Get Mystery Box with random crypto!

አል ሂዳያ የየቲሞች መርጃና በጎ አድራጎት ጀማአ 0993632424//0703136300አዲስ አበባ

የቴሌግራም ቻናል አርማ alhidayatv — አል ሂዳያ የየቲሞች መርጃና በጎ አድራጎት ጀማአ 0993632424//0703136300አዲስ አበባ
የቴሌግራም ቻናል አርማ alhidayatv — አል ሂዳያ የየቲሞች መርጃና በጎ አድራጎት ጀማአ 0993632424//0703136300አዲስ አበባ
የሰርጥ አድራሻ: @alhidayatv
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 15.07K
የሰርጥ መግለጫ

ኑ ተባብረን ባለን አቅም የቲሞችንና የተቸገሩ ሙስሊም ወገኖቻችንን እንርዳ
በልብስ👕👖 በገዘብ በአስዜዛ በጉልበት በሀሳብና
በተለያዩ በቤት ቁሳቁሶች መርዳት ትችላላቹ
ንግድ ባንክ
1000375043298
ሪድዋን ሙሀመድ
አባል መሆን ለምትፈልጉ
ለበለጠ መረጃ
251993632424
ወይም የቢሮ ቁጥር
251703136300
ወይም በኢቦክስ
@RidAmirsab
ሰደቃ ወጀልን ታብሳለች ረሱል (ﷺ)

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2022-12-23 17:51:17
92 viewsإذلم تتعلم التو حيد والعقيدت الصحيحت ستخيفك البو مت ويغير مزاجك, 14:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-21 22:03:45
«"ቶሎ ትቆጣለህ!" ይሉሀል።
የተጠራቀመው ድርጊታቸው ውጤት መሆኑን ግን አያውቁትም...።»
https://t.me/ALHIDAYATMIDIA
627 viewsإذلم تتعلم التو حيد والعقيدت الصحيحت ستخيفك البو مت ويغير مزاجك, 19:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-21 13:05:45
አሰላሙአለይኩም ወራህመቱሏሂ ወበረከትሁ

ዛሬ አንዲት እህታችን የቁርአን እጥረት ላለባቸዉ መስጂዶች ቁርአን እያሰባሰብን እንደሆነ ስትሰማ ተሎ ብላ ነበረ 30 ፍሬ ቁርአን ገዝታ የሰጠችን እህታችን ዱአ አድርጉልኝ ብላለች ልጄ ታማብኛለችና ዱአ አድርጉልኝ ብላለች ሁላቹሁም በዱአ እንተባበራት

ወላሂ ሚገርመኝ ነገር ለኸይርስራ በቃ ሴቶች ብቻ ናቸዉ እየተነሳሱ ያሉት ወንዶች ግን ምን ሁናቹ ነዉ አረ ሰነፋቹ ነቃ በሉጂ

ለማንኛዉም የቁርአንና የኑራንያ እጥረት ላለባቸዉ መስጂድና መድረሳዎች ዉስጥ የተወሰኑትን ሰተን ጨርሰናል እና የመድረሳ ልጆች አሁን ሂደን ባረጋግጥነዉ መሰረት ካለ ምንም ቁርአንና ኑራንያ እጥረት በሰላም እየቀሩና በቁርአን እጥረት ምክኒያትም ከመድረሳዉ ሳይመጡ የቀሩ ልጆችም ወደ መድረሳዉ እየተመለሱና ቁርአናቸዉን እየቀሩ መሆኑን ሂደን አረጋግጠናል ለዚ ኸይር ስራ ለተባበራቹሁን እህት ወንድሞች ጀዛቹሁን አሏህ ይክፈላቹ

አሁንም የቀሩ መስጂዶች መድረሳዎች አሉና በተቻለን መጠን ይህንን የአሏህ ቃል የሆነዉን ቅዱስ ቁርአንን ለነዚ መስጆችና መድረሳዎች ስጦታ እናበርክት ነይቱልን

ኑ ተባብረን ባለን አቅም የቲሞችንና የተቸገሩ ሙስሊም ወገኖቻችንን እንርዳ
በልብስ በገዘብ በአስዜዛ በጉልበት በሀሳብና
በተለያዩ በቤት ቁሳቁሶች
እና የተለያዩ ኢስላማዊ መፀሀፎች ቁርአን ኑራንያና በተለያዩ ነገሮች መርዳት ትችላላቹህ

አባል መሆን ለምትፈልጉ
ለበለጠ መረጃ
0993632424
ወይም የቢሮ ቁጥር
+251703136300
ወይም በኢቦክስ
@RidAmirsab

