Get Mystery Box with random crypto!

Ethiopian Electric Utility

የሰርጥ አድራሻ: @eeuethiopia
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 24.33K
የሰርጥ መግለጫ

EEU Official Telegram Channel
Web: www.eeu.gov.et

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 41

2022-09-03 12:00:58
የኢኤአ የሳምንቱ አበይት መረጃዎች ሲታወሱ
*************
• ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳብ እንዴት በቀላሉ ማወቅ እንደሚቻል የሚያሳይ መረጃ፣

• ለፍጆታ የተሰጠን የኤሌክትሪክ ኃይል ያላግባብ መጠቀም ጉዳቱና ተጠያቂነት፣

• ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ በቴሌ ብር መተግበሪያ ለመክፈል የሚያስችሉ ቅድመ ተከተሎች፣

• በኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማት ላይ የሚፈፀም ስርቆትና የሚያስከትለው ተጠያቂነት፣

• የተቋሙ መሰረታዊ ሠራተኛ የ2014 በጀት ዓመት አፈፃፀምና የኦዲት ሪፖረት ማድመጥ እንዲሁም የቀጣይ በጀት የትኩረት አቅጣጫዎችን ለማስቀመጥ ዓመታዊ ጉባዔ ማካሄዱን፣

• የኤሌክትሪክ አገልግሎት ለማግኘት የሚያስፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎችን፣

• ኤሌክትሪክ እና የሚያከትለው አደጋ፣

• ተቋሙ በመጪው አዲስ ዓመት የኃይል መቆራረጥ ለመቀነስ እያከናወናቸው የሚገኙ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች፣

• የደቡብ እና ምዕራብ አዲስ አበባ ዲስትሪክቶች መጪው አዲስ ዓመትን አስመልክቶ ያከናወኑዋቸው አስፈላጊ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች አበይት መረጃዎቻችን ነበሩ፡፡

ሠናይ ቅዳሜና ዕሁድ እንዲሆንላችሁ ተመኘን!

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

ወቅታዊና ትኩስ የተቋማችን መረጃዎች ወዲያውኑ እንዲደርሳችሁ እነዚህን የትስስር ገፆቻችንን ይወዳጁ፡-

ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/EEUOfficial/
ቲዊተር፡ https://twitter.com/EEUEthiopia
ቴሌግራም፡ t.me/eeuethiopia
ዩቱዩብ: https://www.youtube.com/c/EthiopianElectricUtility
ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et
309 views09:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-03 09:02:57 ዲስትሪክቶቹ ለበዓሉ አስፈላጊ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እያከናወኑ መሆኑን አስታወቁ
*****************
የ2015 ዓ.ም የዘመን መለወጫ በዓልን ምክንያት በማድረግ በህብረተሰቡ ዘንድ የሚኖረውን የኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጎት ለማርካት፣ መቆራረጥና መዋዥቅን ለመቀነስ የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እያከናወኑ መሆኑን የምዕራብና የደቡብ አዲስ አበባ ዲስትሪክቶች አስታውቀዋል፡፡

ክብረ በዓላት ከመድረሳቸው አስቀድሞ ተደጋጋሚ የኃይል መቆራረጥ የሚስተዋልባቸው አካባቢዎችን በመለየት በልዩ ሁኔታ ትኩረት በመስጠት ኤሌክትሪክ እንዳይቋረጥ የቅድመ ጥገናና መከላከል ሥራዎች እንደሚሰሩ የምዕራብ አዲስ አበባ ዲስትሪክት ዳይሬክተር አቶ አብዱ መሀመድ አስታውሰዋል፡፡

