Get Mystery Box with random crypto!

አዲስ መረጃ

የቴሌግራም ቻናል አርማ assebpress — አዲስ መረጃ
የቴሌግራም ቻናል አርማ assebpress — አዲስ መረጃ
የሰርጥ አድራሻ: @assebpress
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.82K
የሰርጥ መግለጫ

ትኩስ መረጃ

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2023-02-23 17:02:46 ብልፅግና ማለት መተማመን በሌላቸው የፖለቲካ ሀይሎች የተመሰረተ ብቻ ሳይሆን ከስህተቱ ተምሮ እየበሰለ መሄድ የማይችልና በማንኛውም መንገድ ስልጣን ላይ ለመቆየት ሲል አገር አፍራሽ ጥፋቶችን የሰራ እና አሁንም እየሰራ የሚገኝ የግርግር ቡድን ነው።
253 viewsHusen Mohammed, 14:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-20 16:43:33
የአፍሪካው አብሪ ኮከብ #አብያችን

በመንደር የተጠለፈ ሳይሆን ለዓለም የሚበቃ እውቀትን ይዞ የሚመራን ድንቅ መሪ ነው አፍሪካም የመጪው ዘመኗን ተስፋ በዚህ ወጣት መሪ ላይ ሙሉ በሙሉ ጥላለች #አብቹ_አባመላ አንተ ለመላው አፍሪካ ኩራት ነህ
255 viewsHusen Mohammed, 13:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-16 03:19:18 ከመተኛታችሁ በፊት እቺን መልሱልኝ በእናታችሁ

ልጅ አላቸው ፣ ሚስት አላቸው ፣ ዝሙት ይሰራሉ ፣ ሺሻ ያጨሳሉ ....እያላችሁ አልነበር ታዲያ እውነት ከነበር ዘመቻችሁ አሁን ልጅ ላለው ጳጳስ ፣ ሚስት ላለው ጳጳስ ነው ክህነት መልሰናል የምትሉት ? አይ እናንተ በውሸት ፎቶሾፕ እየሰራችሁ ስም በማጥፋት ግን ስንቱን ሰዎ አታለላችሁ ? በውሸት የጳጳሳቶችን ስም በማጥፋታችሁስ ሀጥያታችሁ ለ ገሀንም እንኳን መስፈርቱን ያሟላል ? ሴጣን እኮ እናንተን ባየ ሰዓት በቅናት ሰከረ።ባለማወቅ በፅንፈኞች ወንበዴዎች የውሸት የፎቶሾፕ ዘመቻ ተታላችሁ አባቶችን የተሳደባችሁ ዛሬውኑ ንስሀ ግቡ
244 viewsHusen Mohammed, 00:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-15 01:57:27 ስበር ?!

በአፋር ክልል በእስር ላይ የሚገኙ ወጣቶችን ጉዳይ በተመለከተ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የወጣቶች ክንፍ መግለጫ፤

በተለያዩ አከባቢ ያሉ የሀገራችን ወጣቶች በተለያዩ ፖለቲካ ፓርቲዎች ታቅፈው ዋስትና ያለው ዴሞክራሲ እውን እንዲሆን፣ አስተማማኝ ሰላም እና መረጋጋት እንዲሰፍን የተጫዎቱት ሚና ከፍተኛ ከመሆኑም ባለፈ በሀገራችን ዘላቂ ሰላም፤ ልማት፣ ዴሞክራሲ እና እውነተኛ ፌዴራላዊ ስርዓት እንዲረጋገጥ ሲሉ ባካሄዱት መራራ ትግል እና በከፈሉት መስዋዕትነት በፖለቲካ ረገድ በሀገራችን እኩልነት፣ ፍትህ፣ አንድነት፣ ሰላም እና እውነተኛ ፌዴራላዊ ስርዓት ጭላንጭል እንዲታይ ጉልህ ሚና ተጫውተዋል፡፡

ይህም ሆኖ ከአራት አመታት ወዲህ በሀገራችን በታሪክ አጋጣሚ በህዝባዊ ድጋፍና በወጣቶች መራር ትግል ስልጠኑን በእጁ የተቆጣጠረው መንግስት ከሚያደርሰው ጫና የተነሳ በመላ ሀገርቱ የሚገኙ ወጣቶች በተለያዩ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ሀሳባቸውን በነጻነት በማራመድ፣ የራሳቸውን የፖለቲካ፣ የማህበራዊ እና የኢኮኖሚያዊ ተሳትፏቸውን እና ተጠቃሚነታቸውን በታሰበው ልክ ለማረጋገጥ እጅግ አዳጋች ሆኗል፡፡