ሰደቃ ወጀልን ታብሳለች ረሱል (ﷺ)
https://t.me/ALHidayaTv/19946
294 viewsإذلم تتعلم التو حيد والعقيدت الصحيحت ستخيفك البو مت ويغير مزاجك, edited  10:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-16 06:53:57 ➴የውሙል_ጁመዓ➴!
  ____
እናንተ ያመናችሁ ሆይ በአርብ ቀን ወደ ስግደት  በተጠራ ግዜ አላህን ወደ ማውሣት ሂዱ  መሸጥንም ተው ይህ የምታውቁ ከሆነ ለናንተ በላጭ ነው።

ቁርአን 《ሡረቱል ፦ አል ጁሙአህ》
በላጭ ቀናቹ የጁመዐ ቀን ነው
  ረሡል ሠለላሁ አለይሒ ወሠለም
"ፀሀይ ከወጣችባቸው ቀናቶች ሁሉ በላጩ ቀን የጁመዐ ቀን ነው
ረሡል ሠለላሁ አለይሒ ወሠለም

ከላይ ያለፋት መለኮታዊ ንግግሮች በአጠቃላ ኢስላም ከሌሎች ቀናቶች ለይቶ  ለጁመአ ለት  የሠጠውን ደረጃ ያሣዩናል ይህን የተከበረ ቀን በምን መልኩ ማሣለፍ እንዳለብን ከነብዩ ሠለላሁ አለይሒ ወሠለም ዘንድ የመጡት በማውሣት እንተዋወስ
ወደ መልካም ነገር ያመላከተ    እንደሠራው ነው" ይባል የለ ።

የጁመአ ለት ሡብሒ ሠላት ያለው ደረጃ ,አላህ ዘንድ በላጩ ሠላት የጁመአ ቀን ሡብሒ በጀመአ መስገድ ነው።
   
        [ሢልሢለቱ ሰሒህ]

ጁመአ ለት ሡብሒ ሠላት ላይ
    ምንምን ሡራ ይቀሩ ነበር ?
 
የአላህ መልዕክተኛ ሠለላሁ አለይሒ ወሠለምበጁመአ ሡብሒ ላይ
  [አሊፍ ላም ሚም ተንዚሉ: ሠጅዳ]
እና   「ሀል አታ አለል ኢንሣኒ」
              ይቀሩ ነበር
           [ቡሀርና ሙስሊም]

በጁመአ ቀን ሠለዋት ማውረድ
     ያለው ጥቅም

የጁመአ ቀን እና ማታ በኔ ላይ
  ሠለዋትን አብዙ,በይሀቅይ
በላጭ ቀናቹ የጁመአ ቀን ነው የዛ ቀን:     "አደም ተፈጠረ "ሞተ "ጡሩንባ ይነፋል "በህይወት ያለ ሁሉ ይሞታል በኔ ላይ ሠለዋትን አብዙ ሠለዋታቹ በኔ ላይ    የምትቀረብ ናት "
   አስሀቡ ሡነንነወውይ
       ሰሒህ ብለውታል

የጁመዓ ቀን ገላን መታጠብ
#አንደኛቹ ወደ መስጂድ ሢመጣ ገላውን
ይታጠብ ,
     [ ቡሀርና ሙስሊም ]

የጁመአ ቀን ሽቶ መቀባት ፣ ጥሩውን መልበስ ፣ረጋ ብሎ ሣይጣደፍ
ወደ መስጂድ መሔድ በሁጥባ ወቅት ዝም ብሎ ማዳመጥ  ያለው ጥቅም ~የጂመአ ቀን የታጠበ, ሽቶ ካለውና ከተቀባ ,ጥሩ ልብስ የለበሰ , ወደ መስጂድ ሢሔድ በተረጋጋ መንፈስ ከሔደ ,ከተመቸውና ከሠገደ ,አንድንም ሠው ካላስቸገረ , ኢማሙ ሚንበር ላይ  ከወጣበት እስኪሠገድ ድረስ ዝም ያለ  በሁለት ጁመአዎች መሀል ያለውን ወንጀል ይማርለታል

በግዜ መስጂድ መሔድ,የጁመአ ቀን መላይካዎች የመስጂድ በር ላይ ይቆማሉ ከዛ መጀመርያ ቀድሞ የሚገባውን ይፅፋሉ : መጀመርያ መስጊድ የሚገባው ግመል እንደሠጠ ከሱ ቀጥሎ ከብት ከሡ ቀጥሎ በግ ከዛም ዶሮ ከዛም እንቁላል ኢማሙ ሚንበር ላይ ሢወጣ መዝገቡን ዘግተው ሊያዳምጡ ይገባሉ  "
       [ቡኸርና ሙስሊም ]

