2022-11-05 17:00:11
ዶሮ አሳማ እና ተጋሩ ዲያስፖራዎች
ዶሮ ናት አሉ፣ ጓደኛዋን አሳማን እንዲህ ትላታለች፡
"ለምን ምግብ ቤት አንከፍትም? እኔ ለምግብ ቤቱ እንቁላል እየጣልኩ አቀርባለሁ ፡ አንቺ ደግሞ ስጋ አቅርቢ እና የእንቁላል ሳንድዊች እና ሞርቶዴላ እየሰራን እየሸጥን ለምን ሀብታም አንሆንም?"
አሳማዋም ለዶሮዋ እንዲህ ብላ መለሰችላት:–
" አየሽ ላንቺ እንቁላል መጣል ተሳትፎ ነው ለእኔ ግን ስጋ ማቅረብ መስዋትነት ነው"
ምን ለማለት ነው?
እነ አሉላ፣ አብረሃ ደስታ፣ ቴዲ ርዮት፣ ስታሊን እና የመሳሰሉት ዳያስፖራ ተጋሩ ከሙቀቱና እሳቱ ተጠብቀው ለህዝባችን በመንከባለል እና በዩቱብ ፕሮፓጋንዳ "ተሳትፎ" እናደርጋለን እያሉ የትግራይ ወጣቶች እና እናቶች "መስዋእት" እንዲሆኑላቸው የሰላም ስምምነቱን አንቀበልም እያሉ ነው።
ያሳዝናል።
አሁን የታጠቀው ወጣት አስተማሪ፣ ኢንጂነር፣ ተማሪ፣ ፖሊስ፣ ሀኪም፣ ነጋዴ የመሳሰሉት የትግራይ ልጆች ናቸው። ቲዲኤፍ ትጥቅ ይፍታ ማለት እነዚህ ዜጎች ወደ መደበኛ ህይወታቸው ይመለሱ ማለት ነው። ልክ ዲያስፖራ ተጋሩ እየሰሩ በሰላም እንደሚኖሩት በሰላም ህይወታቸውን ይምሩ ነው የተስማሙት።
ይህ ስምምነትን ትህነግ ሲፈርም ትግራይ ውስጥ መሬት ላይ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ ስለሚያውቁ ነው። ነሀሴ ላይ በአስር ግንባር የተጀመረው ሶስተኛ ዙር ውጊያ አልቀናቸውም። ተተኳሽ የለም። ነዳጅ የለም። ሎጂስቲክ የለም። የትህነግ ጦር ተቆራርጦ በየ ፖኬቱ ቀርቷል። አመራሩ ወደ ቆላ ተንቤን መሄጃው ተዘግቶበታል። ፈረንጆችም የትህነግ ነገር ሰልችቷቸዋል።
መሬት ላይ ያለው እውነታን የተመለከተው ትህነግ ሰላም እንደሚያዋጣ ተረድቶ ነው ስምምነቱን የፈረመው። ዳያስፖራው ግን እኔ በድምፄ ተሳትፎ ላድርግ እናንተ በጥይት አረር እየተቆላችሁ አብረን እንታገል ይላሉ።
ማፈሪያዎች
324 viewsHusen Mohammed, 14:00