Get Mystery Box with random crypto!

አል ሂዳያ የየቲሞች መርጃና በጎ አድራጎት ጀማአ 0993632424//0703136300አዲስ አበባ

የቴሌግራም ቻናል አርማ alhidayatv — አል ሂዳያ የየቲሞች መርጃና በጎ አድራጎት ጀማአ 0993632424//0703136300አዲስ አበባ
የቴሌግራም ቻናል አርማ alhidayatv — አል ሂዳያ የየቲሞች መርጃና በጎ አድራጎት ጀማአ 0993632424//0703136300አዲስ አበባ
የሰርጥ አድራሻ: @alhidayatv
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 15.07K
የሰርጥ መግለጫ

ኑ ተባብረን ባለን አቅም የቲሞችንና የተቸገሩ ሙስሊም ወገኖቻችንን እንርዳ
በልብስ👕👖 በገዘብ በአስዜዛ በጉልበት በሀሳብና
በተለያዩ በቤት ቁሳቁሶች መርዳት ትችላላቹ
ንግድ ባንክ
1000375043298
ሪድዋን ሙሀመድ
አባል መሆን ለምትፈልጉ
ለበለጠ መረጃ
251993632424
ወይም የቢሮ ቁጥር
251703136300
ወይም በኢቦክስ
@RidAmirsab
ሰደቃ ወጀልን ታብሳለች ረሱል (ﷺ)

