Get Mystery Box with random crypto!

አዲስ መረጃ

የቴሌግራም ቻናል አርማ assebpress — አዲስ መረጃ
የቴሌግራም ቻናል አርማ assebpress — አዲስ መረጃ
የሰርጥ አድራሻ: @assebpress
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.82K
የሰርጥ መግለጫ

ትኩስ መረጃ

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2022-11-30 14:29:16 ሰበር ዜና

አሁን በደረሰን መረጃ መሰረት የኤርትራ ሰራዊት ትግራይ ክልልን ሙሉ ለሙሉ ለቆ ወጥቷል።
535 viewsHusen Mohammed, 11:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-29 23:02:38
በጅቡቲ ከኢንተርኔት መቋረጥ ጋር ተያይዞ የኢትዮ ሳት ቻናሎች ስርጭት ተቋርጧል
በጅቡቲ ከኢንተርኔት መቋረጥ ጋር ተያይዞ የኢትዮ ሳት ቻናሎች ስርጭት መቋረጡን ኤስ ኢ ኤስ ኢትዮጵያ አስታወቀ፡፡
የኢንተርኔት መቋረጡ ሁሉንም አገልግሎቶች አስተጓጉሏል ያሉት የተቋሙ የምሰራቅ አፍሪካ ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ መነን አገኘሁ ችግሩን ለመፍታት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
እስካሁን ባለው ሂደትም አንዳንድ አገልግሎቶችን መመለስ ተችሏል ያሉት ኋላፊዋ፣ ሁሉንም አገልግሎቶች ወደነበሩበት ለመመለስ ጥረት እየተደረገ መሆኑንም አሳውቀዋል።
በአሸናፊ እንዳለ
==================
ለፈጣን መረጃ የቻናሌ ቤተሰብ ይሁኑ፣ለሌሎች ጋብዙ
599 viewsHusen Mohammed, 20:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-29 14:21:48
ዓለም ዋንጫ
#3ኛ_ዙር_የአለም_ዋንጫ_የምድብ_ጨዋታዎች!!!
ጨዋታዎቹ በዚህ ሳምንት 4 ጨዋታዎች ዛሬ #ማክሰኞ፣4 ጨዋታዎች ነገ #ረቡዕ ፣4 ጨዋታዎች #ሐሙስ እና 4 ጨዋታዎች #አርብ ይደረጋሉ!
ኳታር እና ካናዳ ወድቀው ለሟሟያ የሚጫወቱበት
ፈረንሳይ ፣ ፖርቹጋል እና ብራዚል አልፈው ለሟሟያ ይጫወታሉ
ሴኔጋል ወደ ቀጣዩ ለማለፍ የግድ እኳዷርን ማሸነፍ ግድ ይሆንባታል
አሜሪካ የግድ ማሸነፍ የሚጠበቅባት
ኢራን አቻ ያሳልፋታል
አርጀንቲና የግድ ማሸነፍ ያለባት ጨዋታ
ሳውዲ አረቢያ፣አርጀንቲና እና ፖላንድ የግድ ማሸነፍን እያሰቡ ይገባሉ
ቤልጂየም ካላሸነፈች የምትወድቅበት
የኛዋ አፍሪካ ሞሮኮ አቻ ብቻ እንዲሚያሳልፋት እያወቀች ወደ ሜዳ ትገባለች
ስፔን፣ጃፓን፣ ኮስታ ሪካ እና ጀርመን ማሸነፍን ብቻ እያሰቡ የሚገቡበት ቢሆንም ስፔን አቻ ያሳልፋታል(ብዙ ንፁህ ግቦች አሏት)
ዩራጓይ ማሸነፍ ብቻ ሲሆን ጋና ኮሪያ ተሸንፋ ወይም አቻ ተለያይታ በጨዋታ አቻ ከተለያየች የሚያሳልፋትን ተስፋ ይዛ ወደ ሜዳ ትገባለች።
===================
628 viewsHusen Mohammed, 11:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-26 16:57:34
መረጃ
ትላንት በአርሲ ዞን ጀጁ ወረዳ አጫሞ ቀበሌ ኦነግ ሸኔ በዶክተር አለሙ ስሜ ላይ የቦምብ ጥቃት ሙከራ አድርጎባቸው እንደነበር ታውቋል።
501 viewsHusen Mohammed, 13:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-25 19:05:37
594 viewsHusen Mohammed, 16:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-25 19:05:33 የጉራጌ ዞን ከዛሬ ጀምሮ በኮማንድ ፖስት እንዲመራ ውሳኔ ተላለፈ