የጁመአ ቀን የተከለከሉ ነገሮች

ኢማሙ ሁጥባ ሢያደርግ ማንኛውም አይነት ንግግር ክልክል ነው በመልካም ማዘዝም ከመጥፎ መከልከልም  ቢሆን  "ለጎደኛህ የጁመአ ቀን ኢማሙ ሁጥባ እያደረገ ዝም በል ካልከው ውድቅ የሆነ ነገር ሠርተሀል "ቡሀርና ሙስሊም አህመድ "ውድቅን ነገር የሠራ ከጁመአው ምንም ነገር የለውም "
   የሚል ጨምረው ዘግበዋል

ዘግይቶ መስጂድ መምጣት እና ሠዎች አዛ ማድረግ "ረሡል ሠለላሁ አለይሒ ወሠለም ሁጥባ እያደረጉ አንድ ሠው በሠዎች ጀርባ ላይ እየተረማመደ ሢመጣ "ተቀመጥ! ሠዎችን አስቸገርክ" አሉትኝ

አላህ የተጠየቀውን ነገር የሚመልስባት አንድ ወቅት አለች
#በጁአ ለት አንድ ሠአት አለች እሧን ሠአት አንድ ሙስሊም የሆነ ባርያ አያገኛትም  እሡ የሚሠግድ ሢሆን አላህን አንዳች ነገር አይጠይቀውም
የሠጠው ቢሆን እንጂ
[ ቡኻር እና ሙስሊም ]

ያቺ ሠአት መቼ ናት?
በዚህ ዙርያ ኡለሞች የተለያየ አመለካከት ሠንዝረዋል ከሙስሊም በተዘገበ ሀዲስ ኢማሙ ሁጥባ ከጨረሰበት ሠላት እስኪሰገድ ያለው ክፍተት ነው "አቡ ዳውድ እን ነስእይ በዚህ መልኩ ዘግበዋል

ከጁመአ የመጨረሻው ወቅት ላይ ፈልጓት "በሌላ ዘገባ "ከአስር ቡሀላ
والله اعلم وصلى الله على نبينا محمد وعلى آله وأصحابه وسلم.
╭┅━━• ⚘ •━━━┅╮
https://t.me/mame0999
https://t.me/mame0999
╰┅━━• ⚘ •━━━┅╯
180 viewsSELADIN BASET, 03:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-14 22:47:37
የአል ሂዳያ የየቲሞች መርጃና በጎ አድራጎት ጀማአና

አል ሂዳያ ሙስሊም ጀማአ እግር ኳስ ክለብ ባዲራ
341 viewsإذلم تتعلم التو حيد والعقيدت الصحيحت ستخيفك البو مت ويغير مزاجك, 19:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-13 19:50:47 «የቲምን አደራ»

የቲምን አደራ አሉን የኛ አወራ፣
ስለዚህም ጉዳይ በጥቂቱ እናውራ፣

አባት የሞተበት ገና በልጅነት፣
እናቲቱም ብትሆን አቅሟ የከዳት፣

እጅግ ተቸገሩ ማንም በሌለበት፣
በጣሙን ተራቡ የለም ሚጠይቁት፣

በቀን አንድ ግዜ እሱንም ካገኙት፣
አንድ ልጅ ነበረ አባት የሞተበት፣

ከእናቱ የሚኖር እሷ አቅም የሌላት፣
ነበር በረመዳን በተራዊህ ሰአት፣

እናቱን ጠራና እንደዚህም አላት፣
ሰዎች ተመለሱ ከተራዊህ ሰላት፣

እኛ ሳናፈጥር ይሄሁሉ ሰአት፣
እናቱ ምን ትበል ምን ጉድጓድ ይዋጣት፣

ለነፍስያ ሳይሆን ለልጇ አሳስቧት፣
ሚበላም ሚጠጣ ምንም ቁራሽ የላት፣

የዚ አይነትም አለ እይ አንተ ባለሀብት፣
አንተ የምትበላው በቀን 9አይነት፣

ሌላው ይሰቃያል ቁራሽ ዳቦ ጠፍቶት፣
የቲምን በመርዳት አኼራን ገንባበት፣

ነቢ ተናገሩ በዛ ውድ አንደበት፣
የቲምን የረዳ ከሀተይን ያሉት፣

ካልቻልክም በእጅህ ፀጉሩን እሽለት፣
የነብዩን ትዛዝ ምትተገብርበት፣

ሀብትህንም ቢሆን በረካ ሚያደርጋት፣
ለቸገረው የቲም እጅን በመዘርጋት፣

የአኼራ ቤትን የምታድስበት፣
አላህ ይመድበን የቲም ከሚረዱት።



'' መልካም ተግባራት ምንንም አሳንሰህ አተመልከት
ወንድምህን በብሩ ፈገግታ መገናኘት አንኳ ''
ነቢዩ (ሶ,ዐ,ወ)

