107.8

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiofm107dot8 — Ethio Fm 107.8 E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiofm107dot8 — Ethio Fm 107.8
የሰርጥ አድራሻ: @ethiofm107dot8
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.32K
የሰርጥ መግለጫ

በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

3

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 97

2022-09-02 12:17:17

1.0K views09:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 11:39:51
የማይናማሯ የቀድሞ መሪ አዉንግ ሳንሱኪ በምርጫ ማጭበርበር የ 3 ዓመት ፍርድ ተፈረደባቸዉ፡፡


ይህ የ 3ዓመት ፍርድ ከዚህ በፊት በወታደራዊዉ የማይናማር መንግስት በተፈረደባቸዉ 17 ዓመት የእስር ጊዜ ላይ የሚጨመር ነዉ፡፡

ሳንሱኪ በምርጫ ማጭበርበር ወንጀል የ3 ዓመቱ ፍርድ ከከባድ የስራ ጫና ጋር የተፈረደባቸዉ ሲሆን፣ ከዚህ በፊት በተለያዩ ወንጀሎች ከተፈረደባቸዉ የ 17 ዓመት እስር ላይ የሚጨመር መሆኑም ነዉ የተገለጸዉ፡፡

ሳንሱኪ በ2020 ህዳር ወር ላይ በተደረገዉ ምርጫ ላይ ፓርቲያቸዉ በከፍተኛ የበላይነት አሸንፏል በማለት ምርጫ አጭበርብረዋል ነዉ የተባለዉ ፡፡

በዚህ ወንጀል የተነሳ በተፈረደባቸዉ ፍርድ ሳንሱኪ ለሚቀጥሉት 20 ዓመታት ከፖለቲካዉ ርቀዉ ይቆያሉ የተባለ ሲሆን፣ ወታደራዊዉ መንግስት በሳንሱኪ ዙሪያ ከዚህ በኋላ የሚከሰዉ እና ለፍርድ የሚያቀርባቸዉ ብዙ ወንጀሎች አሉት ነዉ የተባለዉ፡፡


የኖቤል ሽልማት ተሸላሚዋ እና የማይናማር ተቃዋሚ ፓርቲ ቀንደኛ መሪ አዉንግ ሳንሱኪ ባለፈዉ ዓመት በመፈንቅለ መንግስት ከስልጣን መዉረዳቸዉ የሚታወስ ነዉ፡፡

ወታደራዊ መንግስቱ ወደ ስልጣን ከመጣ ወዲህ በተፈጠሩ ግጭቶች ከ 2ሺህ 200 በላይ የሚሆኑ ዜጎች ህይወታቸዉን ያጡ ሲሆን ፣ ከ 15ሺህ በላይ የሚሆኑት ደግሞ ለእስር ተዳርገዋል ሲል የዘገበዉ አልጀዚራ ነዉ፡፡

በእስከዳር ግርማ

ነሐሴ 27 ቀን 2014 ዓ.ም
1.4K views08:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 09:14:40 የዛሬው የኢትዮ ማለዳ ዜናዎቻችን 27-12-14

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።

Telegram https://t.me/ethiofm107dot8

Twitter https://twitter.com/EthioFM

YouTube https://www.youtube.com/channel/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos

Facebook https://www.facebook.com/onelovebroadcast

Website https://ethiofm107.com/

ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 6321 ላይ ይላኩልን።

ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።
1.9K views06:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 19:30:00 ቦሌ አራብሳ ኮንዶሚንየም የተፈጠረው ምንድነው ?