በደቡብ ክልል የሚገኘው የጉራጌ ዞን ከዛሬ አርብ ህዳር 16፤ 2015 ጀምሮ በኮማንድ ፖስት እንዲመራ መወሰኑን የክልሉ ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ አለማየሁ ባውዲ አስታወቁ። የጉራጌ ዞን በኮማንድ ፖስት ስር እንዲሆን የተደረገው፤ ከክልል አደረጃጀት ጥያቄ ጋር በተያያዘ በአካባቢው የተፈጠረውን የጸጥታ ችግር “በመደበኛ አሰራር ለማስተዳደር” ባለመቻሉ መሆኑን የቢሮ ኃላፊው ገልጸዋል።

የደቡብ ክልል ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ ይህን ያስታወቁት፤ የጉራጌ ዞን ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ ትላንት ሐሙስ በሰጡት መግለጫ ነው። የጉራጌ ዞን በተደራጀ ኮማንድ ፖስት እንደሚመራ ትላንት ምሽት በደቡብ ክልል ቴሌቪዥን በተላለፈው መግለጫቸው ይፋ ያደረጉት አቶ አለማየሁ፤ “የኦፕሬሽኑን ስራ” የፌደራል ፖሊስ እና የክልሉ ልዩ ኃይል በቅንጅት እንደሚመሩ ተናግረዋል።

ሁለቱ አካላት ሌሎች የጸጥታ ኃይሎችን ይዘው፤ በተደራጀ መንገድ በአካባቢው ውስጥ እየተፈጠረ ያለውን የጸጥታ ችግር እንደሚያስተዳድሩ የቢሮ ኃላፊው ገልጸዋል። በደቡብ ክልል በማዕከል ደረጃ ይህንን የሚያስተባብር አካል መቋቋሙንም አክለዋል።

ኮማንድ ፖስቱ “በተደራጀ መንገድ በጥፋት ውስጥ ተቀላቅለው ይንቀሳቀሱ የነበሩ ኃይሎችን በቁጥጥር ስር” የማዋል ተግባር እንደሚያከናውን አቶ አለማየሁ በመግለጫቸው ጠቁመዋል። “የጥፋት ይዘቱን ያቀደ፣ የመራ፣ ያስተባበረ፣ አጥፊ ድርጊት የፈጸመ፤ በግለሰብም፣ በቡድን ደረጃም እየተንቀሳቀሱ ያሉ ኃይሎች በደንብ በተደራጀ መንገድ ተለይተዋል” ያሉት የክልሉ ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ፤ “የጸጥታ ኃይሉ እነዚህ ኃይሎችን በሙሉ በቁጥጥር ስር ያውላል” ሲሉ በቀጣይነት የሚወሰዱ እርምጃዎችን አመልክተዋል።

እስካሁን በተደረገው ጸጥታን የማስከበር ስራ፤ በድርጊቱ ተሳተፈዋል የተባሉ ከ70 በላይ ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አቶ አለማየሁ ተናግረዋል። “የጸጥታ አካላችን ቀጥታ እዚህ ላይ ተሳታፊ የነበሩ፣ ፊት ለፊት የተገኙ ከ70 በላይ ሰዎችን ይዟል” ያሉት የቢሮ ኃላፊው፤ ይህን ተከትሎም በተጠርጣሪዎቹ ላይ “በተደራጀ መንገድ ምርመራ የማጣራት ሂደት” እንደሚደረግ አስረድተዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)

[በዚህ ዘገባ ላይ ተጨማሪ መረጃዎች ታክለዋል]
562 viewsHusen Mohammed, 16:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-25 19:05:16
472 viewsHusen Mohammed, 16:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-25 19:05:13 በጉራጌ ዞን ኮማንድ ፖስት የተከለከሉ ተግባራት እና የሚወሰዱ እርምጃዎች ምንድናቸው?

የደቡብ ክልል ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ አለማየሁ ባውዲ ትላንት ሐሙስ በሰጡት መግለጫ ካነሷቸው ነጥቦች ውስጥ የተወሰዱ፦

“የትኛውም ቦታ ላይ፣ የትኛውም ኪስ ቦታ ላይ፣ የትኛውም መንደር ላይ፣ የትኛውም አዳራሽ ውስጥ ያልተፈቀዱ ስብሰባዎች ማድረግ፣ እንቅስቃሴዎች ማድረግ በፍጹም የማይፈቀድ ነው የሚሆነው።”

