Get Mystery Box with random crypto!

Debre Markos University /ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ

የቴሌግራም ቻናል አርማ debre_markos_university — Debre Markos University /ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ D
የቴሌግራም ቻናል አርማ debre_markos_university — Debre Markos University /ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ
የሰርጥ አድራሻ: @debre_markos_university
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 24.90K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የቴሌግራም ገጽ ነው። የዩኒቨርሲቲያችን ወቅታዊ መረጃዎች፣ ልዩ ልዩ ሁነቶች እና የስራ እና የትምህርት ማስታወቂያዎች ይተላለፉበታል። አሁንኑ ቤተሰብ ለመሆን ይቀላቀሉ!!
This is Our Official Telegram Channel. We Provide up-to-date Information about our University.
Join Us Now!🙏

Ratings & Reviews

4.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 13

2023-01-25 16:39:55
#Miss_it_not!
8.4K viewsedited  13:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-25 08:27:51
9.2K views05:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-24 16:12:22
#NEW
8.1K views13:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-23 17:14:07 በደምበጫ ወረዳ ገሊላ ቀበሌ ከእንሰት የተዘጋጀ የምግብ ቀመሳ መርሐ ግብር ተካሄደ፡፡

ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ፥ ጥር 14/2015 ዓ.ም ( ህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት) የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት፣ አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት እና ሌሎችም የዩኒቨርሲቲው ኃላፊዎች፣ የልማት ባንክ ዲቪዥን ሀላፊ፣ መምህራንና ሰራተኞች እንዲሁም የገሊላ ቀበሌ ኗሪ ህዝብና የሀገር ሽማግሌዎች በተገኙበት ከእንሰት የተዘጋጀ ምግብ ቀመሳ ፕሮግራም መርሐ ግብር ተካሄዷል፡፡

በደምበጫ ወረዳ ገሊላ ቀበሌ የእንሰት ፕሮጀክት አስተባባሪ ባወቀ ጥሩነህ እንዳሉት ፕሮጀክቱ በ8 ወረዳዎችና በ32 ቀበሌዎች የሚተገበር እንደሆነ ገልፀው የሀገራችን ህዝብ አንድ አራተኛው ወይም በአሁኑ ሰዓት 32 ሚሊየን የሚሆነው ህዝብ ለምግብነት እየተጠቀመበት እንደሆነም ጠቁመዋል፡፡

ከአንድ ሄክታር እስከ 610 ቶን ድረስ ምርት እንደሚገኝም አያይዘው ገልፀዋል፡፡

ከእንሰት የሚዘጋጁ ምግቦች በጣም ብዙ ጥቅሞችን ማግኘት እንደምንችል የገለፁት የፕሮጀክቱ አስተባባሪ በተለይ የህጻናት መቀንጨር ችግርን እንደሚቀንስም በምርምር እንደተገኘም ተናግረዋል። አርሶ አደሩ እንሰትን እያለማ ምግብ በማዘጋጀት መመገብና ለገበያ ማቅረብ እንደሚኖርበት አሳስበዋል።

እንሰት አካባቢን ለማልማት፣ ለሽያጭ፣ ለቃጫ ምርት፣ ለቡላ፣ ለአረቄ፣ ገንፎ፣ ዳቦ ቆሎ፣ የጾምናፍስክ ፍርፍር ማዘጋጀት እንደሚቻልም አቶ ባወቀ ጥሩነህ አክለው ገልፀዋል፡፡

በመርሐ ግብሩ ላይ አግኝተን ያነጋገርናቸው የሀገር ሽማግሌዎችም የጥምቀት በዓል ዕለት ከእንሰት የተዘጋጀ ምግብ ህዝቡ እንደቀመሰ እና ለማመን ተቸግሮ እንደነበር ጠቁመው እንሰት ለህብረተሰቡ ወጭ ቆጣቢ በመሆኑ ጠንክረን በሰፊው በመስራት የማህበረሰባችንን ሕይወት መለወጥ አለብን ሲሉ መክረዋል፡፡

ይህ መርሐ ግብር ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ ጋር በመተባበር እንሰትን ለምግብነት የማላመድ ፕሮጀክት አካል ነው።
7.7K viewsedited  14:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-23 17:13:57
6.1K views14:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-23 17:13:57
5.7K views14:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-23 17:13:52
5.7K views14:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-18 19:04:50 የደብረማርቆስ ዩኒቨርስቲ ቡሬ ካምፓስ መምህራን እና ሰራተኞች በስነ-ምግባር እና በፀረ ሙስና ዙሪያ ወይይት አደረጉ

=============

ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ቡሬ ካምፓስ፦ ጥር 9/2015 ዓ.ም በቡሬ ካምፓስ ወስጥ የሚታዩ የሙስናና የስነምግባር ችግሮችና አዝማሚያዎች ላይ ትኩረት ያደረገ ውይይት ተካሄደ።

የውይይቱን አስፈላጊነት በተመለከተ የቡሬ ካምፓስ ችፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተሩ ዶ/ር ብርሀኑ አለሙ እንደገለፁት ከሙስናና ከብልሹ አሰራሮች ፅዱ በማድረግና ምቹ የስራ አካባቢን በመፍጠር ተመራጭ የስራ ቦታን ለመፍጠር ታላሚ ያደረገ ወይይት መሆኑን ጠቅሰዋል።

የደብረማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ዳይሬክተር ኮማንደር ይበልጣል ደምሰው በበኩላቸው ይህ ውይይት ሲዘጋጅ ዋና ዓላማው በዋናው እና በቡሬ ካምፓሶች ያሉትን የሙስና ችግሮች በመፍታት ምቹ የስራ አካባቢን ለመፍጠር ነው ሲሉ ገልፀዋል።

