2022-08-05 20:33:16
ሳውዲ ላይ ...
ወጣቱ ኢትዮጵያዊ አንገቱን በሰይፍ ሊቀላ ነው
===================================
* " የግድያ ወንጄል አልፈጸምኩም "
* " ወገንና መንግስት ድረሱልኝ " ብሏል
ታዳጊው አለሙ መኮንን
* ልክ ከዛሬ ሶስት አመት በፊት ሳውዲ ጅዳ የገባው ታዳጊ አለሙ መኮንን ተሾመ ምንም በማያውቀው ጉዳይ ሰው ገድለሃል በሚል ወንጄል አንገቱ እንዲቀላ በሳውዲ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ውሳኔ ተላልፎበታል።
ከሰአታት በፊት ከታሰረበት ወህኒ ሆኖ " ምንም አይነት የግድያ ወንጄል ሳልፈጸም ፣ አሸራም ሆነ ሲገድል አየሁ የሚል ምስክር ሳይመሰከርብኝ ገድሏል ተብዬ አንገቴ በሰይፍ እንዲቀላ ፍርድ ተላልፎብኛል። ወገኖቸና መንግስት ይድረሱልኝ " ሲል ያደረሰኝ መልዕክት ያስረዳል ።
የወጣት አሙ መኮንንን ሙሉ መልዕክት በቀጣይ ቀናት የማቀርበው ይሆናል ።
ፈጣሪ ይድረስልህ
ነቢዩ ሲራክ
ሐምሌ 29 ቀን 2014 ዓም
Share ሼር ምናልባትም ስበብ ቢንሆን መንግሥት በአስቸኳይ ልዩ ቡዱን ይላክ
154 viewsHusen Mohammed, 17:33