https://t.me/ALHidayaTv/19942
595 viewspraise be to allah, edited  16:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-11 22:47:33 የኢስላምን ውላታ ለበላሿ እህቴ!!!
~~~~
ኢስላም ለሴት ልጅ እጅግ በጣም ዘርፈ-ብዙ ውለታዎችን ውሏል።ከዋላቸው ውለታዎች ትልቁና ዋነው በህይወት የመኖር መብቷን ማረጋጋጡ ነው።እንደሚታወቀው ነብዩ ( ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ከመላካቸው በፊት(በጃሂሊያ ስርዓት) ሴት ልጅ እስከነ ነፍሷ ትቀበር ነበር።ኢንሳሳት ላይ እንኳን የማይወሰድ አሰቃቂ እርምጃ ነበር የሚወሰድባት።ይህንን እርኩስ ስርዓት ለዓለም ብርሃን የሆኑት ነብዩና ሙሐመድ(ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ከተላኩ በኋላ ነበር ከስር መሰረቱ ገርስሰው ሴት ልጅ ከጌታዋ የተሰጣት ህይወት በነፃነት እንድትኖር ያደረጉት።
ዛሬ ግን በጣም በሚያሳዝን ሁኔታ ሴት እህታችን ነብዩ ይዘውላት የመጡትን መንገድና ስርዓት በመጣስ ለምርኣባውያን ፋሽንና ሰይጣናዊ መንገድ አጎብድዳ የነርሱን መንገድ ኮቴ በኮቴ እስከመከተል ደርሳለች።ይህ ደግሞ ነብዩ ሰለላሁ ዓለይሒ ወሰለም ከዛሬ አንድ ሺ አራት መቶ አመት በፊት የተናገሩት ነው።("ለተተቢዑነ ሰነነ ሚን ቀብሊኩም ሐዝወል ቁዛ ቢል ቁዛ ሀታ ለው ደኸሉ ጁህረ ዷቢን ለደኽልቱሙህ")ከናንተ በፊት የነበሩትን መንገድ ትከተላላችሁ ኮቴ በኮቴ። የወከሎ(አርጃኖ)ጉድጓድ ቢገቡ እንኳን ተከትላቹሃቸው ትገባለችሁ አሉ። ሶሃቦችም ጠየቁ፦"አል የሁዱ ወናሷራ ያረሱለላህ?" የሁዶችንና ነሷራዎችን ማለታችሁ ነው እንዴ የአላህ መልክተኛ? አሏቸው ነብዩም "ፈመን" ታዲያ ማንነው? አሉ። ልብ በይ እህቴ ነብዩ ይህንን ሀዲስ የተናገሩት ከስሜታቸው አይደለም።አላህ ወደፊት ህዝባቸው ላይ የሚከሰተው ስላሳወቀቸው ነው።ክስተቱን ይሀው ባለነበት ዘመን በተጨባጭ አየነው።

ልብ በይ እህቴ ድሮ በጃሒሊያ ዘመን ሴት ልጅ በግፍ ምንም በማታውቀው አፈር ውስጥ ነበር የምትቀበረው።ዛሬ ግን ምእራባውያን ባመጡልሽ ጦስ በበጎ ፈቃድሽ ጀሓነም ኢሳት ውስጥ እየቀበሩሽ ነው።ነብዩ ያመጡልሽን መከበሪያና ነፃነት ልክ እንደ አፈና ጭቆናና የሴትነት መብት ረገጣ አድርገው ባሳዩሽ የሰው አውሬዎች በምእራባውያን ተጠልፈሽ የዘለዓለም ፀፀት ውስጥ እየጣሉሽ ነው።
ከአለባባስሽ ጀምሮ ያለሽበትን ሁኔ በደንብ ካስተወልሽው ተፈጥሮሽና አሁን ያለሽበት ማንነትሽ የሰመይና ምድር ያክል መራራቁን ታገኚዋለሽ።ኢስላም የሴት ልጅ አለባባስ ሙሉ በሙሉ ትሸፈን ሲል እኮ ለራስሽ ከተለያዩ ሊደርሱብሽ ከሚችሉ ፆታዊ ትንኮሳዎች መጠበቂያ እንዲሆንሽ እንጂ አንቺን ለመበደል ወይም የበታች ለማድረግ እንዳልሆነ ጠንቅቀሽ እወቂ።