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-03-16 18:21:29 ዘመናዊ የባላባት ስርኣት
ድሮ በዘመነ ባላባት ህዝብ በተለያየ እርከን የተከፋፈለ ነበር፡፡ አንደኛ ደረጃ ሰው፣ ሁለተኛ ደረጃ ሰው፣ ሶስተኛ ደረጃ ሰው…፡፡ የታችኛው ደረጃ ለላይኛው ይሰግዳል፣ ያጎበድዳል፡፡ ታችኛው ላይኛውን ሊያገለግል “የተፈጠረ” ነው፡፡ ላይኛው ሲበዛ የተንቀባረረ ነው፡፡ ከሌሎች ጫፍ ሳይደረስ በራሱ አጥር ውስጥ በተገደበ “ጃሎ” ቢልም በተቻለ፡፡ አንጀቴ መቻል! እሺ ይሁን ችግሩ ግን መንቀባረሩም አጉራ-ዘለል መሆኑ ነው፡፡ ባለ ነጭ በቅሎው፣ ባለ ነጭ ጭራው፣ ኩፍሱ የላይኛው መደብ አባል ሲያልፍ ሲያገድም እገረ ቡላው፣ ፀጉረ ጨብራራው፣ አመዳሙ የታችኛው መደብ አባል እንደ ሰፌድ እየተዘረጋ፣ እንደማጭድ እየተቆለፈ ካላሳለፈ ወዮ ለናቱ! የሚለፋው ለሌላ! የሚኖረው ለሌላ! ግን አይበቃም በዚህም ላይ ብዙ ግፍ አለ! “ይቺም እንጀራ ሆና ሚጥሚጣ በዛባት” አሉ፡፡ ቢመርህም ሲያምርህ ይቀራል እንጂ ሌላ ህይወት አታስብ፡፡ በቃ መሮህ መሮህ መሮህ … ከዚያ መሮህ ስለ ምሬትህ ትማረራለህ፡፡ እንደ መረረህ ትኖራለህ እንደመረረህ ትሞታለህ፡፡
“ለምስለኔው ሙክት ለጭቃው ወጠጤ
እንዲህ ሆኜ ነው ወይ ባገር መቀመጤ” ትል ይሆናል፡፡ ካልተመቸህ ካገር ውጣ! ምን ታመጣለህ?! “እምቢ” ካልክ ደግሞ ያንተው ቢጤ እልቆ መሳፍርት አመዳም ጭሰኞችን ያን መከረኛ ከርሳቸውን ወጥቆ ባንተ ላይ ያዘምታቸዋል፡፡ ከመቅፀብትም ትቢያ ያደርጉሃል፡፡ ባይሆን አንዳንዴ ይሳካል፡፡ እምቢታ እምቢተኞችን ይጠራል፡፡ የእንቢተኞች ህብረት ይፈጠራል፡፡ “ፋኖ ተሰማራ” ይዘመራል፡፡ የባላባቱ አከርካሪ ይሰበራል፡፡ ምን ዋጋ አለው እፎይ አትል! ሌላ የባላባት ስርኣት ቀስ እያለ ይጎመራል፡፡ እጀ ጠባቡ በቦላሌ ይቀየራል፡፡ የትላንቱ ባላባት መኮፈሻ ነጭ ፈረስ ተገባብጦ እያነከሰ ጋሪ ይጎትታል፡፡ አንተ ግን ያው ነህ! ከየተረኛው ባላባት ወፍጮ ገብተህ ትፈጫለህ፡፡ እምቢ ያልክ እለት እንደ አንጣሪያ፣ እንደ አቀንጭራ፣ እንደ ቅንጬ አረም በደቦል ተመንጥረህ ትጣላለህ፡፡ አይበቃህም፡፡ መጠጥ ስትል በደንብ ሳትደርቅ ዘርህ ሳይረጭ ትቃጠላለህ፡፡ ተረኛው ይቀጥላል፡፡
ግን ያኔ ያኔ ነበር፡፡ ድሮ በቃ ድሮ ነበር፡፡ አሁንስ በድሮ በሬ አይታረስ ነገር? እኔን ግራ የሚገባኝ ግን የታሪክ አዙሪቱ ነው፡፡ “ታሪክ እራሱን ይደግማል” የሚባለው እውን ተረት ነው ወይስ ሀቂቃ? የትላንቱ የባላባቶች ታሪክ የቋንቋ፣ የቅብና የውርርስ ሂደቱ እንጂ ለካስ ዛሬም ቀጥሎ ኖሯል?!