ዛሬም በፖለቲካና በአመለካከት ልዩነቶች የተነሳ በወጣቶች ላይ በየአከባቢው እየደረሰ ያለውን እስርና እንግልት በማስቆም ትላንት በትግላችን ያረጋገጥናቸውን ድሎችን ዛሬም አስጠብቀን፣ ለነገ ለተሻለ ድል ጠንክረን እንድንሰራ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎችና መላው የኢትዮጵያ ወጣቶች የወጣቶች ክንፍ በማቋቋም ሙሉ ተስፋ ሰንቀዋል።

ይህንን ታሪክ እና መላ የኢትዮጵያ ወጣቶች የጣሉብንን ከፍተኛ ኃላፊነት ለመወጣት በሀገር አቀፍ ሆነ በክልል ደረጃ በወጣቶች ላይ የሚደርስን ጫና በማስቀረት ወጣቶች በአንድነት እና በትብብር ለመስራት የሚያስችላቸውን የፖለቲካ ባህል ለመፍጠር ሰፊ እንቅስቃሴ ስናደርግ ቆይተናል።

በዚህ መሠረት እንደ የወጣቶች ክንፍ የሀገራችን ወጣቶችን የፖለቲካ ተሳትፎ ሁኔታን መነሻ በማድረግ ከነባራዊ ሁኔታ የሚመነጩ የወጣቶች ችግሮችን በውል በመገንዘብ ባሉበት አካባቢ ወጣቶች በፖለቲካው ዘርፍ ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ልዩ ትኩረት በመስጠት ወጣቶችን በምክንያት መድረኮች የበለጠ ለሀገራቸው እንዲጠቅሙ ለማስቻል ተግተን እየሰራን እንገኛለን፡፡

በአፋር ክልል በፖለቲካ ልዩነቶች ምክንያት ወጣቶች በእስር ላይ እንደሚገኙ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፖርቲዎች የወጣቶች ክንፍ መረጃው ደርሶታል። ወጣቶች በፖለቲካው ዘርፍ የሚያደርጉት ንቁ ተሳትፎ በዲሞክራሲ ግንባታ ሂደት ውስጥ ወሳኝ ሚና አለው። የወጣቶችን የፖለቲካ እንቅስቃሴ መገደብ ለሀገራችን የማይጠቅም ኢ-ዲሞክራሲያዊ አካሄድ በመሆኑ ወጣቶች በፖለቲካ ሀሳብ ልዩነቶች ምክንያት ለእስርና እንግልት መዳረግ የለባቸውም።

በመሆኑም የሚመለከታቸው አካላት የወጣቶችን ይህንን የወጣቶች ችግር እልባት በመስጠት ረገድ ትኩረት ሰጥቶ መስራት አለባቸው።

በተጨማሪ በፖለቲካ አስተሳሰብ ልዩነቶች አለአግባብ የታሰሩ ወጣቶች ካሉ ስም ዝርዝር እና አድራሻቸውን በመጥቀስ ለኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የወጣቶች ክንፍ በ #Inbox ማመልከት ወይም ጥቆማ መስጠት ትችላላችሁ።

የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የወጣቶች ክንፍ
የካቲት 7፣ 2015 ዓ.ም
አዲስ አበባ
364 viewsHusen Mohammed, 22:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-11 23:25:41
በሃይማኖት ካባ መፈንቅለ መንግስት አቅደው የነበሩት ገቢ እየሆኑ ነው ቹቻ ወጥር
290 viewsHusen Mohammed, 20:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-11 23:25:01 ትኩስ መረጃ ከዚህ ቦሀለ በየስአቱ እናቀርባለን
289 viewsHusen Mohammed, 20:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-11 23:24:37
ለእሁድ ከተዘጋጀ 500,000 ጧፍ ጋር ነው የተያዘው አሉ
500,000 ጧፍ * በ20 ብር ስትመታ ስንት ይሆናል..... ሒሳብ ስራ....
287 viewsHusen Mohammed, 20:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-11 18:59:23
መምህር ምህረተ አብ አሰፋ የኦርቶዶክስ አማኞችን ስሜት እየኮረኮረ በየአቅጣጫው ጠላት ሲያበዛላቸው ነበር። በበርካታ ግጭት ቀስቃሽ ሃሳቦቹና ጽንፈኝነቱ ይታወቃል።

