Get Mystery Box with random crypto!

Ethiopian Electric Utility

የሰርጥ አድራሻ: @eeuethiopia
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 24.33K
የሰርጥ መግለጫ

EEU Official Telegram Channel
Web: www.eeu.gov.et

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 40

2022-09-08 12:37:35
ክቡራን ደንበኞቻችን እንኳን ለ2015 አዲስ አመት በሰላም አደረሳችሁ!!

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

ወቅታዊና ትኩስ የተቋማችን መረጃዎች ወዲያውኑ እንዲደርሳችሁ እነዚህን የትስስር ገፆቻችንን ይወዳጁ፡-

ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/EEUOfficial/
ቲዊተር፡ https://twitter.com/EEUEthiopia
ቴሌግራም፡ t.me/eeuethiopia
ዩቱዩብ: https://www.youtube.com/c/EthiopianElectricUtility
ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et
6.4K views09:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-08 11:09:19 የኃይል ጭነት በማይበዛባቸው ሰዓታት ኤሌክትሪክ መጠቀም የላቀ አስተዋፅኦ አለው
************************
መጪው የ2015 አዲስ ዓመት በዓል ዋዜማ ላይ እንገኛለን፡፡ እንደሚታወቀው በዓላት ሲመጡ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ፍላጎት ይጨምራል፡፡ ይህንንም ታሳቢ በማድረግ ተቋማችን አስቀድሞ የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እያከናወነ ይገኛል፡፡

ተቋሙ በበዓሉ ዋዜማና በዕለቱ የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥና መዋዥቅ ችግር ሳያጋጥም ለተጠቃሚው ለማድረስ፣ ችግሩ ከተከሰተም አፋጣኝ የአስቸኳይ ጥገና በማከናወን የተቋረጠውን አገልግሎት መልሶ ለማገናኘት የሚያስችሉ የዝግጅት ሥራዎች በማከናወን ላይ ሲሆን፤ ለዚህም የሚረዳ ከኮርፖሬት ጀምሮ እስከ ታችኛው መዋቅር ድረስ የአስቸኳይ ጥገናና ቅደመ-መከላከል ግብረ-ሃይል አቋቁሟል፡፡

ከኃይል ማመንጫ ጀምሮ እስከ ማሰራጫ መስመር ድረስ የሚያጋጥሙ ችግሮችን በአግባቡ ለመፍታትና አቅርቦቱን ለማሳለጥ እንዲቻል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር በቅንጅት ለመስራት የሚያስችል ዝግጅትም ተደርጓል፡፡

ሆኖም መሰል ዝግጅት ቢደረግም ኤሌክትሪክ በባህሪው በተለያዩ ምክንያቶች አልፎ አልፎ ሊቋረጥ እንደሚችል በመገመት በተለይ የመኖሪያ ቤት የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ደንበኞች በአጠቃቀም ወቅት የራሳቸውን አስተዋፅኦ ማበርከት ይገባቸዋል፡፡

በዋዜማውና በዓሉ እለት ደንበኞች የኤሌክትሪክ አጠቃቀማቸው የኃይል ጭነት በማይበዛባቸው ስዓታት በተለይ ከምሽቱ 4፡00 እስከ ንጋቱ 11፡00 ባለው ጊዜ ቢጠቀሙ አስተማማኝና የማይዋዥቅ ኃይል ለማግኘት እንዲሁም በዲስትሪቡዩሽን መስመር ላይ የሚፈጠር መጨናነቅን ለመቀነስ የላቀ ሚና አለው፡፡

በተጨማሪም በዚህ ሰዓት መጠቀም በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ሥራዎችን በአጭር ጊዜ ለመጨረስ፣የፍጆታ ሂሳብንም ለመቀነስ ፋይዳው የጎላ መሆኑን ተገንዝበው፤ በዚህ አግባብ እንዲጠቀሙ እንመክራለን፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ደንበኞች በቤት ውስጥ የሚገለገሉባቸውን የኤሌክትሪክ ቁሳቁሶች ኃይል ቆጣቢና ለአደጋ የማያጋልጡ መሆናቸውን ሊያረጋግጡ ይገባል፡፡

የቅድመ ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኞች በዓሉ ሲደርስ የሚኖረውን አላስፈላጊ እንግልት ለማስቀረት እንዲችሉ ከወዲሁ የሚበቃቸውን ያህል የኤሌክትሪክ ኃይል አስቀድመው እንዲገዙ /ካርድ እንዲሞሉ/ እናሳስባለን፡፡

