Get Mystery Box with random crypto!

ECWC/ኢኮሥኮ/

የቴሌግራም ቻናል አርማ ecwccom — ECWC/ኢኮሥኮ/ E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ecwccom — ECWC/ኢኮሥኮ/
የሰርጥ አድራሻ: @ecwccom
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 12.23K
የሰርጥ መግለጫ

Official ECWC Telegram Channal
.የኮርፖሬሽኑ ዜናዎች
.የጨረታና የሥራ ማስታወቂያዎች
. በየወሩ የሚታተመው የዜና መጽሄት
. ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮች
.በየ 6ወሩ የሚታተመው የኮርፖሬሽኑ ዕይታ መጽሄት እና የኮርፖሬሽኑ ፕሮፋይል በዚህ ገጽ ላይ በየጊዜው ይቀርባል፡፡

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2023-04-26 18:55:09
2.2K views15:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 18:54:45 መልካም ዜና
የማህበራዊ ሃላፊነት ስርዓት (ISO 26000፡2010 Guideline on Corporate Social Responsibility) መስፈርትን ስለማሟላት፤
ኮርፖሬሽኑ ባሳለፍነው በጀት ዓመት ካስቀመጣቸው የሪፎርም አቅጣጫዎች መካከል፤ የኮርፖሬሽኑን አሰራር እና ተቀባይነት የሚያሻሽሉ አዳዲስ የISO ጋይድ ላይኖችን መተግበር ይገኝበታል፡፡

በዚህም መሰረት ተግባራዊ ለመደረግ ከታቀዱ ISO ጋይድላይኖች መካከል የማህበራዊ ኃላፊነት ስርዓት (Guideline on Corporate Social Responsibility) ትግበራ አንዱ ሲሆን፤ በዚህም ትግበራውን አስመልክቶ ኦዲት ተካሂዶ በኦዲት የተለዩ የማስተካከያ ሥራዎች ሲሰሩ ቆይተዋል፡፡ በዚህም ትግበራውን አስመልክቶ ከጋይድ ላይኑ አኳያ አብዛኞቹ መስፈርቶች መሟላታቸው ተረጋግጦ እንዲስተካከሉ የተለዩ አሰራሮች መስተካከላቸው በውስጥ ኦዲተሮች በመረጋገጡ ስርዓቱ በተቋም ደረጃ ይፋ ተደርጓል፡፡

በኦዲተሮች እንዲሻሻሉ አስተያየት ከተሰጠባቸው እና መስተካከላቸው ከተረጋገጡ ውስንነቶች መካከል፤ ጋይድ ላይኑን አስመልክቶ የግንዛቤ ችግር፤ ጋይድ ላይኑን በተመለከተ በተቋም ደረጃ የተቀረፁ ግቦች አለመኖር፤ ለኤች አይቪ ተቆራጭ የሚደረግ ገንዘብ መቆራረጥ እና የህፃናት ማቆያ ሥራ አለመጀመር የሚገኙበት ሲሆን እነዚህ ክፍተቶች አሁን ላይ መስተካከላቸው ተረጋግጧል፡፡

በዚህም በቀጣይ ዓመት እስከሚካሄድ የማረጋገጫ ኦዲት ድረስ ኮርፖሬሽኑ የማህበራዊ ሃላፊነት ስርዓት (ISO 26000፡2010 Guideline on Corporate Social Responsibility) መስፈርትን ያሟላ መሆኑን እያበሰርን፤ በዚህም በሂደቱ ተሳታፊ የነበራችሁ መላው አመራሮች እና ሰራተኞች እንኳን ደስ አላችሁ እንላለን፡፡
2.1K views15:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-24 16:13:42
በዛሬ የሚያዝያ  16 ቀን 2015 ኢትዮ ኮን የቀጥታ ስርጭት ላይ

በእንግዳ ሰዓታችን
ኢ/ር ገድሉ ሙሉጌታ ይባላሉ፡፡  የዛሬ እንግዳችን በእንግድነት የጋበዝኳቸውም በዋናነት አንድ የፈጠራ ስራ ይዘው ብቅ ብለዋል፡፡ ፈጠራቸውም ተገጣጣሚ የሆነ ብሎኬት ነው፡፡ ከሌሎች ብሎኬቶች ይህ ምን ይለየዋል? ይህ ፈጠራ ምን ምን ነገሮችን ያስቀራል? የአገልግሎት ዘመኑንና ሌሎችንም ጥያቄዎችን እያነሳን ቆይታ የምናደርግ ነው የሚሆነው፡፡ እንድትከታተሉትም ሁላችሁንም በያላችሁበት በአክብሮት እጋብዛለሁ፡፡

እናንተም ተሳፎችሁ በዚህ በቴሌግራም ቻናላችን ላይ ያላችሁን ሀሳብ አስተያየት እንደተለመደው አድርሱን፡፡ እንቀበላለን፡፡

ምሽት 2: 00 ሰዓት በአሀዱ ሬድዮ 94.3 የቀጥታ ስርጭት ፕሮግራም ላይ እንገናኝ! 