ዛሬ ለእስር ቤት መዳረጉን ሰምተናል። እርሱ መታሰር ያለበት ዛሬ ሳይሆን ያኔ ነበር።

የግለሰቡ ጠርዘኛ ሃሳቦች እንኳን ለሌላው እምነት ተከታይ ለራሳቸው ለኦርቶዶክሶች የማይጠቅም ነው። የእንዲህ አይነት ሰዎች መታሰር ለሃገር ሰላም ጉልህ ሚና አለው። መልካም ረፍት!
315 viewsHusen Mohammed, 15:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-08 18:45:15
676 viewsHusen Mohammed, 15:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-08 18:45:09 == የእንታረምና የእንለወጥ ጥያቄዎች*** ==

የንጉሠ ነገሥቱ ዙፋን ላይ በግርማሜ ወንድማማቾች ተሞክሮ የነበረው መፈንቅለ መንግሥት በከሸፈ በጥቂት ቀናት ወስጥ ንጉሡን በአካል ሊያገኝ አንድ ሰው ከኒውዮርክ ተሳፍሮ አዲስ አበባ ገባ። ግለሰቡ ደራሲና አምባሳደር ሀዲስ አለማየሁ ነበሩ። አምባሳደር ሀዲስ አለማየሁ በወቅቱ በኒውዮርክ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ውስጥ የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ ሆነው ነበር የሚያገለግሉት። የደብረ-ማርቆስ ተወላጁ ሀዲስ ሚኒሊክ ቤተ-መንግሥት ውስጥ ገብተው ከንጉሡ ዙፋን ቀረቡ። ከወገባቸው አጎንብሰው እጅ ከነሱም በኋላ፤ «እንኳን ግርማዊነትዎን እና ዙፋንዎን እግዚአብሔር አዳነ» በማለት ንጉሡ ከሥዒረ መንግሥቱ መዳናቸው ደስ እንዳሰኛቸው ገለጡ።

ነገር ግን ሀዲስ ቤተ-መንግሥት የሄዱት ለዚህ ብቻ አልነበረም። ከዚያ ይልቅ ሀገሪቱ በተያያዘችው ኋላ-ቀር የአሥተዳደር ሥርዓት ከቀን ወደ ቀን ወደ ከፋ ቀውስ እያዘቀዘቀች መሆኗ ታይቷቸው አዲስ የሥርዓት ማሻሻያ ለውጥ [ሪፎርም]በግዛተ-አጼው ውስጥ እንዲካሄድ የሚጠይቅ ማስታወሻ አዘጋጅተው ለንጉሡ በእጃቸው ለመስጠት ነበር። ንጉሡ የተሰጣቸውን ማስታወሻ ገለጥ ገለጥ አድርገው ማንበብ ጀመሩ።

የማስታወሻው መግቢያ ለንጉሡ ውዳሴ የሚያዥጎደጉድ ነበር፣ ንጉሡ ማስታወሻው ላይ አይናቸው ባቀረቀረበት በድንገት በብስጭት ቱግ አሉ። «እኛ ከንቱ ውዳሴ እንወዳለን እንዲህ ብለህ ያቀረብኸው? እኛ እኮ እናውቀሀለን» ብለው በቁጣ ተናገሩ። ደራሲ ሀዲስም ፈራ ተባ እያሉ «እኔም እኮ አውቅዎታለሁ! [ይሄን በማለቴ] ሊያስሩኝ፣ ሊገርፉኝ፣ ሊገድሉኝ እንደሚችሉ አውቃለሁ» ብለው መለሱላቸው።

ይህ የሐሳብ ልውውጥ በንጉሡና በአምባሳደሩ መካከል ሲካሄድ ኢትዮጵያ ከፍተኛ የአሥተዳደር፣ የሙስና፣ የልማት እና የጸጥታ ችግሮችን የተጋረጠችበት ጊዜ ነበር። ንጉሡና አሥተዳደራቸው ደግሞ ችግሮቹን ለመፍታት ብቻም ሳይሆን ለመረዳትም የተሳናቸው ይመስል ነበር።

