Get Mystery Box with random crypto!

Debre Markos University /ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ

የቴሌግራም ቻናል አርማ debre_markos_university — Debre Markos University /ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ D
የቴሌግራም ቻናል አርማ debre_markos_university — Debre Markos University /ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ
የሰርጥ አድራሻ: @debre_markos_university
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 25.10K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የቴሌግራም ገጽ ነው። የዩኒቨርሲቲያችን ወቅታዊ መረጃዎች፣ ልዩ ልዩ ሁነቶች እና የስራ እና የትምህርት ማስታወቂያዎች ይተላለፉበታል። አሁንኑ ቤተሰብ ለመሆን ይቀላቀሉ!!
This is Our Official Telegram Channel. We Provide up-to-date Information about our University.
Join Us Now!🙏

Ratings & Reviews

4.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 14

2023-01-23 17:13:57
6.1K views14:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-23 17:13:57
5.7K views14:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-23 17:13:52
5.7K views14:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-18 19:04:50 የደብረማርቆስ ዩኒቨርስቲ ቡሬ ካምፓስ መምህራን እና ሰራተኞች በስነ-ምግባር እና በፀረ ሙስና ዙሪያ ወይይት አደረጉ

=============

ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ቡሬ ካምፓስ፦ ጥር 9/2015 ዓ.ም በቡሬ ካምፓስ ወስጥ የሚታዩ የሙስናና የስነምግባር ችግሮችና አዝማሚያዎች ላይ ትኩረት ያደረገ ውይይት ተካሄደ።

የውይይቱን አስፈላጊነት በተመለከተ የቡሬ ካምፓስ ችፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተሩ ዶ/ር ብርሀኑ አለሙ እንደገለፁት ከሙስናና ከብልሹ አሰራሮች ፅዱ በማድረግና ምቹ የስራ አካባቢን በመፍጠር ተመራጭ የስራ ቦታን ለመፍጠር ታላሚ ያደረገ ወይይት መሆኑን ጠቅሰዋል።

የደብረማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ዳይሬክተር ኮማንደር ይበልጣል ደምሰው በበኩላቸው ይህ ውይይት ሲዘጋጅ ዋና ዓላማው በዋናው እና በቡሬ ካምፓሶች ያሉትን የሙስና ችግሮች በመፍታት ምቹ የስራ አካባቢን ለመፍጠር ነው ሲሉ ገልፀዋል።

በ2015 በ 6ወር ውስጥ በስነምግባር እና ፀረ ሙስና የተከናወኑ ስራዎች እና ያጋጠሙ ችግሮች በተመለከተም ሪፖርት ቀርቧል።

በሪፖርቱም በካምፓሱ ውስጥ ያላግባብ የተያዙ ሱቆች እንዲለቀቁ መደረጉ ፣ ያላግባብ የግቢውን ባህር ዛፍ ቆርጠው ለራሳቸው ጥቀም ሊያውሉ ሲሉ ተደርሶባቸው ለምግብ ቤት አገልግሎት እንዲውል መደረጉ ፤ ቤተመጻሕፍት ውስጥ ተሰርቀው የነበሩት የኮምፒውተር እቃዎች አንዲመለሱ መደረጉ፤ በግቢው ውስጥ ያላግባብ ቤት ተሰጧቸው የሚኖሩ መምህራን በህግ አግባብ ቤቱን የማስለቀቅ ስራ መሰራቱ የሚሉ ዋና ዋና ነጥቦች የተካተቱ ሲሆን የተገኙ መልካም ተሞክሮዎችን በሚመለከት ደግሞ ከፍትህ ፣ ከጥበቃ፣ ፖሊስ እና ከስነምግባር እና ከፀረ ሙስና ተቋማት ጋር በቅንጅት መሰራቱ ፤ ያጋጠሙ ችግሮችን በሚመለከት ደግሞ የንብረት ስርቆት ወንጀል መበራከት ፤ የተለያዩ ግለሰቦች ጥቆማ ወይም ቅሬታ በቂ ማስረጃአ አለመሟላት፤ የስነ ምግባር ተገዥነት ዝቅተኛ መሆን ፤ በአቋራጭ የመበልፀግ ፍላጎት መሆን የሚሉት በዋናነት ተጠቅሰዋል።
2.1K views16:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-18 19:04:18
2.0K views16:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-17 21:30:39 በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ቡሬ ካምፓስ ጫጩት ዶሮዎችን በማራባት እንቁላል ለግቢው ማህበረሰብ እያቀረበ መሆኑን ተገለፀ