ኢትዮ ኤፍኤም 107.8 ከአዲስ አበባ ፓሊስ ኮምሽን ያገኘው ይሄን ይመስላል፡፡

በአዲስ አበባ ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 ቦሌ አራብሳ ኮምዶሚኒየም በሁለት ህፃናት ላይ የተፈፀመው የግድያ ወንጀል፤ የተፈፀመው ከጠዋቱ አራት ሰዓት ላይ ነው፡፡

በቤት ሰራተኝነት ተቀጥራ በምትሰራ ወንጀል ፈፃሚ አማካኝነት ክርስቲያን መላኩና ወንጌላዊት መላኩ የተባሉ የሁለት ዓመትና የሶስት አመት ህፃናት ህይወት አልፏል፡፡

የአዲስ አበባ ፓሊስ ኮምሽን ም/ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ለኢትዮ ኤፍኤም እንደተናገሩት ወንጀል ፈፃሚው በቁጥጥር ስር ውላለች፡፡

የህፃናቱ ህይወት በወንጀል ፈፃሚዋ እንዴት እንዳለፈና ሌሎችንም መረጃዎች ፓሊስ ተጨማሪ መረጃ እያጣራ እንደሚገኝ እና ህብረሰተቡም እንዲረጋጋም ም/ ኮማንደር ማርቆስ አደራ ብለዋል፡፡

በየውልሰው ገዝሙ
3.4K views16:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 19:21:16

3.3K views16:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 14:25:58
ዛሬ በክቡራት እና ክቡራን
ከ10:00 - 12:00
እንግዳችን አቶ ታዬ ተፈሪ ይባላሉ፡፡

በግል ኢንቬስትመንት ዘርፍ ተሰማርተው ለበርካታ ኢትዮጵያዊያን የስራ እድል መፍጠር ችለዋል፡፡

የግብርና ምርቶችን ወደ ውጭ ሀገር በመላክ የውጭ ምንዛሪ ያስገኙ ሲሆን ከውጭ ሀገር የሚገቡ ምርቶችን ሀገር ውስጥ በማምረትና በመገጣጠም የውጭ ምንዛሪ ማስቀረትም ችለዋል፡፡

በተጨማሪም ማህበራዊ ሃላፊነታቸውን በተለያዩ ጊዜያት በመወጣት ይታወቃሉ፡፡ ከአነስተኛ የንግድ ስራ እስከ ከፍተኛ የግል ባለሀብትነት የደረሰው ጎዞአቸውን የሚዳስሰውን ፕሮግራማችንን እንድትከታተሉን ተጋብዛችኋል፡፡

በክቡራት እና ክቡራን

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።

Telegram https://t.me/ethiofm107dot8

Twitter https://twitter.com/EthioFM

YouTube https://www.youtube.com/channel/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos

Facebook https://www.facebook.com/onelovebroadcast

Website https://ethiofm107.com/

ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 6321 ላይ ይላኩልን።

ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።
718 views11:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 13:50:06
ለውጭ ማስታወቂያ የሚሆን መሬት በጨረታ ሊቀርብ ነው፡፡

የውጭ ማስታወቂያ አገልግሎት ለሚሰጡ ድርጅቶች መሬት በጨረታ ሊቀርብላቸው መሆኑ ተሰምቷል፡፡
የውጭ ማስታወቂያ አገልግሎት ይሰጡ የነበሩ ድርጅቶች ከዚህ በፊት ባገኙት ቦታ ይጠቀሙ የነበረ ሲሆን ከዚህ በኃላ ለቁጥጥር እንዲያመች ድርጅቶች ግልጽ እና የታወቀ ቦታ ሊኖራቸው ይገባል ተብሏል፡፡

እንደዚሁም በመዲናዋ የአገልግሎት ጊዜያቸው ያለፈባቸው ከ22ሺህ በላይ የውጭ ማስታወቂያዎች ሊነሱ ነው፡፡

ህገ ወጥ ናቸው የተባሉ የአገልግሎት ጊዜያቸው ያለፈባቸው የውጭ ማስታወቂያዎች እንደሚነሱ ነው የተገለጸው፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ የግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን የውጭ ማስታወቂያ ቁጥጥር ዳሬክተር የሆኑት አቶ አዲሱ መለሰ በሚቀጥለው 2015 አመት ከውጪ ማስታወቂያ ጋር በተያያዘ ሰፊ ስራ ለመስራት ዝግጅት መጠናቀቁን ተናግረዋል፡፡