በበዓሉ ዕለት የኤሌክትሪክ ኃይል በሚቋረጥበት ጊዜ የጥገና ስራ ለማከናወን የተቋሙን መታወቂያ የያዙ የቴክኒክ ባለሞያዎቻችን በተለያዩ አካባቢዎች ለስራ ጉዳይ እንደሚንቀሳቀሱ ህብረተሰቡ ተገንዝቦ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግም እንጠይቃለን፡፡

ይሁንና የተቋሙን የጥገና ሰራተኞች በመምሰል መሠረተ-ልማቱ ላይ ስርቆትና ጉዳት ሊያደርሱ የሚችሉ አካላት ሊኖሩ ስለሚችሉ፤ ህብረተሰቡ ይህንን ተገንዝቦ የኤሌክትሪክ ማሰራጫ መስመሮችን እንደራሱ ንብረት አድረጎ በመጠበቅ እንዲተባበርና እኩይ ተግባራት ሲመለከት ለሚመለከተው የፀጥታ አካላትና ለተቋሙ ማሳወቅ ይገባዋል፡፡

በመጨረሻም ድንገት የኤሌክትሪክ አደጋ ቢያጋጥም፣ ተቋሙን የሚመለከቱ ሌሎች መረጃዎች ለመጠየቅ እንዲሁም ጥቆማዎችና አስተያየቶችን ለማቅረብ በአቅራቢያቸው ወደሚገኝ የአገልግሎት መስጫ ማዕከል በአካል በመሄድ ማሳወቅ ወይም ወደ 905 ነፃ የጥሪ ማዕከል መደወል እንደሚያስፈልግ እንጠቁማለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

ወቅታዊና ትኩስ የተቋማችን መረጃዎች ወዲያውኑ እንዲደርሳችሁ እነዚህን የትስስር ገፆቻችንን ይወዳጁ፡-

ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/EEUOfficial/
ቲዊተር፡ https://twitter.com/EEUEthiopia
ቴሌግራም፡ t.me/eeuethiopia
ዩቱዩብ: https://www.youtube.com/c/EthiopianElectricUtility
ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et
5.0K views08:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-08 11:09:14
4.8K views08:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-06 15:12:09 በበዓሉ የኤሌክትሪክ መቆራረጥ ለመቀነስ ዝግጅት መደረጉ ተገለፀ
**********************
በበዓል ወቅት በሚፈጠር የኃይል መጨናነቅ የኤሌክትሪክ መቆራረጥ እንዳይከሰት በሁሉም የደንበኞች አገልግሎት መስጫ ማዕከላት የቅድመ ዝግጅት ስራዎች መሰራታቸውን የሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት ስራ አስፈፃሚ አቶ አበበ ዕድሉ ተናግረዋል።

ከበዓሉ ዋዜማ ጀምሮ የኃይል መቆራረጥ ከመከሰቱ በፊት የሚቆጣጠር እና ችግር ሲፈጠርም ፈጥኖ ምላሽ የሚሰጥ ግብረ ኃይል ዝግጁ መሆኑን ገልፀው፤ የኃይል መቋረጥ ሲያጋጥም ህብረተሰቡ በአቅራቢያው ለሚገኝ ማዕከል ጥቆማ በመስጠት አገልግሎቱን መልሶ እንደሚያገኝ አስገንዝበዋል፡፡

በተጨማሪም ደንበኞች ከተቋሙ ማግኘት ያለባቸውን አገልግሎት ያለ ምንም እንግልት እንዲያገኙ እየተሰራ መሆኑን አስታውሰው፤ ህብረተሰቡም የስነ ምግባር ጥሰቶች የሚፈጽሙ ግለሰቦችን በማጋለጥ ተባባሪ መሆን እንዳለበት አሳስበዋል፡፡

በተመሳሳይ የደቡብ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት አዲሱን ዓመት ምክንያት በማድረግ ግብረ ኃይል በማቋቋም አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እያደረገ መሆኑን የአገልግሎቱ ስራ አስፈጻሚ አቶ ክንፈ ነጋሽ አስታውቀዋል፡፡

ደንበኞች በዓሉን ያለምንም የኤሌክትሪክ መቆራረጥ እንዲያሳልፉ ለማድረግ እንዲሁም ድንገት መቆራረጥ ቢከሰት ፈጣን ምላሽ ለመስጠት አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁንም ገልፀዋል።

