2022-05-23 17:52:08
የጦር ሜዳ ጀብጁ !!!
«ማን ይናገር የነበረ… ማን ያርዳ የቀበረ!»
ብርጋደል ጀኔራል #ሻንበል_በየነን ማን ከጦር ግንባር አውጥቶ ኮምቦልቻ ወሰደው ማን ነበር?… ያልተሰማው የአፋሩ የአንቡላንስ ሹፌር #ናስር_አህመድ_ሰይድ የጦር ሜዳ ጀብዱ…
«ጀኔራሉ እንደቆሰሉ ተነግሮኝ በእኔ አንቡላስ ተጫኑ… የተሰጠኝ ኃላፊነት ትልቅ መሆኑን ሳውቅ እርሳቸውን ይዥ ወደ ኮምቦልቻ ተፍጥነት ተጓዝኩ… ኮምቦልቻም ደርሸ ለሀኪሞቹ ስሙን ሳልናገር ብቻ ከፍተኛ አመራር መሆናቸውን ተናግሬ ነፍሳቸውን እንድታደጉ ነገርኳቸው… ወዳው ሄሌኮፍተር መጥታ ወደ አዲስ አበባ ወሰደቻቸው።»
ቀኑ ጷጉሜ4 ቀን2013ዓ/ም ሐሙስ ቀን ከጦቱ ሶስት ሰአት ገደማ ነው፤ ጥላትን ሓማሮ ተራራ ቆርጦ ለመውጋት በአፋር እዋ በኩል እየመታ እያለ ከተሟሟቀው ውጊያ ላይ ነበር ፊቱ አካባቢ ተመትቶ የወጣው። ወደ ጭፍራ ሆስፒታል ደርሶ የህክምና እርዳታ ከተደረገለት በኋላ፤ ናስር ለሪፈር ይዞ ወደ ኮምቦልቻ ሆስፒታል የደረሰው ከቀኑ9፡00 ሰአት ነበር።
ናስርም እኔም ለሚዲያ እስኪዎጣ ይፋ አላደረግነውም ነበር። በዚህ አጋጣሚ ክብር! እንደ እናት እየተርገበገቡ በጦር መካከል ገብተው ህይወት ለሚታደጉ የአንቡላንስ ሾፌሮች ይሁን!!!
ናስሬ! ምርጥ ጀግናዬ ነህ በርታልኝ!!!
ክብር ለክብራቸው ለተዋደቁት ሁሉ!!!
ቴዎድሮስ አያሌው (ሀብታሙ)
ወልዲያ
t.me//alzarkawihabib
5.1K views14:52