ከተማዋ ከዚህ በፊት ያልነበራት የውጭ ማስታወቂያ መመርያ እና ደንብ ማዘጋጀቷን የተናገሩት አቶ አዲሱ ለ6ሺህ 992 ድርጅቶች የውጭ ማስታወቂያ ፍቃድ ይሰጣል ብለዋል፡፡

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን
ነሐሴ26 ቀን 2014 ዓ.ም
1.1K views10:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 13:38:52
የኬኒያ ፍርድ ቤት ራይላ ኦዲንጋ በምርጫ ውጤት ላይ ያቀረቡትን ክስ ማየት ጀምሯል፡፡

ሚሊያም ሩቶ አሸንፈዋል ተብሎ የነበረው የኬኒያ ምርጫ በተፎካካሪው ራይላ ኦዲንጋ ተቃውሞ እንደገጠመው አይዘነጋም፡፡

የምርጫ ውጤቱ ተጭበርብሯል ያሉት ራይላ ኦዲንጋ ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት መውሰዳቸው ይታወሳል፡፡
ራይላ በፈረንጆቹ 2017 በተመሳሳይ መልኩ የምርጫው ውጤት አልቀበልም ብለው ፍድቤት መውሰዳቸው ይታወሳል፡፡

ለአምስት ተከታታይ አመታት በምርጫ ተወዳድረው ያልተሳካላቸው ራይላ ኦዲንጋ ፍትህ እንፍልጋለን እያሉ ይገኛሉ፡፡

በማርታ ኮሜ የሚመራው የኬኒያ ፍርድ ቤት ራይላ ኦዲንጋ ያቀረቡትን ክስ እየመረመሩ እንደሚገኙ ተናግረዋል፡፡

እጩ ተወዳዳሪው እና ደጋፊዎቻቸው የክስ ሂደቱ እስኪያልቅ ድረስ ከጸብ አጫሪነት ሊቆጠቡ ይገባልም ብለዋል፡፡

ከዚሁ ጋር በተያያዘም በ2017 ከነበረው ምርጫ ጋር በተያያዘ ተፈጥሮ በነበረው ግጭት ልጆቻቸውን በሞት ያጡ ቤተሰቦች ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር እንዲደረግ ጠይቀዋል፡፡

አሁን በሀገራችን ሌላ ችግር እንዲከሰት አንፈልግም የሚሉት እነዚህ ቤተሰቦች መሪዎች እና ደጋፊዎቻቸው በተረጋጋ ሁኔታ የክሱን ውጤት እንዲጠብቁም አሳስበዋል፡፡

አፍሪካ ኒውስ ዘግቦታል

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን

ነሐሴ26 ቀን 2014 ዓ.ም
1.1K views10:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 13:33:19
የጎጆ ብሪጅ ሀውሲንግ በመጪው መስከረም 10/ 2015 ዓ.ም ዕጣ እንደሚያወጣ አስታወቀ

የጎጆ ብሪጅ ሃውሲንግ ትሬዲንግ ከዚህ ቀደም ጳጉሜ 03/2014 ዓ.ም ይወጣል ብሎ የነበረውን የዕጣ ማውጣት ስነሥርዓት ወደ መስከረም 10/2015 ዓ.ም መቀየሩን አስታውቋል ።

ዕጣ የሚወጣበት ጊዜ የተቀየረበት ዋነኛው ምክንያት አዲስ ተመዝጋቢ አባላት ጥያቄ በማቅረባቸውና የአባላቱን ቁጥር ለመጨመር እንደሆነም ተናግሯል ።
ኀየጎጆ ሃውሲንግ ትሬዲንግ ምክትል ዳይሬክተር አቀ ናደው ጌታሁን በሰጡት መግለጫ በዕጣ ማውጣት ስነስርዓቱ ላይ አዲስ የተመዘገቡ 4 መቶ አባላት የሚደራጁበትን ቦታ እንዲያውቁ ይደረጋል ብለዋል።