ከዚህ ጋር ተያይዞ መጪውን አዲስ ዓመት በዓል ምክንያት በማድረግ በዲስትሪክቱ ከ50 ኪ.ሜ በላይ የመካከለኛ እና ከ80 ኪ.ሜ በላይ የዝቅተኛ መስመር የጥገና ስራዎች መጠናቀቃቸውን ገልፀው፤ ለስምንት ትራንስፎርመሮች ተጨማሪ አጋዥ ትራንስፎርመሮች የመትከል ስራ መሰራቱን አስታውቀዋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ የትራንስፎርመሮች የኃይል ጭነት የማመጣጠን፣ ለመቆራረጥ መንስኤ ሚሆኑ የዛፍ ቅንርንጫፎችን የማጽዳት ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡

በተመሳሳይ የደቡብ አዲስ አበባ ዲስትሪክት የዲስትሪቡሽን ኃላፊ አቶ ሱለጣን ሰርሞሎ በበኩላቸው በአዲሱ በጀት ዓመት ያልተቆራረጠ አገልግሎት ለመስጠት የተለያዩ የመልሶ ግንባታ ስራዎች እየተከናወኑ መሆን ጠቅሰው፤ መጪውን አዲስ አመት በማስመልከትም እንደ ከዚህ ቀደሙ አስፈላጊ የቅድመ ጥንቃቄ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የበዓሉን ዋዜማ ጨምሮ በዕለቱ የኃይል መቆራረጥ እንዳይከሰት የኤሌክትሪክ መስመሮች ላይ ችግር ከመፈጠሩ በፊት የሚቆጣጠር፣ የኃይል መቋረጥ ሲከሰት አስቸኳይ ጥገና የሚያደርግ እንዲሁም የሠራተኞችን የሥራ ላይ ደህንነት ለማስጠበቅ የደህንነት ትጥቆችን አድርገው እንዲሰሩ ክትትል የሚያደርግ ግብረ ሃይል መቋቋሙንም ገልፀዋል፡፡

አቶ ሱለጣን እንደገለፁት በአዲሱ በጀት ዓመት ከፍተኛ የኃይል መቆራረጥ በሚከሰትባቸው ኮዬ ፈጬ፣ ቂሊንጦ፣ ለቡ፣ ጀሞ 1፣ ጀሞ 2 እንዲሁም ጀሞ 3 አካባቢዎች ላይ በአጠቃላይ የ9 ነጥብ 5 ኪ.ሜ የመካከለኛ እና 6 ኪ.ሜ የዝቅተኛ መስመር የመልሶ ግንባታ ስራዎች መከናወናቸውን ጠቁመዋል፡፡

በተጨማሪም ለ108 ኪ.ሜ የመካከለኛ እና ለ140ኪ.ሜ የዝቅተኛ መስመር ቅድመ ጥገና መደረጉን እንዲሁም በተለያዩ አካባቢዎች ለስምንት ተራንስፎርመሮች አጋዥ ትራንስፎርመሮች መተከሉን ገልፀዋል፡፡

በባለፈው በጀት ዓመት በሰበታ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በተከሰተ የትራንስፎርመር መቃጠል ምክንያት ጀሞ 2 እና ጀሞ 3 አካባቢዎች ተደጋጋሚ የኃይል መቋረጥ እንደነበረ አስታውሰው፤ በወቅቱ መስመሩን ወደ መካኒሳ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በመስጠት ጊዜያዊ መፍትሄ እንደተሰጠው፤ ኋላም 8 ኪሜ አዲስ መካከለኛ ኃይል ተሸካሚ መስመር በመዘርጋት ችግሩን መቅረፍ ተችሏል ብለዋል፡፡

ለቅድመ ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኞችም ካርድ ለመሙላት እንዳይቸገሩ ከኃላፊ እስከ ጥገና ሰራተኞች ያካተተ ግብረ ኃይል በማዋቀር አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የዲስትሪክቶቹ የስራ ሃላፊዎች አስታውቀዋል፡፡

በመጨረሻም ህብረተሰቡ አገልግሎት አሰጣጡን የሚያደናቅፉ ተግባሮች ሲመለከት እንዲሁም ከተቋሙ እውቅና ውጪ የኤሌክትሪክ አስተላላፊ መስመሮችን የሚነካኩ ግለሰቦች ሲመለከት ለህግ አካላት አልያም ለተቋሙ ጥቆማ በመስጠት የተለመደ ትብበሩን እንዲያደረግ ጠይቀዋል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

