Get Mystery Box with random crypto!

Ethiopian Electric Utility

የሰርጥ አድራሻ: @eeuethiopia
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 24.33K
የሰርጥ መግለጫ

EEU Official Telegram Channel
Web: www.eeu.gov.et

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 38

2022-09-26 09:00:29
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
ወቅታዊና ትኩስ የተቋማችን መረጃዎች ወዲያውኑ እንዲደርሳችሁ እነዚህን የትስስር ገፆቻችንን ይወዳጁ፡-
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/EEUOfficial/
ቲዊተር፡ https://twitter.com/EEUEthiopia
ቴሌግራም፡ t.me/eeuethiopia
ዩቱዩብ: https://www.youtube.com/c/EthiopianElectricUtility
ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et
2.1K views06:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-24 14:03:51 ዋና ስራ አስፈፃሚው ከሐረሪ ክልል ም/ርዕሰ መስተዳድር ጋር ተወያዩ
***************
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሽፈራው ተሊላ ከሐረሪ ክልል ም/ርዕሰ መስተደድር ወ/ሮ ሚስራ አብደላ ጋር በኤሌክትሪክ አገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ ውይይት አድረገዋል።

በውይይታቸውም በክልሉ ስላለው የኤሌክትሪክ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚስተዋሉ ጠንካራና ደካማ ጎኖችን አንስተው የተወያዩ ሲሆን፤ በቀጣይ ጥራት ያለው አገልግሎት በሚሰጥበት ሁኔታ ላይም መክረዋል፡፡

በውይይቱ ላይ ሌሎች የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮችም ተሳትፈዋል።

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

ወቅታዊና ትኩስ የተቋማችን መረጃዎች ወዲያውኑ እንዲደርሳችሁ እነዚህን የትስስር ገፆቻችንን ይወዳጁ፡-

ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/EEUOfficial/
ቲዊተር፡ https://twitter.com/EEUEthiopia
ቴሌግራም፡ t.me/eeuethiopia
ዩቱዩብ: https://www.youtube.com/c/EthiopianElectricUtility
ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et
287 viewsedited  11:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-24 14:03:51
278 views11:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-24 13:31:58
በስርቆት ምክንያት የኃይል አቅርቦት ተቋርጧል
***************
በደብረማርቆስ ከተማ ከ400 ኪ.ቮ ሰብስቴሽን ወጪ ሆኖ ወደ ተለያዩ አካባቢዎች ኃይል በሚያደርሰው ዋና መስመር ትናንት ማታ ላይ ባልታወቁ ግለሰቦች ስርቆት ተፈፅሟል፡፡

በዚህም ጮቄ የኢቢሲ ሬድዮ ማሰራጫ፣ ጮቄ የአሚኮ ማሠራጫ፣ ጮቄ የቴሌ፣ የሮብ ገበያ ከተማ የውሃ አገልግሎት እንዲሁም በአቅራቢ በሚገኙ ሳተላይቶች ላይ የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋርጦባቸዋል፡፡

የተዘረፈው የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ገመድ ከ1.2 ኪ.ሜ በላይ ሲሆን፤ የተቋረጠውን አገልግሎቱ ወደነበረበት ለመመለስ በአሁን ወቅት የደብረ ማርቆስ ዲስትሪክት ቴክኒክ ሠራተኞች ከፍተኛ ርብርብ እያደረጉ ይገኛሉ፡፡

የተቋረጠውን መስመር ተጠግኖ አገልግሎቱን እስኪመለስ ድረስም በእነዚህ አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን በትዕግስት እንድትጠባበቁ እንጠይቃለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

ወቅታዊና ትኩስ የተቋማችን መረጃዎች ወዲያውኑ እንዲደርሳችሁ እነዚህን የትስስር ገፆቻችንን ይወዳጁ፡-

ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/EEUOfficial/
ቲዊተር፡ https://twitter.com/EEUEthiopia
ቴሌግራም፡ t.me/eeuethiopia
ዩቱዩብ: https://www.youtube.com/c/EthiopianElectricUtility
ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et
681 viewsedited  10:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-24 10:42:40 የኢኤአ የሳምንቱ አበይት መረጃዎች ሲታወሱ
**************
• የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የከፍተኛ ማኔጅመንት አባላት፣ የመሰረታዊ ሠራተኛ ማህበር ስራ አመራሮች፣ ከዋናው መስሪያ ቤት ጀምሮ እስከ ማዕከላት ድረስ የሚገኙ የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት ለሶስት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ የምክክር መድረክ በአዳማ ከተማ ማካሄዱን፣

• በየደረጃው የሚገኝ የተቋሙ አመራርና ሰራተኛ በአገልግሎት አሰጣጡ ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን በመቅረፍ የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት መዘጋጀት እንዳለበትና አገልግሎት አሰጣጡን ለማሻሻል እንዲቻል በርካታ የአሰራር ስርዓቶችን ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሽፈራው ተሊላ መግለፃቸውን፣