እስኪ አስቡት! በአለም ላይ ፍርድ ቤት አካባቢ የሚታየው ድንበር ዘለል አጀብ ከባላባቱ ስርኣት ምን ያህል ነው ርቀቱ? ባለጉዳይ ጠንቋይ ቤት እንደገባ ቂላቂል ካልተሸማቀቀ በቃ የፍትህ ስርኣቱ ክብሩ ተደፍሯል ማለት ነው፡፡ ታዲያ “እንዲህ አይባልም”፣ “እንዲህ አይቀመጥም”፣ “እንዲህ አይቆምም”፣ … እያሉ ሰንሰለታማ መመሪያዎችን ከሚደረድሩት እናቶቻችን ምን ይሆን ልዩነቱ? ህገ-ደንቦች ፋሽናቸው ያለፉ፣ አሰልቺ፣ ማዘር እስታይል ትብትቦች አድርገን መቆጠራችን ለምን? የዳኞች ዋና አላማ ፍትህን ማስፈን ወይስ አስፈሪ አባታቸው ገብቶ በስጋት ዐይናቸውን እንደሚያቁለጨልጩ ህፃናት ፍትህ ጠባቂዎችን ማርበትበት ነው? ዶክተሮች አካባቢ የሚታየው መረን የለቀቀ አንባገነንነትስ ሃይ ባይ ማጣቱን ምን ይሉታል? ስነ ምግባር የሚባል ነገር አልነበረም? ዛሬ ቀረ ወይስ መልኩ ተቀየረ? ድብርብር፣ ጭፍግግ፣ ኩፍስፍስ፣ ቅብርርር እያሉ በበሽተኛ ወገን መሀል መንጎባለል ምን የሚሉት ጀብደኝነት ነው? ተረኛ በሽተኛ ተኮርትሞ ተቀምጦ በዘመድ በትውውቅ በጎን ማስገባቱስ ምን የሚሉት ጭራቃዊነት ነው? አቤት ወጥ ረገጥነት! የዚህ የምትበሻቀጥበት ምስኪን በሽተኛ ድምር ጥረት እኮ ነው አንተን ለወግ ማዕረግ ያበቃህ!!! ደግሞ አስተውል አንበሳ በበሽተኛ አንበሶች መሃል የሚጀነን ከሆነ አንበሳ ሳይሆን ጂብ ሆኗል ማለት ነው፡፡
እዚያጋ ደግሞ የበሰበሰውን የጥንቱን የባላባት ስርኣት የሚኮንን የዩኒቨርሲቲ አስተማሪ አንዴ በአይነ ህሊናችሁ ቃኘት አድርጉትማ፡፡ ስለ መልካም አስተዳደር ይሰብካችኋል:: እሱ ግን መልካም ስብእና አልሸተተውም፡፡ መሪዎች አካባቢ ያለውን አንባገነናዊ አካሄድ ከፊታችሁ በምላሱ ያንኮታኩተዋል፡፡ መላ ሰውነቱ ግን ከአንባ ገነንነት የተገነባ ነው፡፡ ምነው ግን ለራሱ ሲሆን “ዘመናዊ” የባላባት ስርኣት ሊገነባ ይታገላል? ስለመከባበር አትሞግቱኝ፡፡ እኔ ከዚያ በላይ ስላለው ሰፈር ነው እያወራሁ ያለሁት፡፡ በቃ እንዲሁ ነው፡፡ በየሙያ ዘርፉ ሁሉም የራሱን የፊውዳል ስርኣት ገንብቷል ወይም እየገነባ ነው፡፡ “ለምን” ካልክ የሙያውን ክብርና ዋጋ አጣቅሶ ያስረዳሃል፡፡ ባይገባህም ይገባሃል፡፡ አሁንም ካልገባህ ግን ያስገባሃል፡፡ “ፍየል ወዲያ ቁዝምዝም ወዲህ” ይሏል ይሄ ነው፡፡ በነገራችን ላይ ፌስቡክም ላይ የፌስቡክ ባላባቶች መሆን የሚያምራቸው የትየሌሌ ናቸው፡፡ ምንም እንኳን በየጥጉ የሚያደፍጡ የፌስ ቡክ ሽምቅ ተዋጊዎች ለፌስቡክ ባላባቶች ምቾት ቢነሱም በተለያየ መልኩ ሰፋፊ ርስቶችን ዘርግተው ፌስቡከኛውን ሁሉ “እኛ እናውቅልሃለን”፣ “እንዲህ ተንፍስ”፣ እንዲህ አስነጥስ” የሚሉት ቀላል አይደሉም፡፡ “ኧረ እንዴት ነው ነገሩ” ብሎ የጠየቀን ሁሉ የፌስቡክ ጭሰኛ ለማድረግ መጠነ ሰፊ ዘመቻ ወይም ወረራ የሚፈፅሙ ባላባቶች እንዳሉ ፌስ ቡኩ ይቁጠረው፡፡ የሚገርመው እነዚህ የፌስ ቡክ ባላባቶች አማራጭ የነፃ ሀሳብ ማንሸራሸሪያ እንደሆኑ የሚሞግቱ፣ ስለ ነፃ ፕሬስ ሌሎችን የሚኮንኑ፣ በነፃ ፕሬስ ፀበል ፀዲቅ ሌሎችን የሚያጠምቁ ከመሆናቸው ጋር ከነሱ የተለየን ሀሳብ ለማስተናገድ ግን ዲሹም፣ ሪሲቨሩም፣ አንቴናውም ይገዳቸዋል፡፡ …
ህይወት እንዲህ ይቀጥላል፡፡ ይሄ ሲያልፍ ተረኛው ይገባል፡፡ እብድ አለም እብድ ስብስብ እብድ ስርአት፡፡