ወቅታዊና ትኩስ የተቋማችን መረጃዎች ወዲያውኑ እንዲደርሳችሁ እነዚህን የትስስር ገፆቻችንን ይወዳጁ፡-

ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/EEUOfficial/
ቲዊተር፡ https://twitter.com/EEUEthiopia
ቴሌግራም፡ t.me/eeuethiopia
ዩቱዩብ: https://www.youtube.com/c/EthiopianElectricUtility
ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et
1.6K viewsedited  06:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-03 09:02:54
1.6K views06:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 15:22:28 በመጪው አዲስ ዓመት የኃይል መቆራረጥ ለመቀነስ የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተከናወኑ ነው
************************
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በመጪው የ2015 አዲስ ዓመት የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ ለመቀነስ የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እያከናወነ መሆኑን በተቋሙ የዋና ስራ አስፈፃሚ ከፍተኛ የቴክኒክ አማካሪ አቶ አስናቀ ታምሩ ገልፀዋል፡፡

እንደ አቶ አስናቀ ገለፃ ተቋሙ በበዓሉ ዋዜማና በዕለቱ ሊከሰት የሚችለውን የኃይል መቆራረጥ ችግር ለመከላከልና ለመቀነስ፣ ሲከሰትም አፋጣኝ ምላሽ የሚሰጥ የአስቸኳይ ጥገናና ቅደመ-መከላከል ግብረ ሃይል በማቋቋም ወደ ስራ ገብቷል፡፡

ግብረ ሃይሉ ከኮርፖሬት ጀምሮ በሁሉም ሪጅኖች፣ ዲስትሪክቶችና አገልግሎት መስጫ ማዕከላት መቋቋሙንም ከፍተኛ አማካሪውና የግብረ ሃይሉ ሰብሳቢው ተናግረዋል፡፡

በቅድመ ዝግጅቱም የኤሌክትሪክ ስርጭት መስመሮችንና ትራንስፎርመሮችን የመፈተሽ፣ የኃይል ጭነት የማመጣጠን፣ ችግር ያለባቸውን የመለየትና የመጠገን፣ የዘመሙ ምሰሶዎችን የማቃናት፣ የረገቡ ሽቦዎችን የማስተካከል እና ለኃይል መቆራረጥ መንስዔ የሆኑ የዛፍ ቅርንጫፎችን የማፅዳት ሥራ በሰፊው እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡

ይህንንም በአግባቡ እንዲከናወን ከኮርፖሬት ጀምሮ እስከታችኛው መዋቅር ድረስ ተከታታይነት ያለው የክትትልና ቁጥጥር ሥራ በመከናወን ላይ መሆኑንም አስታውቀዋል፡፡

ሆኖም መሰል ዝግጅት ቢደረግም ኤሌክትሪክ በባህሪው በተለያዩ ምክንያቶች አልፎ አልፎ ሊቋረጥ እንደሚችል በመገመት የተቋቋመው ግብረ ሃይል በበዓሉ ዋዜማና ዕለት ድንገት ኤሌክትሪክ ቢቋረጥ ወዲያው በፍጥነት ለማገናኘት እንደሚሰራም ጠቁመዋል፡፡

ለዚህም አስፈላጊ የሆኑ የዲስትሪቡዩሽን ዕቃዎች፣ ተሽከርካሪዎችና ሌሎች ተጓዳኝ ግብዓቶች እንዲሟሉ አቅጣጫ ተቀምጧል ብለዋል፡፡

በመጨረሻም አማካሪው በበዓል ወቅት ከኃይል አቅርቦት ጋር የተያያዙ ሌሎች ችግሮች እንዳያጋጥሙ ከኢትጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል ጋር በቅንጅት እየተሰራ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