===============
የደብረ ማርቆሰ ዩኒቨርሲቲ ቡሬ ካምፓስ፥ ጥር/2015 ዓ/ም

የደብረ ማርቆሰ ዩኒቨርሲቲ ቡሬ ካምፓስ ከመማር ማስተማር ተግባሩ በተጨማሪ ትላልቅ ፕሮጀክቶች ቀርጾ በመስራት ላይ ይገኛል ከእነዚህ ተግባራት መካከል በንብ እርባታ ፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ፣ በወተት ላም አርባታ ፣ በሻይ ቅጠልና ቡና እንዲሁም በዶሮ እርባታ ዙሪያ እየሰራ ይገኛል ፡፡

የካምፓሱ ችፍ አክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ብርሐኑ ዓለሙ ካምፓሳችን ለዶሮ እርባታ ምቹ በመሆኑ ጫጩት ዶሮዎችን ከአርባ ምንጭ በማስመጣት በግቢያችን ባዘጋጀነው ማዕከል እያራባን እንገኛለን ሲሉ ገልፀዋል፡፡

ዶሮዎች ሙሉ በሙሉ መጣል ሲጀምሩ ከደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አልፈን ለቡሬና አካባቢው ማህበረሰብ በተመጣጣኝ ዋጋ እንደሚያቀርቡ ገልፀዋል። ከእንቁላል በተጨማሪም የስጋ ዶሮዎችን በማራባት ለማህበረሰቡ ለማቅረብ በዕቅድ ይዘው እየተንቀሳቀሱ መሆናቸውንም ጨምረው ገልጸዋል፡፡

በቡሬ ካምፓስ የማህበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክተር ዶ/ር መለሰ ጋሹ እንደሚሉት ይህ ማዕከል በመቋቋሙ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታዎችን እንደሚሰጥ ጠቅሰው ለአብነትም በዘርፉ ለሚማሩ ተማሪዎችና ተመራማሪዎች እንደ ስልጠና ማዕከል ሆኖ ያገለግላል ብለዋል። በዚህ ዘርፍ የተደራጁ ወጣቶች፣ ሴቶች እናቶች የልምድ ልውውጥ የሚያገኙበትና እንደማስተማሪያ ማዕከልም ይገለገሉበታል ሲሉ ገልፀዋል። ማዕከሉ በአሁኑ ስዓት ለ8 ሰዎች የስራ ዕድል እንደፈጠረም ጨምረው ገልጸዋል ፡፡

የፕሮጀክቱ አስተባባሪ ዶ/ር ቻላቸው ይትባረክ እንደገለጹት በዚህ ማዕከል ውስጥ አራት ሺ የሚሆኑ የአንድ ቀን ጫጩቶችን አስመጥተው አስፈላጊውን ሳይንሳዊውን መንገድ በተከተለ ሁኔታ እንክብካቤ በማድረግ ላይ እንደሚገኙ ገልፀዋል።

///////////////////////////////

ከታች የተቀመጡትን በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ!

ዌብሳይት www.dmu.edu.et
ቴሌግራም https://t.me/Debre_Markos_University
ፌስቡክ https://www.facebook.com/dmu.edu
ዩቱዩብ https://www.youtube.com/channel/UCqQDHEyYDen3aybySpYsF_Q
ቲዊተር https://twitter.com/dmu_ethiopia
እንስታግራም https://www.instagram.com/dmu_ethiopia/
ሊንክድኢን https://www.linkedin.com/in/dmu-ethiopia/

"የዕውቀት አውድማ ከጮቄ ማማ!
1.8K viewsedited  18:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-17 21:29:15
1.8K views18:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-16 22:09:23 ከደረቅ ቆሻሻ የሚመረት ጭስ አልባ የከሠል ምርት ፕሮጀክት ይፋ ሆነ