@HidayaTv
257 viewsإذلم تتعلم التو حيد والعقيدت الصحيحت ستخيفك البو مت ويغير مزاجك, 15:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-16 09:57:29
እዉነት ግን ምነዉ የኑራጌ ክልል ሙስሊም እህት ተማሪዎችን ጉዳይ ችላ አልነዉ

አረ ተዉ ባአላህ ድምፀ እንሁናቸዉ ችላ አንበላቸዉ አረ ተዉ ተዉ
~
በሴኩላሪዝም የሙስሊሞችን መብት እየተጋፉ ከትምህርት ገበታ ያርቃሉ። በሴኩላሪዝም በሚታወቁት የምእራቡ ዓለም ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ግን ሙስሊም ሴቶች ከነ ኒቃባቸው ተምረው ሲመረቁ እያየን ነው። እኛጋ ሴኩላሪዝም ሽፋን እንጂ መንስኤው ጥላቻና ክፋት ብቻ ነው። ማስመሰል በቃ! ችግሩን በስሙ ጥሩት!

ከጭቁኑ መዝገበ ቃላት
1. አስተማሪ- ግንባር ቀደም የመብት አቀንቃኝ ቀንደኛ ተግባራዊ አንባገነን
2. ትምህርት ቤት- ስለ ሰብአዊ መብት በብዛት የሚሰበክበት የሙስሊሞች መብት በስፋት የሚጣስበት የግፍ አፀድ
3. የሀይማኖት መቻቻል- በቲቪና በሬዲየ የሚለቀቅ ሙስሊም አደንዛዥ ኬሚካል
4. ስላሴ- ህፃናት የማይስቱት ቀላል ሂሳብ “አዋቂዎች” ወደው የዋጡት ቅልጥም
5. እኩልነት ለሴቶች- ከወንዶች የግፍ ፌርማታ ተነስቶ ወደሌላ የወንዶች የግፍ ፌርማታ የሚያደርስ ልብስ የሚያስጥል ዘመቻ

የሶሻል ሚዲያ ዘመቻ
=
@HidayaTv
434 viewsإذلم تتعلم التو حيد والعقيدت الصحيحت ستخيفك البو مت ويغير مزاجك, 06:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-11 23:40:55 በስሙ ጥሩት!
~
በሴኩላሪዝም የሙስሊሞችን መብት እየተጋፉ ከትምህርት ገበታ ያርቃሉ። በሴኩላሪዝም በሚታወቁት የምእራቡ ዓለም ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ግን ሙስሊም ሴቶች ከነ ኒቃባቸው ተምረው ሲመረቁ እያየን ነው። እኛጋ ሴኩላሪዝም ሽፋን እንጂ መንስኤው ጥላቻና ክፋት ብቻ ነው። ማስመሰል በቃ! ችግሩን በስሙ ጥሩት!
= @HiDAYATV
217 viewsإذلم تتعلم التو حيد والعقيدت الصحيحت ستخيفك البو مت ويغير مزاجك, 20:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-09 10:16:08 ➲ ሴቶችዬ አገር ስትገቡ ጠንቀቅ በሉ

➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘
➵ማንን አትመኑ መስሊም➴ ሴትም ወንድም ቢሆን ጊዜው ➴አስገፍቷል ማንን ማመን እዳለብንም ግራ ያጋባል