• በተቋሙ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚያጋጥሙ ቁልፍ ችግሮችን ሊፈታ የሚችል የሶስት ዓመት ስትራቴጅክ ዕቅድ ተዘጋጅቶ ለከፍተኛ ማኔጅመንት አባላት እና በየደረጃው ለሚገኙ የስራ ሃላፊዎች መቅረቡን፣

• ተቋሙ የሚሰጠውን አገልግሎት ቀልጣፋ፣ አስተማማኝና ጥራቱን የጠበቀ በማድረግ የህብረተሰቡን ፍላጎት ለማርካት እንዲቻል በቀረቡት የሶስት ዓመት ስትራቴጂክና በ2015 በጀት አመት ዕቅድና በ2014 በጀት ዓመት አፈፃፀም ላይ የተቋሙ አመራሮች የቡድን ውይይት ማካሄዳቸውን፣

• የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከፍተኛ ማኔጅመንት አባላትና በየደረጃው የሚገኙ የስራ ሃላፊዎች ለሶስት ተከታታይ ቀናት ባካሄዱት የውይይት መድረክ ላይ ለብልሹ አስራር ምክንያት የሆኑ ምንጮችን በማስወገድ የደንበኞችን የእርካታ ደረጃ ማሳደግ እንደሚገባ መገለፁ፣

• የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሪት ፍሬህይወት ታምሩ ለአንድ ሃገር ሁለንተናዊ እንቅስቃሴና ኢኮኖሚዊ ዕድገት የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትን ማሻሻልና የደንበኞችን የእርካታ ደረጃ ማሳደግ ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባር መሆኑን መግለፃቸው፣

• በተቋሙ ተከፍተው አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙት የህፃናት ማቆያ ማዕከላት የሴት ሠራተኞችን ተደራራቢ የሥራ ጫና እየቀነሱ መሆኑን፣

• በደብረ ማርቆስ ከተማ የመንገድ መብራት ገመድ ስርቆት ሲፈፅም የነበረው ተጠርጣሪ ግለሰብ በህብረተሰቡ ጥቆማ በቁጥጥር ስር መዋሉንና ምርመራ እየተካሄደበት መሆኑን የሳምንቱ አበይት መረጃዎቻችን ነበሩ፡፡

ሠናይ ቅዳሜና ዕሁድ እንዲሆንላችሁ ተመኘን!

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

ወቅታዊና ትኩስ የተቋማችን መረጃዎች ወዲያውኑ እንዲደርሳችሁ እነዚህን የትስስር ገፆቻችንን ይወዳጁ፡-

ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/EEUOfficial/
ቲዊተር፡ https://twitter.com/EEUEthiopia
ቴሌግራም፡ t.me/eeuethiopia
ዩቱዩብ: https://www.youtube.com/c/EthiopianElectricUtility
ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et
1.7K views07:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-24 10:42:36
1.6K views07:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-23 14:35:55 ለደመራ በዓል ችቦ ሲለኮስ የኤሌክትሪክ አደጋ እንዳይከሰት ተገቢውን ጥንቃቄ ያድርጉ! ከወዲሁ #መልካም_በዓል!

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

4.0K viewsedited  11:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-23 13:56:00
በብልሽት ምክንያት የኤሌክትሪክ ኃይል በአሶሳ ከተማ እና አካባቢው ተቋርጧል
******************
በባምባሲ ወረዳ መንደር 49 አካባቢ ሁለት ክፍተኛ የኤሌክትሪክ ታዎሮች በመውደቃቸው ምክንያት በአሶሳ ከተማ እና አካባቢው ከለሊቱ 11 ሰዓት ጀምሮ ኃይል ተቋርጦል፡፡

አገልግሎቱን ለማስጀመር የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል የምዕራብ ሪጅን ጋር ጥረት እየተደረገ ሲሆን ፤ ጥገናው ተጠናቆ አገልግሎት ዳግም እስኪጀምር ድረስ ክቡራን ደንበኞቻችን በትግዕስት እንድትጠባበቁን በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

ወቅታዊና ትኩስ የተቋማችን መረጃዎች ወዲያውኑ እንዲደርሳችሁ እነዚህን የትስስር ገፆቻችንን ይወዳጁ፡-

ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/EEUOfficial/
ቲዊተር፡ https://twitter.com/EEUEthiopia
ቴሌግራም፡ t.me/eeuethiopia
ዩቱዩብ: https://www.youtube.com/c/EthiopianElectricUtility
ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et
4.0K views10:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-23 11:03:24
ተደጋጋሚ የመንገድ የመብራት ገመድ ስርቆት ሲፈፅም የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገለፀ
*******************
በደብረ ማርቆስ ከተማ የመንገድ መብራት ገመድ ስርቆት ሲፈፅም የነበረው ተጠርጣሪ ግለሰብ በህብረተሰቡ ጥቆማ በቁጥጥር ስር መዋሉንና አስፈላጊው ምርመራ እየተካሄደበት መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ የ2ኛ ፖሊስ ጣቢያ ኃላፊ ኮማንደር ይልማ ስራብዙ ገልፀዋል፡፡