ዛሬ ግን ምእራባውያን ያሰቡልሽ መስሎሽ "ሴትን ልጅ ከሃይማኖትና ከበህል ተፅዕኖ ነፃ እናውጣት" ብለው ከመጡ የፍልስፍና ቂላቂሎች ወጥመድ ወድቀሽ የአኸራሽ ጉዳይ ምን ሊሆን እንደሚችል ግን ከወዲሁ አስቢበት።ዛሬ የነብዩን ሱና ጥሰሽ የከሃዲዎችን ኮተት ፋሽን እጎተትሽ ለመሆኑ በዚሁ ሁኔታ ጀነት ይታሰባልን? "ከላ" በፍፁም።

ሌላው ቀርቶ ስለ አለባባስሽ ሁኔታሽ በስሱ እንመልከት፦
አላህ ያከበረውን ሰውነትሽን በተከበረው ሒጃብ(ጂልባብና ኒቃብ) ተሸፋፍነሽ የራስሽንም የሙስሊም ወንድምሽን ከአስቀያሚው ዝሙት ታደጊ ብሎሽ ሲያበቃ አንቺ ግን ከካፍሮች በኮረጅሽው ፋሽንን ጋር በመገለባበጥ ከራስሽ ተፈጥሮ ጋር ተኳርፈሻል።አላህ በቁርኣኑ፦"አንተ ነብይ ሆይ ለምስቶችህ ለልጆችህና ለምእመናን ሴቶችም በላቸው ሒጃባቸውን(ጂልባብ ኒቃባቸውን) በራሳቸው ላይ እንዲለቁ እዘዛቸው" ይላል።እንግዲህ "ሙእሚን ሴት መሆን እፈልጋለሁ የነብዩ ተከታይ ነኝ"ብለሽ የምታስቢ ከሆነ አለባበስሽ ምን መምሰል አንዳለበት ከነብዩ ሚስቶችና ልጆች ተርታ አሰልፎሽ በነብዩ አንደበት እየመከረሸ ነው።ረቡና ተባረከ ወተዓላ!!!። በወርቃማው ምክር ቀደምት ሙእሚናት ሴቶች እንደተመከሩበት አንቺም ተመከሪበት።ከልብ ባልመነጨ ውዴታ ዝም ብለሽ "ፍዳካ ያረሱለላህ"እያልሽ ፕሮፋይል ማድመቂያ አትሰሪ።ውዴታሽን ትእዛዛቸውን በመፈፀም በተግባር አሳይ።
እንዲህ ሲባል አንዳንዷ እህት ያምታመጣው አንድ ንግግር አለች "ኢማን በልብ ነው በተከናነበ አይደለም።" ይቺህ እግርና ራስ የሌላት ከመሀል የተቀነጨበች ንግግር ብዙ ስሜት ተከታዮች የሚጠቀሙባት ነጣላ ንግግር ናት።ኢማን በልብ ብቻ ነው ወይስ በውጫው አካልም የሚታይ ነው? አብረን እንመልከት፦
ነብዩ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) እንዳሉት፦"ሰውነታችን ውስጥ አንድ ቁራጭ ስጋ አለች እሷ ስትስተካከል መላው በሰውነታችን ይስተካከላል።እሷ ስትበላሽ መላው ሰውነታችን ይበላሻል።" ተመልከች እህቴ ነብዩ እንዳሉት ቀልቡ የተስተካከለ ውጫዊ አካሉም ይስተካከላል "።እያሉሽ ነው። አንቺ ግን ዳሌሽን ወንዶችን ለማማለል በጠባብ ልብሶች ወጣጥረሽ፣ጡትሽን ወደ ፊት ገትረሽ፣ፀጉርሽን እንደ ግመል ሻኛ ወደ ላይ ፎቆ ሰርተሽ፣አይንሽን በኩል አጥቁረሽ፣ከንፈርሽን ደም እንደላሰ ውሻ በቀለም ተነክረሽ....ወዘተ። እነዚህንና የመሳሰሉትን ቆሻሻ በህሪያትን ተላብሰሽ ኢማን አንዳለው አፍሽን ሞልተሽ ስለ ኢማን ስታወሪ ቲንሽ እንኳን አታፍሪም? ወይስ ያንቺ ኢማን ነብዩ ከተናገሩት የኢማን አይነት የተለየ ነው? ለነገሩ ስለ ኢማን ገና በቅጡ መች ገባሽና።ያንቺ ጭንቅላት ከእውቀት ነፃ የሆነ ማሽን ሆኗል።

ለመሆኑ አሁን ተወጣጥረሽ ወደ ሀራም የተጣራሽበት ሰውነትሽ ነገ ምን እንደሚጠብቀው አስበሽ ታውቂያለሽ???
አስቲ የተወሰነ ላስታውስሽ፦
ያው መቼም እዝህች ምድር ላይ ለተወሰነልሽና ለተፈቀደልሽ ግዜ ከኖርሽ በኋላ ሞት የሚባለው መመለሻ የሌለው በጣም ሩቅ ጉዞ መጓዝሽ አይቀርም። አንግዲህ እንደ ሚታወቀው ነፍስሽ ከአካልሽ ከተነጣጠለችባት ሰዐት ጀምሮ በሰው እጅ መገለባበጥሽ ይጀምራል። ስምሽ ሁላ "ሬሳ" ይባላል። ዛሬ ሰውነትሽን ሰትሪው አጅነብይ እንዳይመለከተው ስትባይ አምፀሽ ስትገላለጪ የነበረውን ያኔ ሳትወጂ አጣቢዎች ራቁትሽን አድርገው ያገለባብጡታል።አጥበው ሲጨርሱም ዛሬ በተለያዩ የቻይና ፋሽን ጨርቅ ስታሽሞነሙኚው የነበረውን አካልሽን በተወሰነች አቦጀዴ(ከፈን) ጠቅልለው ቁጭ።ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን!!!