➵አገር ቤት ስትገቡ እቃ ይዘሽልኝ ሂጂ ሲሎሽ
ይዘሽ የምቴጅውን ➴እቃ በደኔብ እወቂ እይው
ዝብለሽ አምናታለሁ አምነዋለው ብለሽ ሳታይ አትሂጂ ሀታ ➴➴ጓደኛሽም ብቶን እይው  ማንኛውም እቃ ሰው ➴ከኸይር ነገር ሸር ተንኮል
ምቀኝነት ያለበት ➴አይጠፋም አላህ ይጠብቀን
➘➘➘➘➘➘➘
➵ሊላው ኤርፖርት ላይ ብዙ ሊቦች ሌብነት ስራቸው አድርገው ➴የያዙ አታላዮች ታክሴዎች ሴቶች  ➴በተለይ ሂጃብ ለብሷ ምንም ጥርጣሪ እንይኖርሽ አርገው ይቀርቡሻል አትመኚ ➴ጠንቀቅ
➘➘➘➘➘➘➘➘➘
➲የትም ቦታ ስቴጂ ታክሲ ውስጥ እንዳትሸወጂ ጠንቀቅ
➘➘➘➘➘➘➘➘
➵ ታክሲ ስትገቢ ሚያጠ ➴ራጥርሽ ነገር ካየሽ እንዳገቢ  ስጀት ላይ የለመድሽ ነፃነት አገርሽም እንዛ መስሎሽ ችልተኛ እንዳትሆኜ
➘➘➘➘➘➘➘➘➘
➵ ካጠገብሽ እርጉዝ ካለች  አትሸወጂ ጨርቅ ሆዷ ላይ ጠቅጥቃ አመመኝ ብላ ችግር ፈጥራ አንቺ ደንግጠሽ ትኩረትሽን ወደሷ ስታረጊ እቃሽ ከቦርሳሽ አሟጠው ይወስዳሉ ጠንቀቅ
ጥፍግ አርገሽ ያዢ ቦርሳሽን የታመም ሰው ተመስለው አውቀው እርጎ ባፋቸው ይዘው እዳስታወኩ አንቺ ላይ ሊተፉ ይችላሉ ቀፎሽ ስጠራርጊ እነሱ ላፍ ያረጎሻል ቦርሳሽን ይዘሽ ጥረጊው  ካጋጠመሽም
➘➘➘➘➘➘➘➘➘
➘➘➘➘➘➘➘➘➘
➵ስልክሽን ከቦርሳሽ➴ አታውጪ በጅሽ አትያዤው  እንጂሁም መንገድ ላይ እያወራሽ ከትሂጂ ቦታ ➴➴መርጠሽ ጥግ ይዘሽ አናግሪ➴➴➴➴➴➴
ላዚም አስፈላጊ ስልክ ➴ካልሆነ በስተቀር አታንሺ ትደርሽበታለሽ ➴ቤትሽ ስደርሺ ማውራት ትችያለሽ እንደ ➴ ድሮ በጅ ይዞ ጎርድ ጎርደድ እያለ ➘ይዞ መሄድ ቀረ አይን አውጣ ሆነዋል  ➴ሊቦች ሌብነት መተዳደሪቸው ➴ያሰጉት አሉ ቢቻልሽ በውድ ዋጋ የገዛሽው ስልክ ቤትሽ አስገምጠሽ ስቶጪ ➴ቀለል ያሉ ስልኮች ያዤ

➘➘➘➘➘➘➘➘➘

➵ቦርሳሽን በጎን አትያዢ  ➴በፊለፊትሽ አድርገሽ ➴ያዢ
➵እዩኝ እዩኝ አትበይ ደ➴በቅ ላዚም ጉዳይ ከሊለብሽ ➴ላልሆነ ነገር ዝብለሽ አትውጪ።
➘➘➘➘➘➘➘➘➘
➘➘➘➘➘➘➘➘➘
➵ጓደኛዬ ሁለት ስልክ ታክሲ ውስጥ ወሰደብኝ አለች  ብልጥ ሁኑ➘➘➘

➘➘➘➘➘➘➘➘➘
➵ከመውረዳቹ በፊት መውረጃቹ ቦታ ስደርሱ
ሳትወርዱ ቦርሳቹን እዩት እናም  እናተ ከገባቹ በኋላ የወረደሰው ከታክሲ ስታዩ እዩ ጥፍግ አርጋቹ በፊለፊታቹ ያዙ  ምናልባትም እቃቹ ይገኝ ይሆናል ከተሰረቀ
➘➘➘➘➘➘➘➘➘
➵ስትቀመጡ➴ ከወንዶች ጋር ተጋፍታቹ አትሄዱ የፈለገ ብቸኩሉም ታክሲ ውስጥ ስትገቡ➴ በግፊያ  ስለሚሰርቁ ➴ቦርሳቹን በፊለፊት አርጋቹ
ገመዱን ሳይሆን እጃቹን በፊለፊት አርጋቹ ቦርሳውን ያዙ
➵ብዙ ሲስተሞች ይኖራሉ አትመኑ ጊዜው ከፍቷል እህቶቼ የዋህነት አያጥቃቹ
➘➘➘➘➘➘➘➘
➵ስትወጪ ሁሌም አዝካሮችን ብለሽ ውጪ አላህ ይጠብቀን