ከዚህ በተጨማሪም የጎጆ ሃውሲንግ ያለቁ 4 ሳይቶችና ለማህበራቱ ካርታ ርክክብ እንዲሁም 4 የሳይቶች የግንባታ ፍቃድ ርክክብ እንደሚከናወን አቶ ናደው አስታውቀዋል ።

በዕለቱ ለጤና ባለሙያዎች የመኖሪያ መንደር ለመገንባት ከጤና ሚኒስቴርና ከዳሽን ባንክ ጋር የመግባቢያ ስምምነት እንደሚያደርግም ታውቋል።

የጎጆ ብሪጅ ሃውሲንግ እስካሁን 4 ሳይቶች፣ 8 ማህበራት ፣ እና ከ 1 ሺህ በላይ አባላትን ማፍራት መቻሉም በመግለጫው ተነስቷል።

ጎጆ ብሪጅ ሃውሲንግ በከተማዋ ያለውን የቤት ችግር ለመቅረፍ እየሰራ የሚገኝ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ነው ተብሏል ።

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን
ነሐሴ 26 ቀን 2014 ዓ.ም
1.1K views10:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 13:32:27
ቻይና ሰብዓዊነትን የሚጣረስ ወንጀል ሳትፈጽም አትቀርም ብሏል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፡፡

የቻይና በአግላይነት እና በዘፈቀደ እስር ቤት ያስገባቻቸዉ የዩጉር ጎሳ ተወላጅ እና ሌሎች ሙስሊሞች ላይ ምናልባት የሰብዓዊ መብት ጥሰት ሳትፈጽም አልቀረችም ብሏል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሪፖርቱ፡፡

የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ሚሼል ባችሌት በቻይና ላይ ባላቸዉ የተለሳለሰ አቋም በብዙ ዲፕሎማቶች እና የመብት ተሟጋች ሲተቹ ቢቆዩም የአራት ዓመት የስራ ዘመናቸዉ ሊያበቃ ደቂቃዎች ሲቀሯቸዉ ሪፖርቱን ይፋ አድርገዋል፡፡

48 ገጽ ያለዉ ሪፖርቱ ቻይና በተከተለቻቸዉ የሽብር እና የጽንፈኝነት ምላሽ ስትራቴጂ ምክንያት በዢንጂያንግ ግዛት ዉስጥ ከባድ የሆነ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ወንጀል ፈጽማለች ብሏል፡፡

የሰብዓዊ መብቶች ቢሮ እንደገለጸዉ በዩጉር ጎሳ ተወላጅ ሙስሊሞች እና በሌሎች የሙስሊም ማህበረሰቦች ላይ በዘፈቀደ በተፈጸመ እስር ምክንያት በቻይና መንግስት አለምዓቀፋዊ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ወንጀል መፈጸሙን ገልጿል፡፡

ሚሼል ባችሌት የቻይና መንግስት እነዚህን በየካምፑ እንዲሁም በተለያየ የማቆያ ስፍራዎች የታሰሩ ሁሉንም ዜጎች እንዲፈታ አዘዋል፡፡

የተለያዩ የመብት ተሟጋች ድርጅቶች ቻይናን በምታደርሰዉ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ምክንያት ሲወቅሱ ቆይተዋል፣ አሜሪካም ቻይናን በዘር ጭፍጭፋ ከሳታለች፡፡

ቻይና በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የወጣዉን ሪፖርት በፍጹም አልቀበልም ስትል 131 ገጽ ያለዉ ሪፖርት አስገብታለች፡፡

በጉዳዩ ላይ ብዙ ቁጥር ያላቸዉ ሙስሊሞች ቻይና የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ታቁም በሚል ለተቃዉሞ አደባባይ መዉጣታቸዉን የዘገበዉ ሮይተርስ ነዉ፡፡

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን
ነሐሴ 26 ቀን 2014 ዓ.ም
963 views10:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