====================

ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ፥ ጥር 8/2015 ዓ.ም
በዩንቨርስቲያችን የማህበረሰቡን ችግር ፈች የሆኑ በርካታ ፕሮጀክቶች ተቀርው ወደስራ ገብተዋል። በዛሬው ዕለትም ጭስ አልባ የከሠል ምርትን ለማህበረሰቡ ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል ፕሮጀክት የዩንቨርስቲው አመራሮች፣ ሠራተኞችና ከልማት ባንክ የመጡ እንግዶች በተገኙበት የፕሮጀክቱ ሀሣብና የተገኘውን ውጤት የማስተዋወቂያ መርሐ ግብር ተካሄደ፡፡

የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝደንት ዶ/ር አስካለ ማርያም አዳሙ ይህ ፕሮጀክት በአካባቢያችን ከሚገኙ ደረቅ ቆሻሻዎች የሚመረትና ጭስ አልባ በመሆኑ ለዩንቨርስቲውና ለከተማው ባጠቃላይ ለሀገራችን ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው የመስሪያ ቦታና ማሽኖች ተሟልተው በስፋት ወደስራ ይገባ ዘንድ ለፕሮጀክቱ ባለቤት እገዛ እንደሚያስፈልገው ገልፀዋል፡፡

የፕሮጀክቱ ባለቤት በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የሲቪል ምህንድስና መምህርና ተመራማሪ ፈቃዱ እንግዳ ይህ የከሰል ምርት ፦ ጭስ አልባ፣ ረዘም ላለ ጊዜ የሚነድ፣ የእሳት ብልጭታ የሌለውና ከአቧራ ነፃ በመሆኑ በባህላዊ መንገድ ከሚመረተው ከሰል እንደሚለይ ገልጿል። ከተማን ፅዱ ለማድረግ፣ደንና አካባቢን ለመጠበቅ፣ የሴቶችና ህፃናትን ጤናና ደህንነት ለመጠበቅ፣የስራ ዕድል ለመፍጠርና የኢኮኖሚ ድጋፍ ለማድረግ ጠቀሜታው የጎላ እንደሆነም አስረድቷል፡፡

ከከሰሉ በተጨማሪም ለተፈጥሮ ማዳበሪያና የዕፅዋትን ተባይና ፈንገስ ለመከላከል የሚያስችሉ የእንጨት ኮምጣጤና የእንጨት ሬንጅ የተሰኙ ምርቶች ማምረት እንደሚቻልም አሳይተዋል፡፡

በኢኖቬሽን ሚኒስቴር እውቅናና ሽልማት እንዳገኘም ተጠቅሷል፡፡

አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ይኼይስ አረጉ ተምሮ ራስን ከመለወጥ አልፎ ለማህበረሠቡ ትልቅ ፋይዳ ያለው ስራ መስራት የሚደነቅና የሚበረታታ ስለሆነ የዩንቨርስቲውም ሆነ የከተማው ማህበረሰብ ድጋፍና ክትትል ማድረግ አለበት ብለዋል፡፡

ከታች የተቀመጡትን በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ!

ዌብሳይት www.dmu.edu.et
ቴሌግራም https://t.me/Debre_Markos_University
ፌስቡክ https://www.facebook.com/dmu.edu
ዩቱዩብ https://www.youtube.com/channel/UCqQDHEyYDen3aybySpYsF_Q
ቲዊተር https://twitter.com/dmu_ethiopia
እንስታግራም https://www.instagram.com/dmu_ethiopia/
ሊንክድኢን https://www.linkedin.com/in/dmu-ethiopia/

"የዕውቀት አውድማ ከጮቄ ማማ!"
877 viewsedited  19:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-16 22:05:20
1.0K views19:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-15 05:27:13 የደብረ ማርቆሰ ዩኒቨርሲቲ ከኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በግብርናና ተፈጥሮ ሀብት እንዲሁም በመሬት አስተዳደር ትምህርት ክፍሎች በ2015 ዓ.ም ለሚሰጠው የመውጫ ፈተና ንድፈ ማሳያ ዝግጅት ( Blue Print Preparation ) ዙሪያ ዐውደ ጥናት አካሄደ

===================

በ2015 ዓ.ም ለግብርናና ተፈጥሮ ሀብት እንዲሁም ለመሬት አስተዳደር ትምህርት ክፍሎች ተመራቂ ተማሪዎች ለሚሰጠው የመውጫ ፈተና ንድፈ ማሳያ ዝግጅት (Blue Print Preparation ) ከጥር 4 -5 /2015 ዓ.ም ለሁለት ቀናት በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተካሄዷል፡፡