ይህ ግብረ ሃይል እና እስከ ሳተላይት ድረስ የተዋቀረ መሆኑንም አመላክተዋል፡፡

ደንበኞችም ችግሮች ሲገጥሟዋቸው በአቅራቢያቸው ለሚገኙ ማዕከላት በፍጥነት በማሳወቅ ፍጣን ምላሽ ማግኘት እንደሚችሉም ጠቁመዋል፡፡

የደቡብ ምዕራብ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት የዲስትሪቢዩሽን ኦፕሬሽንና ሜንቴናንስ ሃላፊ አቶ እስራኤል ሀብታሙ በበኩላቸው የኃይል መቆራረጥ በስፋት የሚታዩባቸው አካባቢዎችን በመለየት አስፈላጊዉን ቅድመ ዝግጅት በማድረግ የጥገና ስራዎች በመስራት ላይ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በክልሉ የሚገኙ ደንበኞች በተቻለ መልኩ ኃይል ሳይቆራረጥ እንዲያገኙ ለማድረግ ሰፊ የቅድመ ዝግጅት ሥራ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡

በዋዜማውና በዕለቱ ለሚፈጠሩ መቆራረጦች ምላሽ የሚሰጥ ግብረ ሃይል እስከ ማዕከል ድረስ መቋቋሙንም አስታውቀዋል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

ወቅታዊና ትኩስ የተቋማችን መረጃዎች ወዲያውኑ እንዲደርሳችሁ እነዚህን የትስስር ገፆቻችንን ይወዳጁ፡-

ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/EEUOfficial/
ቲዊተር፡ https://twitter.com/EEUEthiopia
ቴሌግራም፡ t.me/eeuethiopia
ዩቱዩብ: https://www.youtube.com/c/EthiopianElectricUtility
ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et
3.0K viewsedited  12:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-06 15:12:09
2.7K views12:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-06 08:46:01 አገልግሎቶቹ ለበዓሉ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እያከናወኑ ነው
*****************
የአማራና የኦሮሚያ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎቶች በመጪው የአዲስ ዓመት በዓል ወቅት ሊከሰት የሚችለውን የኃይል መቆራረጥ ችግር ለመከላከል የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን እያከናወኑ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

አገልግሎቶቹ በዓሉን ምክንያት በማድረግ በዋዜማውና በዕለቱ ድንገት ለሚከሰት የኃይል መቆራረጥ ችግር አፋጣኝ ምላሽ የሚሰጥ ግብረ ሃይል አቋቁመው ወደ ስራ መግባታቸውንም ጠቁመዋል፡፡

የአማራ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት የዲስትሪቡሽን ቴክኒካል ሰፖርት ኃላፊ አቶ ሽመላሽ ግርማው የኃይል መቆራረጥ ችግር ለመከላከል ከተከሰተም አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት ችግር ያለባቸውን የኤሌክትሪክ መስመሮች በመለየት የቅድመ መከላከል ሥራ በመስራት ላይ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

በበዓላት ወቅት የኃይል ፍላጎት እንደሚጨምር የገለፁት ኃላፊው፤ ይህንን ታሳቢ በማድረግ አስቀድሞ ቅድመ ዝግጅቶች መጀመራቸውን አስታውሰዋል፡፡

ደንበኞች በቤት ውስጥ የሚጠቀሙባቸው የኤሌክትሪክ ቁሳቁሶችም ኃይል ቆጣቢና ለአደጋ የማያጋልጡ መሆናቸውን ሊያረጋግጡ ይገባል ብለዋል፡፡

የኦሮሚያ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት የዲስትሪቡሽን ቴክኒካል ሰፖርት ኃላፊ አቶ ግርማ ወልቀባ በበኩላቸው በመጪው በ2015 ዘመን መለወጫ በዓል ወቅት በክልሉ ሊከሰት የሚችለውን የኃይል መቆራረጥ ችግር ለመከላከል የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

በዚህም በክልሉ የሚገኙ በሁሉም ዲስትሪክቶች እና በአገልግሎት መስጫ ማዕከላት የኤሌክትሪክ መስመሮችና ትራንስፎርመሮችን የመፍተሸና የጥገና ስራዎችን የማከናወን ስራ እየተከናወነ ነው ብለዋል፡፡

አቶ ግርማ አክለውም በበዓሉ ዋዜማና በዕለቱ የኃይል መቆራረጥ ችግር እንዳያጋጥም ለማድረግ በሚደረገው ጥረት የሚያስፈልጉ ግብዓቶች ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

በበዓሉ ወቅት የሃይል መጨናነቅ እንዳያጋጥም ደንበኞች የኃይል ጭነት በማይበዛባቸው ሰዓታት መጠቀም እንዳለባቸውና የተቋሙ ሠራተኞች በመምሰል መሠረተ-ልማቱ ላይ ስርቆትና ጉዳት የሚያደርሱ አካላትን ሲመለከት ለሚመለከተው የፀጥታ አካላትና ለተቋሙ ማሳዋቅ እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

