Get Mystery Box with random crypto!

Debre Markos University /ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ

የቴሌግራም ቻናል አርማ debre_markos_university — Debre Markos University /ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ D
የቴሌግራም ቻናል አርማ debre_markos_university — Debre Markos University /ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ
የሰርጥ አድራሻ: @debre_markos_university
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 25.10K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የቴሌግራም ገጽ ነው። የዩኒቨርሲቲያችን ወቅታዊ መረጃዎች፣ ልዩ ልዩ ሁነቶች እና የስራ እና የትምህርት ማስታወቂያዎች ይተላለፉበታል። አሁንኑ ቤተሰብ ለመሆን ይቀላቀሉ!!
This is Our Official Telegram Channel. We Provide up-to-date Information about our University.
Join Us Now!🙏

Ratings & Reviews

4.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 15

2023-01-15 05:24:37
3.1K views02:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-13 16:24:57
2.6K views13:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-13 14:40:21 በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርስቲ የአካል ጉዳተኛ ተማሪዎች መረጃ ማዕከል ተቋቋመ

==============

ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ:- ጥር 04/2015 ዓ.ም (ህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት)

ኖርዌይ ውስጥ የሚገኙ ሁለት ዩኒቨርሲቲዎች ሀገር ውስጥ ከሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች በጋር በመተባበር በደብረማርቆስ ዩኒቨርስቲ ለሚማሩ የአካል ጉዳተኛ ተማሪዎች የሚያገለግል የመረጃ ማዕከል ማቋቋማቸውን የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርስቲ ምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዚዳንት ዶ/ር አስካለ ማርያም አዳሙ ገለፁ ።

የተቋቋመው ማዕከል ልዩ ልዩ የአካል ጉዳት ላለባቸው ተማሪዎች ስልጠናቸውን ማመቻቸት፣ ልዩ ለዩ አጋዥ የትምህርት ቁሳቁሶችን ማፈላለግ ላይ እንደሚሰራ እና በተለይም በችግሩ ውስጥ የሚገኙ ተማሪዎች አምዕሯቸውን በተገቢው መንገድ እንዲጠቀሙበት የስነ ልቦና ስልጠናዎችንም እንደሚሰጥ አክለው ገልፀዋል።

በማዕከሉ አገልግሎት እንዲሰጡ ታስቦ ባሳለፍነው የፈረንጆች ዓመት ብሬሎችና የድምፅ መቅጃዎች መገዛታቸውንም ጨምረው ተገልፀዋል።

በማዕከሉ የታቀፉ 21 የሚሆኑ የአካል ጉዳት ያለባቸው ተማሪዎች ከህዳር ጀምሮ ወራዊ ከፍያ እንዲያገኙ እንደተደረገም ተገልጿል።

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ታፈረ መላኩ በኩላቸው በደብረማርቆስ ዩኒቨርስቲ የተለያዩ የአካል ጉዳት ያለባቸው ተማሪዎች መኖራቸውን ጠቀሰው ለእነሱ የሚሆን የመረጃ ማዕከል ባለመኖሩ ከፍተኛ የሆነ ችግር ይገጥማቸው ነበር ብለዋል።

መረጃ ማዕከሉን በበቂ ቁሳቁሶች ለማደራጀት እንቅስቃሴእየተደረገ መሆኑን ገልፀው ባለድርሻ አካላትም የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ መልዕክት አስተላልፏል።

ዌብሳይት www.dmu.edu.et
ቴሌግራም https://t.me/Debre_Markos_University
ፌስቡክ https://www.facebook.com/dmu.edu
ዩቱዩብ https://www.youtube.com/channel/UCqQDHEyYDen3aybySpYsF_Q
ቲዊተር https://twitter.com/dmu_ethiopia
እንስታግራም https://www.instagram.com/dmu_ethiopia/
ሊንክድኢን https://www.linkedin.com/in/dmu-ethiopia/

"የዕውቀት አውድማ ከጮቄ ማማ!"