መልካም ምሽት !

ዘወትር ሰኞ ምሽት በግንባታው ዘርፍ ላይ ትኩረቱን የሚያደርገው ኢትዮ ኮን ሳምንታዊ ፕሮግራማችን ምሽት 2፡00 - 3፡00 በአሀዱ ሬድዮ 94.3 በቀጥታ ስርጭት ይጠብቁን!
2.2K views13:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-24 16:10:14
774 views13:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-22 11:48:24
1.7K views08:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-19 15:30:36
1.8K views12:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-19 09:06:45
የልማት ተነሺ አርሶ አደሮች ማዕከል ግንባታ በቅርቡ ይጠናቀቃል
*****************
(ኢ ፕ ድ)
በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ የሚገኘው የልማት ተነሺ አርሶ አደሮች ማቋቋሚያ የእንስሳት እርባታና ተዋጽዖ ማዕከል ግንባታ በቅርቡ እንደሚጠናቀቅ የመዲናዋ ዲዛይንና ግንባታ ሥራዎች ቢሮ አስታወቀ።
የአዲስ አበባ ዲዛይንና ግንባታ ሥራዎች ቢሮ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ብዙአየሁ ጉታ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደተናገሩት፤ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ኮዬ ፈቼ የጋራ መኖሪያ አካባቢ በ14 ሄክታር መሬት ላይ የልማት ተነሺ አርሶ አደሮች ማዕከል እየተገነባ ነው፡፡ ይህ የልማት ተነሺ አርሶ አደሮች ማቋቋሚያ የእንስሳት እርባታና ተዋጽዖ ማዕከል ግንባታ በቅርቡ ይጠናቀቃል፡፡
ማዕከሉ ለሁለት ሺህ የልማት ተነሺ አርሶ አደሮች የስራ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን የገለጹት አቶ ብዙአየሁ፤ ፕሮጀክቱ ከ800 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት ተይዞለት የግንባታው አፈፃጸም 95 በመቶ መድረሱን
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=96946
2.5K views06:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-15 09:52:32
748 views06:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-07 11:07:41 የጨረታ ጥሪ ማስታወቂያ
የፈረንጅ ሱፍ እና ሰሊጥ ለመሸጥ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር ECWCT/NCB/SG-113/2015
በኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን በቃሊቲ መጋዘን የሚገኘውን የፈረንጅ ሱፍ እና ሰሊጥ ባሉበት ቦታና ሁኔታ በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡

1. ተጫራቾች የግብር ከፋይ ምዝገባ ሰርተፍኬት፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉበት መረጃ እና የተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይ መሆናቸውን ማረጋገጫ ሰርቲፊኬት በማቅረብ የጨረታውን ሰነድ የማይመለስ ብር 300/ሶስት መቶ ብር/ በመክፈል ዘወትር በሥራ ስዓት ከዋናው መ/ቤት የሃገር ውስጥ ጥቅል ግዥ ቡድን በአካል በመቅረብ መግዛት ይችላሉ፡፡

2. የጨረታው አሸናፊ የሚወሰነው በጨረታ ሰነድ ውስጥ የተመለከቱትን መስፈርቶች አሟልቶ ከፍተኛ ዋጋ የሚያቀርበው ሲሆን የጨረታ ሰነዱ የተዘጋጀው በአማርኛ ቋንቋ ነው፡፡


3. ተጫራቾች ጨረታውን ለዚህ ተግባር በተዘጋጀው ሣጥን ገቢ የሚያደርጉበት የመጨረሻ ቀን ሚያዝያ 03 ቀን 2015 ዓ.ም እስከ ጠዋት 4፡3ዐ ሰዓት ድረስ ብቻ ነው፡፡

4. ተጫራቾች ከሚጫረቱበት ጠቅላላ ዋጋ ብር አስር በመቶ /10%/ የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ ቼክ /CPO/ ወይም በባንክ ዋስትና ከመጫረቻ ሰነዳቸው ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ በኢንሹራንስ ቦንድ /በሌላ መልክ የሚቀርብ ማንኛውም ማስከበሪያ ተቀባይነት የለውም፡፡

5. ጨረታው ተጫራቾች ወይንም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ሚያዝያ 03 ቀን 2015 ዓ.ም እስከ ጠዋት 05፡00 ሰዓት ጉርድ ሾላ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን ዋናው መ/ቤት ቅጥር ግቢ የስብሰባ አዳራሽ ይከፈታል፡፡


6. መ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡


7. ለበለጠ መረጃ በሚከተለው አድራሻ መጠየቅ ይቻላል፡፡

የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን
አድራሻ ጉርድ ሾላ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ህንፃ አለፍ ብሎ
አንድነት ት/ቤት ፊት ለፊት
የኮርፖሬት ግዥና ንብረት አስተዳደር ዋና መምሪያ
የፖ.ሣ.ቁጥር 21952/1000
የስልክ ቁጥር 0118-13-45-27 /011-8-72-29-58
1.1K views08:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-04 14:42:29
Dear All. Please register for your free pass.Thank you.
2.3K views11:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