2022-05-20 16:39:02
“ሩሲያ ዶንባስን ወደ ሲኦል ለውጣታለች”
የዩክሬንፕሬዚዳንት ዘለንስኪ
ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዜሌንስኪ ሩሲያ የዩክሬኗን ዶንባስ ክልል ወደ ሲኦል ቀይራታለች አሉ፡፡
ዜሌንስኪ ሞስኮ ምስራቃዊ ዶንባስ ክልልን ወደ ሲኦል ለውጣታለች ሲሉ ክስ ያቀርባሉ፡፡
ፕሬዚዳንቱ በኪዬቭ በነበራቸው ንግግር በኦዴሳ ክልል እንዲሁም በማዕከላዊ ዩክሬን ከተሞች ጥቃቶች ያለማቋረጥ መቀጠላቸውን አጽንኦት ሰጥተውበታል ፡፡
ዶንባስ የተሰኘው ክልል ሙሉ ለሙሉ ወድሟል ፡፡
ፕሬዚዳንቱ እንደሚሉት የክሪሚሊን ፖለቲከኞች ለዚህ ሁሉ ጥፋት ምንም ዓይነት ወታደራዊ ማብራሪያ የላቸውም፡፡
ሩሲያ አቅዳ ያደረገችው እና በተቻላት መጠን ዩክሬናውያንን ለማጥፋት የተነሳሳችበት ጦርነት ነው በሚልተደጋጋሚ ትችቶች ይሰነዘራሉ፡፡
ሐሙስ የዩክሬን የመከላከያ ሚንስቴር ሞስኮ በዶንባስ ጥቃቷን አጠናክራ ቀጥላለች ፤ንፁኃን ዜጎችም ከአካባቢው እንዳይወጡ ከልክላለች በሚል ወንጅሏታል፡፡ ሮይተርስ
5.6K views13:39