Get Mystery Box with random crypto!

Debre Markos University /ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ

የቴሌግራም ቻናል አርማ debre_markos_university — Debre Markos University /ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ D
የቴሌግራም ቻናል አርማ debre_markos_university — Debre Markos University /ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ
የሰርጥ አድራሻ: @debre_markos_university
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 24.90K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የቴሌግራም ገጽ ነው። የዩኒቨርሲቲያችን ወቅታዊ መረጃዎች፣ ልዩ ልዩ ሁነቶች እና የስራ እና የትምህርት ማስታወቂያዎች ይተላለፉበታል። አሁንኑ ቤተሰብ ለመሆን ይቀላቀሉ!!
This is Our Official Telegram Channel. We Provide up-to-date Information about our University.
Join Us Now!🙏

Ratings & Reviews

4.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 12

2023-02-06 12:36:54
119 views09:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-06 12:36:52
93 views09:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-06 12:36:50
87 views09:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-06 12:35:00 በቅድሚያ በ2014 ዓ.ም ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና ወስዳችሁ ለዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች እንኳን ደስ አላችሁ እንላለን!!

ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ መናገሻ ከሆነችው አዲስ አበባ ከተማ 300 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በምትገኘውና የጎጃም ማዕከል በሆነችው ደብረ ማርቆስ ከተማ ውስጥ የሚገኝ ስመ ጥር ዩኒቨርሲቲ ነው።

ዩኒቨርሲቲያችን በአሁኑ ስዓት የካበተ የማስተማር ልምድ እና እውቀት ባላቸው የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር መምህራን በመታገዝ በ63 ትምህርት ዘርፎች የመጀመሪያ ድግሪ ፣ በ83 የትምህርት ዘርፎች የ2ኛ ዲግሪ እና 10 በሚሆኑ የትምህርት ዘርፎ ደግሞ በሶስተኛ ድግሪ ተማሪዎችን ተቀብሎ በማሰልጠን ላይ ይገኛል።

ደብረ ማርቆስ ኒቨርሲቲ ከተመሰረተበት 1999 ዓ.ም ጀምሮ እስከአሁን ድረስ በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ከ54 ሺህ በላይ ብቃት ያላቸው ባለሙያዎችን አፍርቶ ለሀገራችን ማህበራዊ ፣ምጣኔ ሀብታዊና ፖለቲካዊ ግልጋሎቶች የበኩሉን አስተዋፅኦ አበርክቷል።

ዩኒቨርሲቲያችንን ከሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች የሚለየው በየአመቱ 3.75 እና በላይ ያስመዘገቡ ተማሪዎችን እውቅና ሽልማት የሚሰጥበት " የተማሪዎች አምባሳዳር " መርሐ ግብር ማዘጋጀቱ ነው። ይህ መርሐ ግብር ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች የሚበረታቱበት እና ሽልማት የሚሰጡበት ዝግጅት ሲሆን ሌሎቹ ተማሪዎችም በጓደኞቻቸው ውጤት እንዲነሳሱና የውድድር ስሜታቸው እንዲዳብር ዕድል የሚፈጥር መርሐ ግብር ነው፡፡ ዩኒቨርሲቲያችን ለሶስት ተከታታይ አመታት ይህንን ዝግጅት በደማቅ ሁኔታ ያከበረ ሲሆን ዘንድሮም ለአራተኛ ጊዜ ለማክበር ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ላይ ይገኛል።

ዩኒቨርቲው የተመሰረተባት የደብረ ማርቆስ ከተማና የአካባቢው አየር ንበረትም ከቆለቀማውም ሆነ ከደጋማው የሀገራችን አካባቢዎች ለሚመጡ ሁሉ ፍፁም ተስማሚ የሆነ ወይና ደጋማ የሚባል የአየር ንብረት ባለቤት ነች፡፡ ማህበረሰቡም ከተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች የሚመጡ ተማሪዎችን በመልካም አቀባበል ተቀብሎ የማስተናገድና እንደልጆቹ የመንከባከብ ባህል ያለው ማህበረሰብ ነው፡፡
ከሁሉም በላይ ደግሞ ዩኒቨርሲቲያችን ለተማሪዎቹ ምቾት አብዝቶ የሚጨነቅና ፍፁም ሰላምና መረጋጋት የሰፈነበት ዩኒቨርሲ በመሆኑ ቀዳሚ ምርጫችሁ ብታደርጉት በብዙ እንደምትጠቀሙ እንተማመናለን!!

“የዕውቀት አውድማ ከጮቄ ማማ”
ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ
የአስተዋዮችና የጎበዞች ምርጫ!

ከታች የተቀመጡትን ማስፈንጠሪያዎች በመጫንና በመቀላቀል ተጨማሪ መረጃዎችን ማግኘት ይችላሉ

ዌብሳይት www.dmu.edu.et
ቴሌግራም https://t.me/Debre_Markos_University
ፌስቡክ https://www.facebook.com/dmu.edu
ዩቱዩብ https://www.youtube.com/channel/UCqQDHEyYDen3aybySpYsF_Q
ቲዊተር https://twitter.com/dmu_ethiopia
እንስታግራም https://www.instagram.com/dmu_ethiopia/
ሊንክድኢን https://www.linkedin.com/in/dmu-ethiopia/
160 viewsedited  09:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-03 15:53:10 " የቅኝ ግዛት ትርክቶች እና የኢትጵያ ብሔረ መንግስት ግንባታ ቅኝ ባልተገዛችው ኢትዮጵያ ፥ ተረኮች እና እውነታዎች" በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ትምህረተ -ጉባኤ ተካሄደ።