ከእኛ ጋር ሰለሆናችሁ ምስጋናችን የላቀ ነው!
868 viewsedited  11:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-13 14:39:52
847 views11:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-13 14:39:51
775 views11:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-13 14:39:46
863 views11:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-11 11:56:34 የደብረ ማርቆስ ዩንቨርሲቲ ተማሪዎች አንድ ጉርሻ ለወገኔ በሚል ድጋፍ አሰባስበው የገና በዓልን አቅም ከሌላቸው ወገኖች ጋር ማሳለፋቸውን ገለፁ
================

የዩንቨርሲቲው ተማሪዎች ከተማሪዎች ህብረት አመራሮች ጋር በመተባበር አንድ ጉርሻ ለወገኔ በሚል ከዩንቨርሲቲው ማህበረሰብ ድጋፍ በማሰባሰብ በተለያዩ ምክንያቶች በዓልን ለማክበር አቅም የሌላቸው ወገኖችን በመለየትና ለበዓል የሚሆኑ ቁሳቁሶችን በማሟላት በዓልን በደስታ እንዲያሳልፉ አድርገዋል፡፡

በዩንቨርሲቲው የአራተኛ ዓመት የኮንስትራክሽን ማኔጅመንትና የድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴው ሰብሳቢ ተማሪ ቶማስ አበባው እኛ በዓልን ተደስተን ስንውል በጎነት ለራስ ነውና ለምን የአቅማችንን በማድረግ ወገኖቻችንን አናስብም በሚል ድጋፉን ለማድረግ እንደተነሳሱና ልምድ ካላቸው ተማሪዎች ህብረት ጋር በመተባበር ገንዘብ ከማሰባሰብ ጀምሮ ከብት ገዝቶ እስከ ምገባ ድረስ በመስራት ከ200 በላይ አቅም ለሌላቸው ወገኖች ተደራሽ እንዳደረጉ ተናግሯል፡፡

ሌላው የአራተኛ አመት የመካኒካልና ኢንደስትሪያል ምህንድስ ተማሪና እንዲሁም የተማሪዎች ህብረት የፋይናንስ ክፍል ተጠሪ ተማሪ ደርበው መላክ በዓሉን ከግል ደስታ ይልቅ ሌሎችን ማሰብ ትልቅ የአዕምሮ እርካታ እንደሚሰጥ ገልፆ በማማከርና ገንዘቡን በተመለከተ ክትትል በማድረግ የበኩሉን ድርሻ እንደተወጣ ተናግሯል፡፡

ባጠቃላይ ከዩንቨርሲቲው ማህበረሰብ 30 ሺ ብር አሰባስበው የቀንድ ከብትና አስፈላጊ ቁሳቁሶችን በማሟላት በዓልን ከወገኖቻቸው ጋር ማክበራቸው ለወደፊቱም መነሳሳትን ፈጥሮልናል ብሏል፡፡

ለወደፊቱም ሁሉም ማህበረሰብ ይህንን ቢለምድና በሰፊው ቢሰራበት የተሻለ እንደሚሆን አሳስቦ በእነሱ በኩልም አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልፁዋል፡፡

የተማሪዎች ህብረት ፕሬዝዳንት ተማሪ ጌጤነህ ሸገን ከዚህ በፊትም ተማሪዎች በግላቸው አንዳንድ ድጋፎችን ሲያደርጉ መቆየታቸውን ገልፆ ለበዓልም አቅም የሌላቸውንና የተፈናቀሉ ወገኖችን በተወሰነ መልኩ ስሜታቸውን መጋራት ተችሏል ብሏል፡፡ በተማሪዎች ህብረት በጎ አድራጎት ዘርፍም አልባሳትን በማሰባሰብ ድጋፍ ማድረግ እንደተቻለና ወደፊትም በቋሚነት ለመስራት ቁርጠኛ መሆኑን ተናግሯል፡፡ በመጨረሻም የዩንቨርሲቲው ማህበረሰብ በቀናነት ትብብር ስላደረገላቸውና የከተማው ማህበረሰብም ሁሌም ከጎናቸው ስለሆነ አመስግኗል፡፡


ዌብሳይት www.dmu.edu.et
ቴሌግራም https://t.me/Debre_Markos_University
ፌስቡክ https://www.facebook.com/dmu.edu
ዩቱዩብ https://www.youtube.com/channel/UCqQDHEyYDen3aybySpYsF_Q
ቲዊተር https://twitter.com/dmu_ethiopia
እንስታግራም https://www.instagram.com/dmu_ethiopia/
ሊንክድኢን https://www.linkedin.com/in/dmu-ethiopia/

"የዕውቀት አውድማ ከጮቄ ማማ!"