ግለሠቡ ወንጀሉን ለመፈፀም ከዚህ በፊትም ከ500 ሜትር በላይ የመብራት ገመድ ሰርቆ በ14 ሺህ ብር መሸጡን፣ በገዢው መጋዘን ፍተሻ ሲደረግም የተጠቀሰው ገመድ መያዙን ኃላፊው አስታውሰዋል፡፡

በከተማ አስተዳደሩ የመንገድ መብራት ላይ ተደጋጋሚ ስርቆት በመፈፀሙ ምክንያት መብራት መቋረጡን እና በአካባቢው ማህበረሰብ ላይ ተፅኖ መፍጠሩንም ተናግረዋል፡፡

ህብረተሰቡ በመሠረተ ልማት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች የሚያስከትሉትን ተፅዕኖ በመገንዘብ አካባቢውን ከፀጥታ ሀይሉ ጋር በመቀናጀት ሊጠብቅ እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡

ወንጀሎችን ለመከላከል ቤት በማከራየት የሚተዳደሩ ግለሠቦችም የተከራዮችን ማንነት እና አድራሻ ማወቅ እንዲሁም መታወቂያቸውን ኮፒ በማድረግ በቅርብ ለሚገኙ የቀበሌ የጸጥታ ሀይሎች በማስመዝገብ የበኩላቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

ወቅታዊና ትኩስ የተቋማችን መረጃዎች ወዲያውኑ እንዲደርሳችሁ እነዚህን የትስስር ገፆቻችንን ይወዳጁ፡-

ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/EEUOfficial/
ቲዊተር፡ https://twitter.com/EEUEthiopia
ቴሌግራም፡ t.me/eeuethiopia
ዩቱዩብ: https://www.youtube.com/c/EthiopianElectricUtility
ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et
4.3K views08:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-23 09:16:04 ከደመራ በዓል አከባባር ጋር ተያይዞ የኤሌክትሪክ አደጋ እንዳይከሰት ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል
************************
በቅድሚያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የመስቀል በዓልን ለሚያከብሩ የእምነቱ ተከታዮች ከወዲሁ እንኳን ለ2015 ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልፃል፡፡

ከመስቀል ደመራ በአል አከባባር ጋር ተያይዞ የእምነቱ ተከታዮች በተለያዩ ቦታዎች ችቦ የማብራት ስነ ስርአት ያካሂዳሉ፡፡ በዚህ ወቅት አደጋ እንዳይከሰት ከፍተኛ ጥንቃቄ ሊያደርጉ ይገባል፡፡


በዚህ ወቅትም ደመራ ሲለኮስ ከኤሌክትሪክ ምሰሶዎች፣ ትራንስፎርመሮችና መስመሮች በጣም በራቀ መልኩ ማከናወን እንዲሁም የእሳት አደጋ እንዳይከሰት ቅድመ ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡

ጥንቃቄ ባለተሞላበት ሁኔታ ከኤሌክትሪክ ንክኪ ጋር በሚፈጠሩ አደጋዎች በሰውና ንብረት ላይ ጉዳት ሊያስከትሉ ይችላሉ፡፡

በመሆኑም ለአከባበሩ ድምቀት የአሌክትሪክ ምሰሶዎችን በመጠቀም የሚደረጉ የማስዋብ ሥራዎች ለኤሌክትሪክ አደጋ ሊያጋልጥ ስለሚችል ከፍተኛ ጥንቃቄ እንደሚገባው ተቋሙ ያሳስባል፡፡

ከዚህ ጋር ተያይዞ በኤሌክትሪክ ማሰራጫ ምሰሶዎች ላይ በተሽከርካሪዎች አደጋ የማደርስ ተግባር በበዓላት የሚሰተዋል በመሆኑ አሽከርካሪዎች ጥብቅ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ተቋሙ በማከል ያሳውቃል፡፡

ህብረተሰቡ መሰል አደጋዎች እንዳይከሰቱ የበኩልን ትብብር እንዲያደርግ እየጠየቅን፤ ሆኖም ድንገት ከኤሌክትሪክ ጋር በተገናኘ አደጋ ካጋጠመ ወይም ሌላ መረጃ ሲፈለግ ወዲውኑ በአቅራቢያ በሚገኝ አገልግሎት መስጫ ማእከል ቀጥታ ስልክ በመደወል ወይም በአካል በመሄድ ማሳወቅ ያስፈልጋል፡፡

በአማራጭነት በአዲስ አበባና ዙሪያው የሚገኙ ደንበኞቻችን በነፃ የጥሪ ማዕከላችን 905 ነፃ የጥሪ ማዕከል በመደወል ማሳወቅ እንደሚቻል እንገልፃለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

ወቅታዊና ትኩስ የተቋማችን መረጃዎች ወዲያውኑ እንዲደርሳችሁ እነዚህን የትስስር ገፆቻችንን ይወዳጁ፡-

ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/EEUOfficial/
ቲዊተር፡ https://twitter.com/EEUEthiopia
ቴሌግራም፡ t.me/eeuethiopia
ዩቱዩብ: https://www.youtube.com/c/EthiopianElectricUtility
ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et
4.4K views06:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