ያንቺ ጣጣ መች በዚህ ያበቃል ገና የባሰው ሰቀቀን የተሞላበት ህይወት ከፊትለፊትሽ ተደቅኖ።እሱም የቀብር(በርዘኽ) ህይወትሽ ነው።ገና ሬሳሽን ተሸክመው ሲሄዱ "ወዴት ነው የምትወስዱኝ? መልሱኝ እንጂ" እያልሽ ገና ቀብሩን ሳትገቢ የከንቱ "ዋይታሽን" ታሰሚያለሽ። የሞተን መቅበር ግዴታ የሆነባቸው ቤተሰቦችሽና ወገኖችሽ ሳይወዱ ወስደው በዛች ከሁለት ሜትር ባልበለጠች የዘለዓለም ቤትሽ ሸለቆ ውስጥ ያስገቡሻል።ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን!!! እህቴ ዛሬ አንደፈለግሽ ስትወጣጥሪውና በተለያዩ የሜካፕ አይነቶች ስታኳኩይው የነበረው ሰውነትሽ ምን ላይ እንደሚወድቅ አስቢው።ቀጥታ አፈር ላይ ነው የምትነጠፊው።መኚታሽ አፈር፣ትራሱ አፈር፣ ግድግዳው አፈር፣ ጣሪያው አፈር፣ በላይሽ ላይ የሚመለሰው አፈር።ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን!!!።

ነኪርና ሙንከር መጥተው ሲጠይቁሽ ትክክለኛውን መልስ ከመመለስ ይልቅ አንደ አሂያ ነው የምትጮሂው። ሰባት ምድርን ቁልቁል እስክትገቢ ድረስ ነው አናትሽን በያዙ መዶሻ የሚያላትሙሽ።ቀድሞውንም በጠባቡ የተሰራቿ ቀብርሽ ይባስ ብላ የጎዲን አጥንትሽ የቀኙ በግራ የግራው በቀኝ እስከሚወጣ ሁለቱ ኩላሊቶችሽ ካፍንጫሽ እስከሚወጣ ቀብርሽ ስያጣብብሽ ምን ይውጠሽ ይሁን???
እህቴ "ሳይቃጠል" በቂጠል ነውና አሁንም አረፈደም ሞት ሳይቀድምሽ በተውበት ቅደሚው። የነብዩ ሱና ይግዛሽ።ዲናችን ሙሉእ የሆነ ዲን ነውና ተብቃቂበት።

ሼር ሼር

Abu Mahir (Abdurezak)
675 viewsእንደ አበባ ፈክተሽ ወንድ ከምታፈዢ ሂጃብሽን(ኒቃብሽን) ለብሰሽ ጌታሽን ተገዢ!!!, 19:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-11 22:42:55 ሔር-ባንድ ምንድነው?
~
ሔር-ባንድ ማለት አሁን ባለነበት ግዜ ብዙ ሙስሊም ሴቶች ፀጉራቸው ላይ የሚደርቡት ሒጃባቸውን ወደ ላይ ከፍ አድርገው የሚሰቅሉበት ዘመን አመጣሽ ጨርቅ ነው።በርግጥ ሙስሊም ሴቶች ብቻ አይደለም የሚጠቀሙት።አልፎ አልፎ ሌላ እምነት ተከታዮችም ሲጠቀሙት ይታያል።ነገር ግን በሙስሊሞቹ ላይ በቢዛት ይታያል።ምክኒያቱም የሌሎች እምነት ተከታይ ሴቶች ፀጉራቸውን ገልጠው እንደፈጉት ለሰው እይታ ስለሚታይላቸው ወደ ታችም ለቀው ወደ ላይም ሰቅለው በግልፅ ማሳየት ይችላሉ።ስለዚህ ሔር-ባንዱን ለመጠቀም ብዙም አይጨነቁም።የኛ እህቶች ግን ፀጉራቸውን በሒጃባቸው ስለሚሸፍኑትና ጎላ ብሎ ስለማይታይላቸው ግዴታ ጨርቅ እየጠቀለሉ ወይም ሔር-ባንድ በመጠቀም ወደ ላይ ካልቆለሉት ፀጉር ያላቸው አይመስላቸው ስለዚህ በብዛት የሔር-ባንድ ተጠቃሚ ሙስሊም እህቶቻችን ሁነው ተገኙ።