ወቅታዊና ትኩስ የተቋማችን መረጃዎች ወዲያውኑ እንዲደርሳችሁ እነዚህን የትስስር ገፆቻችንን ይወዳጁ፡-

ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/EEUOfficial/
ቲዊተር፡ https://twitter.com/EEUEthiopia
ቴሌግራም፡ t.me/eeuethiopia
ዩቱዩብ: https://www.youtube.com/c/EthiopianElectricUtility
ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et
4.4K views12:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 15:22:10
3.6K views12:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 15:21:56
3.6K views12:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 09:27:28 ኤሌክትሪክ እና የሚያከትለው አደጋ
*************
ኤሌክትሪክ ለአንድ ሃገር የማህበራዊና ኢኮኖሚዊ ልማት ስኬት የሚጫወተው ሚና እጅግ የጎላ ነው፡፡ ከእያንዳንዱ ተጠቃሚ የዕለት እንቅስቃሴ ጀምሮ እስከ ከፍተኛ ኢንዱስትሪ ድረስ የኤሌክትሪክ አገልግሎት የሚጫወተው ሚና በቀላሉ ተጠቅሶ አያልቅም፡፡

ታዲያ ይህ እጅግ አስፈላጊና የልማቱ የጀርባ የሆነው ኤሌክትሪክ በአግባቡና በጥንቃቄ ካልተጠቀምነው በአካልና በንብረት ላይ የሚያደርስው አደጋ ከፍተኛ መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡

የኤሌክትሪክ አደጋ የማስተላለፊያና የማሰራጫ መስመሮች ተፈጥሮዊና ሰው ሰራሽ በሆኑ ምክንያቶች ጉዳት ሲደርስባቸው፣ የማስተላለፊያ መስመሮች ሲበጠሱ፣ ገመዶች እርስ በርሳቸው ሲነካኩ እና የኤሌክትሪክ ተሸካሚ ምሰሶዎች ሲወድቁ ባለማወቅ በሚደረግ ንኪኪ ሊከሰት ይችላል፡፡

የመሰረተ ልማት ስርቆት፣ የኤሌክትሪክ ምሰሶና ትራንስፎርመር ባለበት ቅርብ ርቀት ላይ ግንባታ ወይም የንግድ ሥራ ማከናወን፣ በቤት ውስጥ የኤሌክትሪክ ኢንስታሌሽን በባለሞያና በአግባቡ አለማከናወን፣ ቆጣሪ ያለግባብ መነካካትና ሌሎችም ለኤሌክትሪክ አደጋ መከሰት ትልቅ አስተዋፅኦ አላቸው፡፡

የኤሌክትሪክ አደጋ ሲከሰት ከፍተኛ የሆነ የአካል ጉድለት፣ የንብረት ውድመትና የህይወት መሰዋትነት የሚያስከትል በመሆኑ፤ አደጋዎች እንዳይከሰቱ፣ ከተከሰቱም ጉዳት ሳያደርሱ ለመከላከል የሚያስችሉ ተግባራትን ማከናወን ያስፍልጋል፡፡

በዚህ ረገድ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በአካልና በህይወት ሊደርስ የሚችለውን የኤሌክትሪክ አደጋ ለመቀነስ በርካታ ስራዎችን እያከናወነ ሲሆን፤ ለህብረተሰቡ ግንዛቤን የሚያሳድጉ መረጃዎችን ከማድረስ በተጨማሪ ለአደጋ መንስኤ የሚሆኑ ያረጁ መሰረተ ልማቶችን የማሻሻልና ዓቅም የማሳደግ ሥራ በየጊዜው እየሰራ ይገኛል፡፡

ለሠራተኞቹም የኤሌክትሪክ አደጋ የሚመለከቱ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና የመስጠት፣ የቅድመ አካባቢያዊና ማህበራዊ ጥናት ማካሄድ፣ የሴፍቲ ኦዲት ማከናወን፣ የስራ ላይ ደህንነት መጠበቂያ መሳሪያዎችን የማሟላት ተግባር በሰፊው እየሰራ ነው፡፡