ወቅታዊና ትኩስ የተቋማችን መረጃዎች ወዲያውኑ እንዲደርሳችሁ እነዚህን የትስስር ገፆቻችንን ይወዳጁ፡-

ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/EEUOfficial/
ቲዊተር፡ https://twitter.com/EEUEthiopia
ቴሌግራም፡ t.me/eeuethiopia
ዩቱዩብ: https://www.youtube.com/c/EthiopianElectricUtility
ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et
4.8K views05:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-06 08:45:58
3.4K views05:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-05 12:08:25 ዲስትሪክቱ ለበዓሉ የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እያከናወነ ነው
****************
ከመጪውን የአዲስ ዓመት በዓል ጋር ተያይዞ ሊኖር የሚችለውን የሃይል መቆራረጥ ለመቀነስ የሚያስችል የቅድመ መከላከልና ጥገና ስራ እያከናወነ መሆኑን በኦሮሚያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የፊንፊኔ ዙሪያ ዲስትሪክት ዳይሬክተር አቶ ካብታሙ ቀፀላ ገልፀዋል፡፡

ዳይሬክተሩ አክለውም ከበዓሉ ጋር ተያይዞ የሚፈጠረውን ከፍተኛ የኃይል ፍላጎትና የመስመር መጨናነቅ ታሳቢ በማድረግ የመስመር ፍተሻ፣ የረገቡ ሽቦዎችን መወጠር፣ ለኃይል መቆራረጥ መንስኤ የሚሆኑ የዛፍ ቅርንጫፎችን መቁረጥ፣ የትራንስፎርመሮችን ደህንነት ማረጋገጥ እንዲሁም ከፍተኛ ኃይል ጭነት ያለባቸውን መስመሮችን በመለየት የማበዳደር ስራ እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

በፊንፊኔ ዙርያ ዲስትሪክት ለገጣፎ፣ ሰበታ፣ ገላን፣ ቡራዩ፣ ሱሉልታና አካባቢዎቻቸው ከፍተኛ የኃይል መቆራረጥ ችግር የሚያጋጥማቸው አካባቢዎች ናቸው ያሉት ዳይሬክተሩ፤ ይህንንም ለማስቀረትም በበጀት ዓመቱ በአጠቃላይ 306 ኪ.ሜ የመካከለኛ እና ከ 439 ኪ.ሜ በላይ የዝቅተኛ መስመር የጥገና ስራ፤ 231 የአዳዲስና 80 አጋዥ ትራንስፎርመሮች ተከላ ስራ በዲስትሪክቱ መስራቱን ተናግረዋል፡፡

በበዓሉ ዕለትም ሆነ በዋዜማው የኃይል መቆራረጥ ችግር እንዳይከሰት ክትትል የሚያደርግ፣ ከተፈጠረም የአስቸኳይ ጥገና አገልግሎት የሚሰጥ፣ የሠራተኞችን የሥራ ላይ ደህንነት የሚከታተል እና የግብዓት አቅርቦት ስራዎች የሚሰራ ግብር ሃይል በማዋቀር የበዓሉን መድረስ እየተጠባበቁ መሆኑን ጨምረው ገልፀዋል፡፡

በመጨረሻም አቶ ካብታሙ በበዓሉ ምክንያት የሚፈጠረውን ግርግር ተገን በማድረግ በተቋሙ መሠረተ ልማት ላይ ስርቆትና ጉዳት ሊያደርሱ የሚችሉ አካላት ሊኖሩ እንደሚችሉ ጠቁመው፤ ህብረተሰቡ ይህንን ከወዲሁ ተገንዝቦ የኤሌክትሪክ ማሰራጫ መስመሮችን በመጠበቅ እንዲተባበርና እኩይ ተግባራትን ሲመለከት ለሚመለከታቸው የህግ አካላትና ለተቋሙ በአፋጣኝ እንዲያሳውቅ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

ወቅታዊና ትኩስ የተቋማችን መረጃዎች ወዲያውኑ እንዲደርሳችሁ እነዚህን የትስስር ገፆቻችንን ይወዳጁ፡-

ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/EEUOfficial/
ቲዊተር፡ https://twitter.com/EEUEthiopia
ቴሌግራም፡ t.me/eeuethiopia
ዩቱዩብ: https://www.youtube.com/c/EthiopianElectricUtility
ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et
496 views09:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-05 12:07:55
511 views09:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-05 12:07:34
516 views09:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