በ2015 በ 6ወር ውስጥ በስነምግባር እና ፀረ ሙስና የተከናወኑ ስራዎች እና ያጋጠሙ ችግሮች በተመለከተም ሪፖርት ቀርቧል።

በሪፖርቱም በካምፓሱ ውስጥ ያላግባብ የተያዙ ሱቆች እንዲለቀቁ መደረጉ ፣ ያላግባብ የግቢውን ባህር ዛፍ ቆርጠው ለራሳቸው ጥቀም ሊያውሉ ሲሉ ተደርሶባቸው ለምግብ ቤት አገልግሎት እንዲውል መደረጉ ፤ ቤተመጻሕፍት ውስጥ ተሰርቀው የነበሩት የኮምፒውተር እቃዎች አንዲመለሱ መደረጉ፤ በግቢው ውስጥ ያላግባብ ቤት ተሰጧቸው የሚኖሩ መምህራን በህግ አግባብ ቤቱን የማስለቀቅ ስራ መሰራቱ የሚሉ ዋና ዋና ነጥቦች የተካተቱ ሲሆን የተገኙ መልካም ተሞክሮዎችን በሚመለከት ደግሞ ከፍትህ ፣ ከጥበቃ፣ ፖሊስ እና ከስነምግባር እና ከፀረ ሙስና ተቋማት ጋር በቅንጅት መሰራቱ ፤ ያጋጠሙ ችግሮችን በሚመለከት ደግሞ የንብረት ስርቆት ወንጀል መበራከት ፤ የተለያዩ ግለሰቦች ጥቆማ ወይም ቅሬታ በቂ ማስረጃአ አለመሟላት፤ የስነ ምግባር ተገዥነት ዝቅተኛ መሆን ፤ በአቋራጭ የመበልፀግ ፍላጎት መሆን የሚሉት በዋናነት ተጠቅሰዋል።
2.1K views16:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-18 19:04:18
2.0K views16:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-17 21:30:39 በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ቡሬ ካምፓስ ጫጩት ዶሮዎችን በማራባት እንቁላል ለግቢው ማህበረሰብ እያቀረበ መሆኑን ተገለፀ

===============
የደብረ ማርቆሰ ዩኒቨርሲቲ ቡሬ ካምፓስ፥ ጥር/2015 ዓ/ም

የደብረ ማርቆሰ ዩኒቨርሲቲ ቡሬ ካምፓስ ከመማር ማስተማር ተግባሩ በተጨማሪ ትላልቅ ፕሮጀክቶች ቀርጾ በመስራት ላይ ይገኛል ከእነዚህ ተግባራት መካከል በንብ እርባታ ፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ፣ በወተት ላም አርባታ ፣ በሻይ ቅጠልና ቡና እንዲሁም በዶሮ እርባታ ዙሪያ እየሰራ ይገኛል ፡፡

የካምፓሱ ችፍ አክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ብርሐኑ ዓለሙ ካምፓሳችን ለዶሮ እርባታ ምቹ በመሆኑ ጫጩት ዶሮዎችን ከአርባ ምንጭ በማስመጣት በግቢያችን ባዘጋጀነው ማዕከል እያራባን እንገኛለን ሲሉ ገልፀዋል፡፡

ዶሮዎች ሙሉ በሙሉ መጣል ሲጀምሩ ከደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አልፈን ለቡሬና አካባቢው ማህበረሰብ በተመጣጣኝ ዋጋ እንደሚያቀርቡ ገልፀዋል። ከእንቁላል በተጨማሪም የስጋ ዶሮዎችን በማራባት ለማህበረሰቡ ለማቅረብ በዕቅድ ይዘው እየተንቀሳቀሱ መሆናቸውንም ጨምረው ገልጸዋል፡፡

በቡሬ ካምፓስ የማህበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክተር ዶ/ር መለሰ ጋሹ እንደሚሉት ይህ ማዕከል በመቋቋሙ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታዎችን እንደሚሰጥ ጠቅሰው ለአብነትም በዘርፉ ለሚማሩ ተማሪዎችና ተመራማሪዎች እንደ ስልጠና ማዕከል ሆኖ ያገለግላል ብለዋል። በዚህ ዘርፍ የተደራጁ ወጣቶች፣ ሴቶች እናቶች የልምድ ልውውጥ የሚያገኙበትና እንደማስተማሪያ ማዕከልም ይገለገሉበታል ሲሉ ገልፀዋል። ማዕከሉ በአሁኑ ስዓት ለ8 ሰዎች የስራ ዕድል እንደፈጠረም ጨምረው ገልጸዋል ፡፡

የፕሮጀክቱ አስተባባሪ ዶ/ር ቻላቸው ይትባረክ እንደገለጹት በዚህ ማዕከል ውስጥ አራት ሺ የሚሆኑ የአንድ ቀን ጫጩቶችን አስመጥተው አስፈላጊውን ሳይንሳዊውን መንገድ በተከተለ ሁኔታ እንክብካቤ በማድረግ ላይ እንደሚገኙ ገልፀዋል።

///////////////////////////////

ከታች የተቀመጡትን በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ!

ዌብሳይት www.dmu.edu.et
ቴሌግራም https://t.me/Debre_Markos_University
ፌስቡክ https://www.facebook.com/dmu.edu
ዩቱዩብ https://www.youtube.com/channel/UCqQDHEyYDen3aybySpYsF_Q
ቲዊተር https://twitter.com/dmu_ethiopia
እንስታግራም https://www.instagram.com/dmu_ethiopia/
ሊንክድኢን https://www.linkedin.com/in/dmu-ethiopia/

"የዕውቀት አውድማ ከጮቄ ማማ!
1.8K viewsedited  18:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