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካል ሣይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ትምህርት ክፍል " Colonial Narrative and Nation Buliding in a Non-Colonized Ethiopia : Rhetoric Versus Reality " በሚል ርዕስ የደብረ ማርቆስ ዪኒቨርስቲ ምሁራን የተሳተፉበት 25/05/2015 ዓ.ም በንግስተ_ሳባ አዳራሽ ትምህርተ-ጉባኤ አካሂዷል።

በትምህርተ - ጉባዔው መምህር አሳቡ ሰውነት የፖለቲካል ሳይንስ እና አለም አቀፍ ግንኙነት ትምህርት ክፍል ተጠሪ የጉባኤውን የውይይት ፅሁፍ አቅርበዋል።

በፅሑፋቸውም ያካተቷቸው ጭብጦች፦ የሀገረ መንግስት ግንባታ ጽንሰ ሃሳብ፣ የብሔረ መንግሥት ግንባታ ፅንሰ ሃሳብ፣ ቀኝ ግዛት በብሔረ መንግስት ግንባታ ላይ ያሳደረው ተጽኖ እና እውነታዎች ፤ ሀገረ መንግስትና ሉዐላዊነት እንዲሁም ኢትዮጵያ ቀኝ ግዛት አለመገዛቷ ሀገረ መንግሥት ግንባታ ላይ ያመጣው ተጽዕኖ የሚሉ ናቸው።

በሌላ በኩል የቀኝ ግዛት ትርክቶች በሀገረ እና በብሔረ መንግስት ግንባታ ላይ በየዘመኑ በነበሩ ፖለቲካዊ አስተሳሰቦች ላይ የራሱ የሆነ ተጽኖ ማድረጉን ገልፀዋል።

ከጉባዔው ተሳታፊ ምሁራንም ልዩ ልዩ አስያያቶችና ጥያቄዎች የተሰጡ ሲሆን ይህንን ጉባኤ ያዘጋጀውን የፓለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ት/ክፍልም ተመስግኗል።
1.7K views12:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-03 15:53:07
1.7K views12:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-02 18:26:04 የሂሳብ መዝገብ አያያዝና የኦዲት ትምህርትን በተግባር ማስተማሪያ ማዕከል ለማቋቋም የሚያስችል አውደ ጥናት
ተካሄደ

=================

ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ፣ ጥር 25/2015 ዓ.ም (ህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት)

ተማሪዎች በፅንሰ ሀሳብ የተማሩትን ትምህርት በተግባር ለማየት ወደ ሌላ ቦታ ሳይሄዱ በዩንቨርስቲያቸው ውስጥ ተግባሩን እንዲማሩ ለማድረግ በአካውንቲንግና ፋይናንስ ትምህርት ክፍል አስተባባሪነት መንግስታዊና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች የመጡ የሂሳብ አዋቂዎች፣የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ መምህራንና ተማሪዎች በተገኙበት የተግባር ማስተማሪያ ማዕከሉን ለማቋቋም የሚያስችል ዐውደ ጥናት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡

የደብረ ማርቆስ ዩንቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ይሄይስ አረጉ (ዶ.ር) በመክፈቻ ንግግራቸው የሳይንስ ትምህርት ዋና ተልዕኮው እውነትን በመፈለግ ችግርን መፍታት በመሆኑ የሚታይ፣የሚዳሰስ፣የሚኖር፣የሚሰራና የሚተገበር ስራ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

በመሆኑም ተማሪዎችን ብቁ ለማድረግ፣ ንግድን ለማዘመንና የማህበረሰቡን ችግር ለመፍታት እንደነዚህ አይነት የተግባር ማዕከላት መቋቋማቸው አስፈላጊና የሚያስደስት ተግባር መሆኑን ገልፀዋል፡፡

የአውደ ጥናቱ አቅራቢ በአካውንቲንግና ፋይናንስ ትምህርት ክፍል መምህር ደረጀ ብርሃኔ እንደገለፁት ይህ ማዕከል መቋቋሙ ተማሪዎች የፅንሰ ሀሳብ ዕውቀታቸውን ከተግባራዊ ዕውቀት ጋር አጣምረው ወደ ስራ ዓለም ሲገቡ ለተሰማሩበት የስራ ዘርፍ ብቁ እንዲሆኑና ቀጣሪ ድርጅቶች፣ኢንቨስተሮች፣አበዳሪዎች፣መንግስት እና መሰል ተቋማት ከኪሳራና ከተሳሳተ ውሳኔ እንዲድኑ ያስችላቸዋል ብለዋል፡፡

ዓላማውም ተማሪዎች ወሳኝ የሆኑ ሰነዶችን እንዲያውቁና እንዲለዩ፣ሰነዶችን መሰረት ያደረገ የሂሳብ መዝገብ እንዲይዙ፣በያዙት ሂሳብ መሰረት የፋይናንስ መግለጫዎችን እንዲያዘጋጁና ኦዲቶችን በትክክል እንዲሰሩ በማስቻል በቀጣሪ ድርጅቶች ተፈላጊና ተመራጭ እንዲሆኑ ማድረግ ነው ሲሉ ገልፀዋል፡፡
3.4K views15:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-02 18:25:57
3.2K views15:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-02 08:32:20
#NEW
4.3K views05:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-31 09:56:57
#NEW
3.4K views06:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