ተጠቃሚው ህብረተሰብም የኤሌክትሪክ አደጋ እንዳይከሰት ከመከላከል አኳያ የራሱ ሚና መወጣት አለበት፡፡ ሁሉም ደንበኛ የጥራት ደረጃቸውን ከፍ ያሉ መገልገያ ቁሳቁሶችን መጠቀም፣ የቤት ውስጥ ኢንስታሌሽን ስራ በባለሞያ ብቻ ማከናወን፣ የኤሌክትሪክ ምሰሶች በቆሙበት አካባቢ ግንባታዎችና ሌሎች የንግድ ስራዎችን ከመስራት መቆጠብ፣ በኤሌክትሪክ መስመሮች ላይ ልብስና መሰል ፖስተሮችን አለማስቀመጥ፣ ህፃናትን የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ካለባቸው አካባቢዎች እንዲጫወቱ አለመፍቀድ ያስፈልጋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ገመዶች በተለያዩ ምክንያቶች ተበጥሰው ሲወድቁ በእጅ አለመንካትና የተቋረጠውን መስመር በራስ ለማገናኘት አለመሞከር ሊደርስ የሚችለውን አደጋ ለመቀነስ ያስችላል፡፡

ኤሌክትሪክ የማገናኘት ሥራ በቂ ሙያዊ እውቀት የሚጠይቅ የስራ ዘርፍ በመሆኑ ማንኛውም አካል የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመሮችን፣ ትራንስፎርመሮችንና የተቆረጡ የኤሌክትሪክ ገመዶችን ከመንካት ሊቆጠብ ይገባል፡፡

የኤሌክትሪክ መስመሮችን የመጠገን ስራ በሃላፊነት የተሰጠው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በመሆኑ ከተቋሙ ሠራተኞች ውጭ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን የሚነካካ አካል ሲኖር ለህግ አስከባሪ አካላት በማሳወቅ ተጠያቂ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡

በመጨረሻም የ2015 አዲስ ዓመት እየደረሰ በመሆኑና ከወትሮው በተለየ በበዓላት ወቅት የሚኖረው የኤሌክትሪክ አጠቃቀማችን ከፍ ስለሚል አደጋ እንዳይከሰት ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲደረግ እንጠይቃለን፡፡ ከላይ የተዘረዘሩትን ልዩ የጥንቃቄ መንገዶችን በመጠቀም የኤሌክትሪክን አደጋ መከላከል ያስፈልጋል፡፡

ድንገት ያልታሰበ አደጋ ቢደረስ ወይም አጠራጣሪ ነገሮች ከተመለከቱ በአቅራቢያ ከሚገኝ የተቋሙ የአገልግሎት መስጫ ማዕከል በአካል በመሄድ ወይም በ905 ነፃ የጥሪ ማዕከል በመደወል ማሳወቅ ይቻላል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

ወቅታዊና ትኩስ የተቋማችን መረጃዎች ወዲያውኑ እንዲደርሳችሁ እነዚህን የትስስር ገፆቻችንን ይወዳጁ፡-

ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/EEUOfficial/
ቲዊተር፡ https://twitter.com/EEUEthiopia
ቴሌግራም፡ t.me/eeuethiopia
ዩቱዩብ: https://www.youtube.com/c/EthiopianElectricUtility
ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et
3.0K views06:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 09:25:12
2.3K views06:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 14:27:09 የኤሌክትሪክ አገልግሎት ለማግኘት የሚያስፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎች
***********
ለነጠላ ፌዝ ቆጣሪ አዲስ ኃይል ጥያቄ ከሆነ

1. የአመልካቹ የቀበሌ መታወቂያ፣ ፓስፖርት ወይም መንጃ ፈቃድ፣
2. አንድ ጉርድ ፎቶ /3 በ 4/፣
3. የኪራይ ቤት ከሆነ ከባለቤቱ የተሰጠ የስምምነት ደብዳቤ፣
4. ለኃይል ማሻሻያ ወይም ለተጨማሪ ቆጣሪ ከሆነ የኤሌክትሪክ ፍጆታ የመጨረሻ ክፍያ ደረሰኝ፣