የንጉሠ ነገሥቱ የሥልጣን ዘመን እያከተመ መኾኑ የታወቀው ቢያንስ ከ1966ቱ ዓብዮት 10 እና 15 ዓመታት በፊት ነበረ። ግዛተ-አጼው በተለያዩ ወቅቶች ይነሱበት የነበረው የከተማና የገጠር አመጾች ሕዝቡ በሥርዓቱ ላይ የነበረው ተስፋ እየተንጠፋጠፈ መሄዱን እያመላከቱ ነበር። የንጉሡና አሥተዳደራቸው እያደረ ከመሻሻል ይልቅ እየተበላሸና እየቆረቆዘ የሚሄድ አካሄድ ያልጣማቸው አምባሳደር ሀዲስ ሀገሪቱ የገጠሟትን ችግሮች በፈርጅ በፈርጅ በመለየት ሊወሰድ ይገባል ያሉትን መፍትሄ ነበር በማስታወሻቸው ያስቀመጡት።

ይህ ለሥርዓቱ ቅርብና ቤተኛ የሆነ ሰው ያቀረበው የ«እንሻሻል» ማስታወሻ በንጉሡም ሆነ ባለሟሎቹ ይህ ነው የሚባል ግምት ሳይሰጠው ቅርጫት ውስጥ ተጣለ። በንጉሡ አሥተዳደር ውስጥ ኾነው ግዛተ-አጼው እንዲሻሻልና ከእንከኖቹ እንዲታረም ሐሳብና ማስታወሻ ያቀረቡት አምባሳደር ሀዲስ ብቻ አልነበሩም። ንጉሡን ከ1953ቱ መፈንቅለ መንግሥት የታደጓቸው ጀነራል መርእድ (የወቅቱ መከላከያ ሚኒስትር)፣ ልዑል ራስ አስራተ ካሳን ጨምሮ አምባሳደር ብርሃኑ ድንቄ፣ ጀነራል አብይ አበበ ወዘተ አሥተዳደራቸው እንዲሻሻል የሚጠይቅ ይፋዊ ማስታወሻ ለንጉሡ አቅርበዋል።

የእነዚህ ግለሰቦች ጥያቄዎች በቅንነት የተሞሉና ከጀርባቸው የተለየ ዓለማ የነበራቸው አልነበሩም። የሁሉም ማስታወሻዎች ጭብጥ የንጉሡ አሥተዳደር ሕገ-መንግሥቱን ከመለወጥ ጀምሮ ግዛተ-አጼው ዘመኑን፣ የኅብረተሰቡን ንቃተ ሕሊና፣ ፍላጎትና አሁናዊ ሁኔታዎችን ያገናዘበ ለውጥ እንዲያመጣ የሚጠይቁ ነበሩ። የእነዚህን ሁሉ ሰዎች ውትወታ ጆሮ ዳባ ልበስ ያሉት ንጉሡ በ1966 በተነሳ አብዮት ንግሥናቸውንና ለዘመናት ይዘውት የቆዩትን የጥቅም ሞኖፖሊ ከእነቤተሰባቸው አጡ። አሳቸወም ያ ሁሉ ክብርና ሞገስ ተቀምተው በመፀዳጃ ቤት ጉድጓድ ውስጥ ተቀበሩ።

የንጉሡ ታሪክ ለማሳያነት ቀረበ አንጂ የብዙ መንግሥታትና ተቋማት ታሪክ ተመሳሳይ ነው። ዘመንና ጊዜ እየተቀየረ ሲሄድ የኅብረተሰብ አኗኗር፣ ፍላጎት፣ የመብት ጥያቄ ወዘተ አብሮ እየተለወጠ ይሄዳል። ሕዝብ አይናቅም። ሕዝብ የአሥተዳደርም ሆነ የአካታችነት ጥያቄ ሲያነሳ ወደ ጎን መግፋት መዘዙ ብዙ ነው። የንጉሡ መንግሥት ተሰባበሮ የወደቀው ራሳቸው ንጉሡና አሥተዳደራቸው «ኃላፊነትን ለመቀበል አልደረሰም» ባሉት ሕዝብ ነበር። ሕዝብ ማድመጥ አይጎዳም!

*** የአብዮቱን ወር ወርሃ የካቲትን አስመልከቶ የሰፈረ ማስታወሻ
633 viewsHusen Mohammed, 15:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