ከእኛ ጋር ሰለሆናችሁ ምስጋናችን የላቀ ነው!
3.4K viewsedited  08:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-11 11:56:32
3.2K views08:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-11 08:10:14
በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ማህበራዊ ሳይንስና ስነ ሰብ ኮሌጅ የእንግሊዝኛ ቋንቋና ስነ ፅሑፍ ትምህርት ክፍል የመጀመሪያ ዙር የሶስተኛ ድግሪ (PH.D) ሁለት ዕጩ ተመራቂዎችን በነገው ዕለት ማለትም ጥር 04/2015 ጥዋት 2:30 እና ከስዓት ከ8:30 ጀምሮ የመመረቂያ ፅሑፋቸውን እንዲያቀርቡ ያደርጋል። ስለሆነም ፍላጎቱ ያላችሁ የግቢያችን ማህበረሰብ በሙሉ በንግስተ ሳባ አዳራሽ በመገኘት ከላይ በተጠቀሰው ስዓት መሠረት መከታተል የምትችሉ መሆኑን እናሳስባለን!
1.3K viewsedited  05:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-10 21:31:17 ልዩ ትኩረት የተሰጣቸው ስድስት ፕሮጀክቶች ተገመገሙ

=======================

የደ/ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ በ2015 ዓ.ም ብቻ ለእያንዳንዳቸው ከአምስት መቶ ሺ (500,000) ብር በላይ የተመደበላቸውን ስድስት ፕሮጀክቶች በማኔጅመቱ የበጀት አመዳድቡን፣ የበጀት አጠቃቅሙንና የግዥ ስርዓቱን በተመለከተ ግምገማ አደረገ፡፡

የዩኒቨርስቲያችን ፕሬዝዳንት ታፈረ መላኩ (ዶ/ር) እንደገለፁት ፕሮጀክቶቻችን ውጤታማና ዘላቂ መሆን የሚችሉት ማህበረሰቡ ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻው በአግባቡና በግልጸኝነት ሲሳተፍ መሆኑን ገልጻው ማህበረሰቡ በጉልበቱ፣ በሙያውና በገንዘቡ የሚጠበቅበትን አስተዋጽኦ ማድረግ አለበት ብለዋል፡፡

ሁሉም የዩኒቨርስቲያችን ማህበረሰብ ፕሮጀክቶችን በሚሰራ ጊዜ ልክ እንደሸበል በረንታው ፕሮጀክት አጋዥ አካላትን በማሳተፍ ሊሆን ይገባል፡፡ ለሸበል በረንታው የተቀናጀ ፕሮጀክት ለሶስት ዓመት ከተመደበው 31 ሚሊዮን ብር ውስጥ 25 ፐርሰንቱ ማለትም 7.9 ሚሊዮን ብር ዩኒቨርስቲው ሲሸፍን ቀሪው 75 ፐርሰንቱ ከ23 ሚሊዮን ብር በላይ የሚሆነው በጀት Bread for the World በተባለ ዓለም አቀፍ ድርጅት መሸፈኑ ትልቅ መማሪያ ሊሆነን ይገባል ብለዋል፡፡

የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር አስካለማርያም አዳሙ ፕሮጀክቶችን በሚመለከተው ባለሙያ በዝርዝር ስናስገመግም መመሪያችንን መሰረት አድርገን የማህበረሰቡን ተሳትፎ ሊያረጋግጥ በሚችል መልኩ በአግባቡ አይተናል፤ አሁንም በዩኒቨርስቲው ማኔጅመት የሚሰጡንን አስተያይቶች በአግባቡ ይዘን እንተገብራቸዋለን ሲሉ ገልጸዋል፡፡

ስድስቱም ፕሮጀክቶች በፕሮጀክት መሪዎች የቀረቡ ሲሆን ለ2015 ዓ.ም የማህበረሰብ ተሳትፎን በመጨመር የጸደቀላቸው በጀት

1. የማህፀን በር ካንሰር ፕሮጀክት ብር 612 ሺ
2. የዓይነ ስውራን ተማሪዎች ሽንት ቤት ግንባታ ፕሮጀክት ብር 618 ሺ
3. የመድሐኒታማ ዕፅዋት ፕሮጀክት የእንሰሳት ቤት ግንባታ 1.5 ሚሊዮን
4. የወይንማ ገራሞ ፕሮጀክት ብር 2.8 ሚሊዮን
5. የኳሽባ ቀበሌ የአካባቢ ጥበቃ ፕሮጀክት ብር 4.58 ሚሊዮን
6. የሸበል በረንታ የተቀናጀ የአቅም ግንባታን የልማት ፕሮጀክት 13 ሚሊዮን ብር

በአጠቃላይ ብር 23.11 ሚሊዮን የሚወስዱ ፕሮጀክቶች በአስቸኳይ ወደ ስራ ይገቡ ዘንድ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡

በመጨረሻም ዶ/ር ታፈረ መላኩ በጥብቅ ዲሲፕሊን እየተራን የምሁራንን አቅም በአግባቡና በተጨባጭ ስራዎች ላይ በማዋል የማህበረሰባችንን ችግሮች ጠንከር ባሉ ፕሮጀክቶች ማቃለል ተልዕኳችን ነው ሲሉ ገልፀዋል፡፡
1.5K viewsedited  18:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