Get Mystery Box with random crypto!

Ethio Fm 107.8

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiofm107dot8 — Ethio Fm 107.8 E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiofm107dot8 — Ethio Fm 107.8
የሰርጥ አድራሻ: @ethiofm107dot8
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.32K
የሰርጥ መግለጫ

በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

3

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 95

2022-09-09 08:24:21
በ2015 በጀት አመት ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ሁለት ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ማቀዱን የግድቡ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽህፈት ቤት አስታወቀ።


የግድቡን ቀሪ ግንባታ ለማከናወን ለሚያስፈልገው ተጨማሪ 60 ቢሊየን ብር የህዝብ ተሳትፎ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ ቀርቧል።


የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ህዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሔራዊ ምክር ቤት 14ኛ መደበኛ ጉባኤውን ትናንት አካሂዷል።

የግድቡ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽህፈት ቤት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ታገል ቀኑብህ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በኢትዮጵያውያን እውቀትና ገንዘብ እየተገነባ የሚገኘው ታላቁ የህዳሴ ግድብ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ታላላቅ ስኬቶችን አስመዝግቧል።


በሀገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ለግድቡ እያደረጉት ያለው ድጋፍ ተጠናክሮ መቀጠሉንም ጠቅሰዋል።


በሃብት ማሰባሰብ በኩል በ2014 በጀት ዓመት ከ1 ነጥብ 18 ቢሊዮን ብር በላይ መሰብሰቡን ገልጸው፤ በተያዘው 2015 በጀት ዓመት 2 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ መታቀዱን ሰምተናል፡፡


ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን

ጳጉሜ 04 ቀን 2014 ዓ.ም


ለወቅታዊና ታማኝ መረጃዎች የቴሌግራምና የዩቲዩብ ቻናላችንን ይከታተሉን!

Telegram https://t.me/ethiofm107dot8
YouTube https://www.youtube.com/channel/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos
2.8K views05:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-09 07:15:03
ዛሬ በአዲስ አበባ ነጻ የትራንስፖርት አገልግሎት ይሰጣል፡፡


የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ፥ “የአገልጋይነት ቀን”ን ምክንያት በማድረግ ነው የነጻ ትራንስፖርት አገልግሎት እንደሚሰጥ የገለጹት፡፡


በዚህም አዳዲስ የሚሰማሩ አውቶቡሶችን ጨምሮ ፣ ሸገር የብዙኃን ትራንስፖርት አገልግሎት ድርጅትና አንበሳ የከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት ከጠዋቱ 12 ሰዓት እስከ ምሽቱ 3 ሰዓት ድረስ በነፃ አገልግሎት እንደሚሰጡ ገልጸዋል፡፡


ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን

ጳጉሜ 4 ቀን 2014 ዓ.ም
2.8K views04:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-08 22:39:24
የዩናይትድ ኪንግደም የ70 ዓመታት ንግሥት ዳግማዊት ንግሥት ኤልዛቤጥ በ96 ዓመታቸው አረፉ።

የ96 ዓመቷ የዩናይትድ ኪንግደም እና የኮመን ዌልዝ አገራት ንግሥት ኤልዛቤት ዳግማዊት አረፉ።

ንግሥቲቱ ማረፋቸውን የባኪንግሃም ቤተ-መንግሥት ይፋ አድርጓል።

ቀደም ሲል ሐኪሞች የንግሥቲቱ ጤና በአሳሳቢ ሁኔታ ላይ ነው ብለው ነበር።

የንግሥቲቱ የጤና ሁኔታ አሳሳቢ መሆኑን ተከትሎ በርካርታ የንጉሣውያን ቤተሰብ አባላት ንግሥቲቱ ወደሚገኙበት ስኮትላንድ ባልሞር ቤተ-መንግሥት አቅንተው ነበር።

ንግሥት ኤልዛቤት ዳግማዊት በ70 ዓመት የንግሥና ዘመናቸው በርካታ ማኅበራዊ እና ፖለቲካዊ ለውጦችን ተመልክተዋል።

የንግሥቲቱን የጤና አሳሳቢ መሆን ዜና  ከተሰማ በኋላ በርካታ ፖለቲከኞች እና ተዋቂ ግለሰቦች በዜናው መረበሻቸውን ሲገልጹ ነበር።

ንግስት ኤልዛቤጥ ወደ ንግስናው የመጡት እአአ 1952 ነበር።

ንግሥቷ በ70 ዓመታት የንግስና ዘመናቸው በዩኬ እና በመላው ዓለም ብዙ ማሕበራዊ ለውጦች ተከናውነዋል።

የንግሥት ኤልዛቤጥ ሞትን ተከትሎ የመጀመሪያ ልጃቸው ቻርልስ የዩናይትድ ኪንግደም እና የኮመንዌልዝ አገራት ንጉሥ መሆናቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን

ጳጉሜ 03 ቀን 2014 ዓ.ም
3.2K views19:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-08 09:23:51
Thank you #Wake & Bake Pastry
559 viewsedited  06:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-08 09:15:20 የዛሬው የኢትዮ ማለዳ ዜናዎቻችን 03-13-14

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።

Telegram https://t.me/ethiofm107dot8

Twitter https://twitter.com/EthioFM

YouTube https://www.youtube.com/channel/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos

Facebook https://www.facebook.com/onelovebroadcast

Website https://ethiofm107.com/

ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 6321 ላይ ይላኩልን።

ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።
647 views06:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-07 18:02:19

2.1K views15:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-07 17:47:09
በካታር የዓለም ዋንጫ ‹‹በተመረጡ የስታዲየም ክፍሎች›› አልኮል ይቀርባል፡፡

በ2022ቱ የዓለም ዋንጫ ‹‹ በተመረጡ የስታዲየም ክፍሎች›› አልኮል እንደሚቀርብ አዘጋጆቹ ተናግረዋል ፡፡
የፊፋ የዓለም ዋንጫ በሙስሊም ሃገር በመካከለኛው ምስራቅ ሲከናወን ይህኛው ለመጀመሪያ ጊዜ ነው ፡፡
በእስልምና ደግሞ አልኮል መጠጣት ይከለከላል ፡፡

በዋና ከተማዋ ዶሃ 40 ሺ ሰዎችን ማስተናገድ የሚችል ለደጋፊዎች በተከለለ ቦታ ግን መጠጥ እንደሚሸጥ ማረጋገጫ ተሰጥቷል ፡፡

‹‹ሰዎች ወደዚህ መጥተው ፈጽሞ የማይረሱትን ተሞክሮ ገብይተው እንዲሄዱ እንፈልጋለን ›› በማለት ዋና ስራ አስፈጻሚው ናስር አል ካተር ለቢቢሲ ተናግረዋል ፡፡
አልካትር ‹‹ የአልኮል ስትራቴጂያችንን በማጠናቀቅ ላይ ነን›› እስከዚያው ግን በስታዲየሙ ዙሪያ ደጋፊዎች መጠጥ የሚጎነጩበትን መንገድ ይፋ አድርገናል ብለዋል ፡፡
ፊፋ የጨዋታ መግቢያ ትኬት የያዙ ደጋፊዎች ከጨዋታው መጀመር እና መጠናቀቅ በኋላ በስታዲየሙ ዙሪያ መጠጥ የሚጎነጩበት አማራጭ እንደሚኖራቸው አሳውቋል ፡፡

በአቤል ጀቤሳ
ጳጉሜ 02 ቀን 2014 ዓ.ም
2.2K views14:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-07 17:20:41

2.1K views14:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-07 13:12:01
ቱክል ተሰናበቱ

የቼልሲው አሰልጣኝ ቶማስ ቱክል ከትላንቱ የቻምፒየንስ ሊግ ሽንፈት በኋላ ተሰናብተዋል ፡፡ የቀድሞው የቦሩሲያ ዶርትሙንድ እና ፒኤስጂ አሰልጣኝ ከ20 ወራት በኋላ የስታምፎርድ ብሪጅ እህል ውሃቸው ተቋርጧል ፡፡

ጀርመናዊው በሰማያዊዎቹ ቤት ባሳለፉት ጊዜ የቻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን ማሸነፋቸው ይታወቃል ፡፡ ይህንን ያደረጉት በተሸሙ በአራት ወራቸው መሆኑ አስመስግኗቸው ነበር ፡፡ የዩኤፋ ሱፐር ካፕ እና የክለቦች የዓለም ዋንጫንም አሸንፈዋል ፡፡

የዘንድሮውን የውድድር ዘመን የጀመሩበት መንገድ ግን ትችት ሲያሰነዝርባቸው ነበር ፡፡ በክረምቱ የዝውውር መስኮት ለተጫዋቾች ዝውውር ከፕሪምየር ሊግ ክለቦች ሁሉ ቀዳሚ የሆነው ክለብ በቡድኑ ላይ ከፍተኛ መሻሻል ባለማሳየቱ አሰልጣኙ የስንብት ደብዳቤ እንዲቆረጥላቸው አስገድዷል ፡፡

ቶድ ቦህሊ አዲስ አሰልጣኝ እስከሚሾም ድረስ የአሰልጣኝ ቡድኑ አባላት በሃላፊነት እንዲመሩ ወስነዋል ፡፡
አዲስ አሰልጣኝ ለመሾም ‹‹ትክክለኛው ጊዜ ነው ›› ሲሉም ባወጡት መግለጫ አሳውቀዋል ፡፡

በአቤል ጀቤሳ
2.8K views10:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-06 12:20:29
1.7K views09:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