ሔር-ባንድ መጠቀም በኢስልምና መነፅር፦

ሔር-ባንድ መጠቀም በኢስልምና በሁለት መንገድ ሐራም(ክልክል)ነው።ለዚህም ማስረጃዎችን መጥቀስ ይቻላል።
1ኛ ነብዩ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) በአንድ ወቅት ላይ ወደ ገበያ ሄደው ገበያ ላይ ዞር ዞር ሲሉ አንደ እህል ሻጭ እህሉን በጆኒያ ሰፍሮ ቆሟል ከዛም ነብዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ክንዳቸውን ሰበሰቡና እጃቸውን ወደ ውስጥ አስገቡት።ከዛም እርጥበት የነካውን እህል በጃቸው ዘገኑና "ለምንድነወ በአንድ ጆኒያ ላይ እርጥቡን ከውስጥ አድርገክ ደረቁን ከላይ ያደረግከው?"ማለትም ያው መቼም ሰው ያየውን ስለሆነ አምኖ የሚገዛው ሰዎች ከላይ ደረቁን አይተው ከታች እርጥብ መሆኑን አያውቁምና ሙሉ ጆኒያውን ገዝተው ይሄዳሉ።ስለዚህ እንዴት ሰውን ታታልላለህ? የገዘ ሊገዛ የተወ ሊተው እንዴት እርጥቡን በግልፅ እያሳየክ አትሸጥም?ደረቁን ከላይ አስመስለክ እርጥቡን ከስር ደብቀክ ትሸጣለክን?ማለታቸው ነው።ከዛም ነብዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ አሉ፦"መን ገሸና ፈለይሰ ሚንና(ያተለለን ከኛ አይደለም)"ብለው አሉት።ከዚህ ሐዲሥ በግልፅ የምንረዳው ነገር አንድ ሰው ከላይ ሌላ ነገር እያሰየ ከውስጥ ግን በተቃራኒ ከሆነ ገሽ(ማተለል)ነው ማለት ነው።አንድ ሰው አታላይ ከሆነ ደግሞ ከነብ አይደለም።ይሄው ነብዩ በግልፅ ያታለለ ከኛ አይደለም እያሉ ነው።እሺ ይህንን ሐዲሥ ከተረዳን ወደ ሔር-ባንዱን ስለመልበስ በሐዲሡ አንፈትሸው።

እህቴ ሆይ?

አንቺ አላህ በሰጠሽ ፀጉር ትንሽም ትሁን አመስግነሽ መኖር ያቃተሽ ዊግንና የመሳሰሉትን አርቴፊሻል ፀጉር ለፀጉርሽ መቀጠል አይቻል።ዊግ የተጠቀመችን ሴት ነብዩ ረግሟታል ስትባይ አሁን ደግሞ "አልሸሹም ዞር አሉ" አይነት ነገር ውስጥ ገብተሻል።አንቺ የሌለሽን ፀጉር ያለሽ ለማስመሰል ዊጉን ስትከለከይ የተለያዩ ዘመን አመጣሽ ጨርቃ ጨርቅ እየለጠፍሽ እንቶ ፈንቶ ጎትተሽ መጣሽ?ወላሂ እመኚኝ አታላይ ነሽ!ቅድም በሐዲሡ እንዳየነው የሌለውን ያለ ማስመሰል ከላይ ሌላ ከውስጥ ሌላ መሆን ገሽ (ማታለል) ነው።አንቺ ከውስጥ የሌለሽን ያክል ፀጉር ከላይ ጨርቅ ከምረሽ ፀጉር ያለሽ ለማስመሰል መጣጣር ይቅርብሽ።"አይ አይቀርብኝም"ካልሽ ደግሞ በቃ ከነቢዩ ላለመሆንሽ እርግጠኛ ሁኚ።

2ኛው ሀዲሥ፦ነብዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ወደፊት ስለሚመጡ ሸረኛ ሴቶች አላህ በራህመት አይኑ የማያያቸው ብለው ባህሪያቸውን ሲያብራሩ ከጠቀሱት አንዱ "ፀጉራቸውን እንደ ግመል ሻኛ ወደ ላይ ከፍ አደርገው ይቆልሉታል"ነበር ያሉት።ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን! ተመልከቺ ምን ያክል እንደተዛተብሽ።