“አሁን እንደሚታወቀው አጥፊው ቡድን ሰላማዊ ሰልፍ ይጠራል። ሲፈልግ ይከለክላል። ሲፈልግ ‘አቁሜያለሁ’ ይላል። ሲፈልግ ‘ቀን ቀይሬያለሁ’ እያለ በተለያየ መንገድ ህዝቡን እያወናበደ ነው ያለው። በዚህ መንገድ የመንግስት ተቋማት እና በየደረጃው ያሉ የመንግስት አመራሮች ካልሆኑ በስተቀር፤ ህጋዊ በሆነ መንገድ የሚጠሩ ስብሰባዎች፣ ህዝባዊ ሰልፎች ካልሆኑ በስተቀር፣ በየትኛውም መንገድ በህገ ወጥ መንገድ በተከፈቱ (ፌክ) አካውንቶች የሚተላለፉ መልዕክቶች እና ጥሪዎች ተቀባይነት የላቸውም።”

“ከዚህ በኋላ ለጥፋት የሚንቀሳቀሱ ቡድኖች፣ በህግ ያልተፈቀደላቸውን እንቅስቃሴ የሚያደርጉ አካላት፣ ኃላፊነት ከተሰጣቸው የመንግስት አመራሮች ውጪ ህጋዊ ባልሆነ በየትኛውም መንገድ የትኛውንም እንቅስቃሴ የሚያደርጉ አካላት ላይ የጸጥታ ኃይሎች ሁሉንም አይነት የህግ እርምጃ ይወስዳሉ።”

“እዚህ ሀገር ህግ ስላለ፣ ህግ ደግሞ ለሁሉም እኩል ስለሆነ፤ አጥፊ ድርጊት የፈጸመ ላይ በሙሉ ህጋዊ እርምጃ ይወሰዳል።”

“ህዝቡ ያነሳው ነባራዊ ሁኔታ እና በመሬት ላይ እየሆነ ያለው ጉዳይ የማይገናኙ እና ፍጹም ተቃራኒ የሆኑ ድርጊቶች ስለሆኑ በተደራጀ መንገድ ጥፋት ውስጥ ተቀላቅለው ይንቀሳቀሱ የነበሩ ኃይሎች በቁጥጥር ስር ይውላሉ።”

“የጥፋት ይዘቱን ያቀደ፣ የመራ፣ ያስተባበረ፣ አጥፊ ድርጊት የፈጸመ፤ በግለሰብም፣ በቡድን ደረጃም እየተንቀሳቀሱ ያሉ ኃይሎች በደንብ በተደራጀ መንገድ ተለይተዋል። እነዚህን ኃይሎች በሙሉ ጸጥታ ኃይሉ በቁጥጥር ስር ያውላል።”

[ በ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” የተጠናቀረ]
509 viewsHusen Mohammed, 16:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-23 14:18:03
ጥፊ ቀምሱ ..

በየ ጊዜው በየሄደበት ጥፊ የሚቀምሰው ኢማኑኤል ማክሮን ትናንት አዲስ ጥፊ ቀመሰ
417 viewsHusen Mohammed, 11:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-22 19:34:50
የሳዑዲ ዓረቢያው ንጉሥ ነገ የዕረፍት እና የደስታ መግለጫ ቀን ሆኖ እንዲከበር አወጁ
****************


የሳዑዲ ዓረቢያው ንጉሥ ሳልማን ቢን አብዱልአዚዝ አል ሳዑድ፣ የሀገሪቱ ብሔራዊ ቡድን በአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን ላይ ያስመዘገበውን አስደናቂ ድል ተከትሎ ነገ (ረቡዕ) በመላ ሀገሪቱ የዕረፍት እና የደስታ መግለጫ ቀን ሆኖ እንዲከበር አውጀዋል።

በዚህም መሠረት በነገው ዕለት በሀገሪቱ የሚገኙ ሁሉም የመንግሥት እና የግል ሠራተኞች እንዲያርፉ እና በሁሉም ደረጃ የሚገኙ ተማሪዎች ትምህርት ቤት እንዳይገቡ ተደርጓል።

መላው የሳዑዲ ዓረቢያ ዜጎች እና በሀገሪቱ የሚኖሩ ሁሉ ቀኑን በደስታ እንዲያሳልፉ ተፈቅዶላቸዋል ሲል የዘገበው ሳዑዲ ጋዜጣ ነው።

ሳዑዲ ዓረቢያ በ2022ቱ የዓለም ዋንጫ በምድብ C ከአርጀንቲና ጋር ያደረገችውን ጨዋታ 2 ለ 1 በሆነ ውጤት ማሸነፏ ይታወሳል።
529 viewsHusen Mohammed, 16:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