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሪዚዳንት ዶ/ር ይኸይስ አረጉ እንደገለጹት የመውጫ ፈተና የትምህርት ጥራትን ከምናስጠብቅባቸው መንገዶች አንዱ በመሆኑ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ልዩ ትኩረት በመስጠት መስራት ይገባቸዋል አሁን ላይ ሁለት ትውልድ ይታየኛል 1ኛው የአድዋው ትውልድ ሲሆን 2ኛው ደግሞ የአሁኑ ትውልድ ነው ? በአድዋ ትውልድ የነበረው ጥያቄ የነጻነት ፣ የአንድነት የዘመናዊነት የነበር ሲሆን እሱንም አባቶቻችን በጠመንጃ በአፈሙዝ ድል አድርገው አልፈውታል ፤ አሁን ደግሞ ሳይንሳዊ ዕውቀት የህልውና ጥያቄ እየሆነ እየመጣ ነው። ሳይንሳዊ ዕውቀትን በደንብ ያልታጠቀ ትውልድ ችግርን ተቋቁሞ መኖር አይችልም ፤ እሳካሁን የመጣንበትም የመቶ ዓመት የትምህርት ሥረዓት በብዙ ችግሮች የታጠረ በመሆኑ እሱን ካለበት ችግር መንጥቆ ለማውጣት ከምሁራን ብዙ ይጠበቃልና እንዲህ አይነት ውይይቶች ተጠናክረው መቀጠል ይኖርባቸዋል ብለዋል።

በዚህ የውይይት መርሐ ግብር ላይ ከኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርት ሚኒሲቴር የከፍተኛ ትምህርት ብቃትና ጥራት ማረጋገጥ ዴስክ ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ሲሳይ ሰሙ እንደገለጹት በትምህርት ሚኒሲቴር ለ2015 ዓ.ም ተመራቂ ተማሪዎች የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና አተገባበር በተመለከተ ከመስከረም 2015 ዓ.ም ጀምሮ በርካታ ተግባራት ሲከናወን መቆየቱን ጠቅሰው ተማሪዎች የሚማሯቸውን ትምህርቶች በቂ ዕውቀት፣ ክህሎትና አመለካከት መጨበጣቸውንና ሀገሪቱ የምትፈልገውን የተማረ የሰው ኃይል በበቂ ጥራት መዘጋጀታቸውን ለማረጋገጥ ሁሉም የ2015 ዓ.ም የመንግስትም ሆነ የግል ተቋማት ተማሪዎች መውጫ ፈተናውን እንዲወስዱ ለማድረግ የፈተና ንድፈ ማሳያ (Blue print ) እየተዘጋጀ ይገኛል ብለዋል፡፡

ፈተናውን በቴክኖሎጂ እንዲሰጥ ለማድረግም በየዩኒቨርሲቲዎች ከ30 ሺ በላይ ኮምፒውተሮችን ከኢንተርኔት ጋር መገናኘታቸውን ገልፀዋል። በዚህ ዓመት በሚሰጠው የመውጫ ፈተናም በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ከ110 ሺህ ተማሪዎች እና ከግል ተቋማት ደግሞ 140 ሺህ በላይ ተማሪዎች ያልፋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅም ገልፀዋል ፡፡

በመጨረሻም ይህ የመውጫ ፈተና በሀገራችን ለመጀመሪያ ጊዜ የሚሰጥ እንደመሆኑ ተቋማት ተማሪዎቻቸውን በበቂ ሁኔታ ዝግጁ እንዲያደርጉ ፤ መምህራንም ተማሪዎቻቸውን በሚገባ ማገዝና ማብቃት ላይ ትኩረት እንዲሰጡ ፤ ተማሪዎችም በዚህ ዓመት የሚሰጠው የመውጫ ፈተና የማይቀር መሆኑን አውቀው ጊዜያቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙ እና ራሳቸውን ለዚህ ፈተና ዝግጁ እንዲያደርጉ መልዕክታቸውን አጠቃለዋል ፡፡
3.2K viewsedited  02:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