ዛሬ አንቺ ረጅም ፀጉር ይኑርሽም አይኑርሽም ጨርቃ ጨርቅ ላቃቅመሽ ወደላይ መቆለልሽ በቀላሉ ከአላህ ራህመት እራቅሽ መሆኑን አትጠራጠሪ።ከአላህ ራህት ርቀሽ በማን ራህመት ስር እንደ ምትሆኚ ደግሞ አስቢበት የቤት ስራ ሰጥቼሻለሁ።"ምነው አካበድክሳ አላህ እንዳንተ አይደለም መሃሪ ነው"ምናም ብለሽ ደግሞ የተለመደውን "ማስተኛ መርፌ" እራስሽን አትውጊ።እኔም ምንም ያካበድኩብሽ ወይም ከራሴ ያመጣሁብሽ አዲስ ነገር የለም።ሐዲሥ ነው የነገርኩሽ።ልቦለድ አልፃፍኩልሽም።

ምናልባት "ሔር-ባንዱን ፀጉር ማሳዥያ ብለን እንጂ ሌላ ፈልገንበትኮ አይደለም" ልትይኝ ትችያለሽ።ለፀጉር ማሳዝ ከተፈለገማ ድሮ እህቶች ሲጠቀሙት የነበረ ትንንሽ በየ ሱቁ የሚሸጥ ፀጉር ማሳዣም አለ።ኧረ ለምን ሌላ በቀላሉ በብር ላስቲክ ስትጠቀሚ አልነበረም?ዛሬስ የሚጠቀም የለም?ምን አዲስ ነገር አለው?ፀጉርሽን ሰብስቦ ሊይዝልሽ ካልሆነ በቀር።"እንዴት በሰለጠ ዘመን የብር ላስቲ ምናምን ትላለክ?"ልትይኝ ትችያለሽ።አዎ እልሻለሁ!ኧረ እንደውም ለምን በቁራጭ ገመድ ፀጉርሽን አትሰበስቢም!ምክኒያቱም ይህ ነው ላንቺ የሰላም ቀጠና።ከአላህ በራህመት አይን ከመራቅ መቶ በመቶ የብር ላስቲክ ይሻልሻል።የተፈቀደን ነገር ለክብርሽ "አልመጠነኝም" ብለሽ ወደ ሀራም መሄዱ ትልቁን ክብር ማጣት ይህ ነው የሚሆነው።መቼም እርግጠኛ ነኝ ብዙ ሰዎች ተሰብስበው ቢራ ሲጠጡ ብትመለከቺ ይህ ሰው ሁሉ ቢራ እየጠጠ እየተዝናና እኔ ውኃ መጠጣቴ ሼም ነው።ዘመናዊነትንም ማጣት ነው ብለሽ ቢራ አታዢም አይደል?ሺ ግዚ ዘመናዊ አይደለችም ይበሉሽ እንጂ አቅልሽ ካልደነዘዘ በቀር አይንሽ እያየ ቢራ ገዝተሽ አትጠጪም አደል? ልክ እንደዚሁም ብዙ ሴቶች ሔር-ባንድን ስለተጠቀሙ እኔ እንዴት ፋሽኑ ባለፈ ፀጉር ማሳዣ እጠቀማለሁ ወይም እታች ወርጄ በብር ላስቲክ እጠቀማለሁ ብለሽ ሌሎች የተጠቀሙት ጨርቅ ካልጠቀለልኩኝ ካልሽ የአስተሳሰብ ድንዙዝነት አለ ማለት ነው።ከዚህ ድንዛዜ ደግሞ ማገገም አይቻልም ዲንን በመማር ቢሆን እንጂ።ስለዚህ አደራሽ ያለ መታከት ዲንሽን በቅጡ ተማሪ።ነገ ከነገ ወዲያ ሳትይ አላህን ፈርተሽ በላይሽ ላይ ያለውን ዘመን አመጣሽ ድርሪቶ አውልቀሽ ጣይ።



አደራ ለአላህ ብላችሁ ሼር ማድረግን እንዳትረሱ።ወላሂ ብዙ እህቶች እዚህ በሽታ ላይ ናቸው።












Abu Mahir (Abdurezak)
742 viewsእንደ አበባ ፈክተሽ ወንድ ከምታፈዢ ሂጃብሽን(ኒቃብሽን) ለብሰሽ ጌታሽን ተገዢ!!!, 19:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-07 22:41:30 እስቲ ራሳችንን እንፈትሽ
በቀን ውስጥ ምን ያህል ኸይር ስራ ሰርተናል?
በቀንምን ያህል ሰለዋት አውርደናል?
293 viewsردونــــا مـُـه‍ـــمــــد, 19:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-07 01:20:26
73 viewsAllah is great, 22:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