5. ጥያቄው ለሽርክና ማህበር ከሆነ በተራ ቁጥር 1 የተጠቀሰው እንደተጠበቀ ሆኖ የሽርክና ማረጋገጫ ሰነድ ኮፒ፤

6. በመንግስታዊ አካል ለሚተዳደሩ ቤቶችና ቦታዎች የሚኖሩ ነዋሪዎች በሁለት መንገድ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆን ይችላሉ፡-

• ቤቱን በመንግስት ስም የተዋዋለ ተከራይ በሚመለከተው የመንግስት አካል ሲፈቀድና ተጠቃሚው ማንነቱን የሚገልፅ መታወቂያ ሲያቀርብ አገልግሎቱ የሚፈቀድለት ሲሆን ነገር ግን ማንኛውም ኃላፊነት ቤቱን የሚያስተዳድረው የመንግስት አካል ይሆናል፡፡

• የመንግስት /የቀበሌ/ ቤት ተከራይ የኪራይ ውል አያይዞ ሲያቀርብ አገልግሎቱን በተከራይ ስም ሊያገኝ ይችላል፡፡ ለሚሰጠው ኃላፊነትም ሙሉ ኃላፊነት የተከራዩ ይሆናል፡፡

• ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ድርጅት ከሆነ ከላይ ከላይ በተራ ቁጥር የተጠቀሰው እንዳለ ሆኖ የድርጅቱ የምዝገባ የምስክር ወረቀት፣ የድርጅቱን ዋና ስራ አስኪያጅ ማንነትንየሚገልፅ መታወቂያ፤

• ኢንስፔክሽን /ማስገመቻ ለነጠላ ፌዝ 90 ብር

ለሶስት ፌዝ እና ለከፍተኛ ኃይል ጠያቂዎች

1. ከላይ ለነጠላ ፌዝ አገልግሎት ከተጠቀሱት ማስረጃዎች በተጨማሪ በባለስልጣን /ኤሌክትሪክ ነክ ሥራ ፈቃድ ባለው ተቋራጭ/ የተሰጠ የውስጥ ኤሌክትሪክ መስመር ምርመራ መጠናቀቁን የሚገልፅ የምስክር ወረቀት እና 14 ኪሎ ዋት እና በላይ የሚጠይቁ ከሆነ የኤሌክትሪክ ዲዛይን ፕላን ማቅረብ አለባቸው፡፡

2. አገሌግልቱን ለመስጠት ለሚከናወኑ የኢንስፔክሽን እና የማስገመቻ ክፍያዎች (በየጊዜው የሚደረገው የዋጋ ክለሳ እንደተጠበቀ ሆኖ ከየካቲት 2013 ዓ.ም ጀምሮ ስራ ሊይ የሚገኘው ከዚህ በታች ተመላክቷል)

• ለባለ ሶስት ፌዝ ቆጣሪ 300 ብር
• ከ24 ኪሎ ዋት እስከ 120 ኪሎ ዋት 500 ብር
• ከ121 ኪሎ ዋት እስከ 1 ሜጋ ዋት 5000 ብር
• ከ 1 ሜጋ ዋት በላይ 10 ሺህ ብር

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

ወቅታዊና ትኩስ የተቋማችን መረጃዎች ወዲያውኑ እንዲደርሳችሁ እነዚህን የትስስር ገፆቻችንን ይወዳጁ፡-

ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/EEUOfficial/
ቲዊተር፡ https://twitter.com/EEUEthiopia
ቴሌግራም፡ t.me/eeuethiopia
ዩቱዩብ: https://www.youtube.com/c/EthiopianElectricUtility
ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et
4.5K viewsedited  11:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 14:27:04
3.3K viewsedited  11:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