➵ጥንቃቄና ቤትኛውም ቦታ አብሮን ሊኖር የሚገባ ነገር ነው።
أم نوح
ለህቶች እንዲዳረስ ሼር እያረጋቹ

ጆይን
https://t.me/HiDAYATV
https://t.me/HiDAYATV
398 viewsإذلم تتعلم التو حيد والعقيدت الصحيحت ستخيفك البو مت ويغير مزاجك, 07:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-08 22:07:31
አሰላሙአለይኩም ወራህመቱሏሂ ወበረከትሁ በአሏህ ፈቃድ ሆኖ እኝግዲህ አጠቃይ ለረመዷን ለእናቶች የወር አስቤዛ ባለፈዉ እሁድ ሰተን ነበረ ዛሬ ደሞ አንዳድ ድርጅቶች አብረዉን በመሳተፋቸዉ ምክኒያት አልሀምዱ ሊላህ 120ፓስታ ካርቶንና 100 መዳበሪያ 25ኪሎ የሚይዝ መኮረኔ ዛሬ አስገብተናል ኢንሻ አሏህ ለእናቶችም በየቤታቸዉ እየዞርን ስንሰጥ ነበረ አልሀምዱ ሊላህ አሏህ ስለፈቀደዉና ስለረዳን ከአምናዉ ረመዷን ይልቅ የዘንድሮዉ ረመዷን በጣም ቀላል በሆነ መልኩ ለ280እናቶች ለረመዷን አስቤዛ ሰተናል


አምና ለ50እናቶች ነበረ ዘንድሮ ግን 280እናቶች ስራዉንም በቀላሉ ከረመዷን በፊት ልንጨርስ ነዉ አሁን የቀሩን እናቶች 32እናቶች ብቻ ናቸዙ ሀዬ እነሱን ተረባርበን እንስጣቸዉ እናስገባላቸዉ ሀዬ ሀዬ ዳይ ወደ ስራ


አል ሂዳያዎች ግን በጣም እየጠነከራቹ ነዉ አሏህ ይጨምርላቹ
https://t.me/ALHidayaTv/20027?single
https://t.me/ALHidayaTv/20027?single
264 viewsإذلم تتعلم التو حيد والعقيدت الصحيحت ستخيفك البو مت ويغير مزاجك, 19:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-07 15:47:28 ያጀማአ ኢድ አል ፈጥር ስንት ቀን ቀረዉ
349 viewsإذلم تتعلم التو حيد والعقيدت الصحيحت ستخيفك البو مت ويغير مزاجك, 12:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-04 21:39:40
አሰላሙአለይኩም ወራህመቱሏሂ ወበረከትሁ ዛሬ በአሏህ ፈቃድ ሁኖ አንዲት ሙሉ የአል ሂዳያ ጀማአ ተሰባሶቦ 10ካርቶን ዘይትና አምስት አምስት ኪሎ የሚይዝ በስመቲን ሩዝ 2ኩንታል ገዝተዋል ይህ የተገዜዉ በአል ሂዳያ ጀማአ አባላቶች ብቻ ነዉ አል ሂዳያዎች ማሻ አሏህ ጠክራቹሀል አሏህ ይጨምርላቹ

እንግዲ ኢንሻ አሏህ አስቤዜዉን ለመሳኪኖች የፊታችን እሁድ ጀምሮ መስጠት እንጀምራለን

ሌሎችም መሳኪኖች ስላሉን መሳተፍ የምትፈልጉ እህት ወንድሞች ተሳተፉ የአጅሩም ተካፋይ ሁኑ መሳተፍ ለምትፈልጉ በዉስጥ መስመር አናግሩን @RidAmirsab

https://t.me/ALHidayaTv/20023
https://t.me/ALHidayaTv/20023
508 viewsإذلم تتعلم التو حيد والعقيدت الصحيحت ستخيفك البو مت ويغير مزاجك, edited  18:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-28 22:42:19
አልሀምዱ ሊላህ በአሏህ ፈቃድ የአሚራችን ሪድዋን ሙሀመድ እህትና ምክትል አሚራችን ኢክራም ሰኢድ እንዲሁም አብዱረዛቅ ሙክታር ቃል በገቡት መሰረት 12 ካርቶን ፓስታና 10ካርቶን አምስት ሊትር ዘይት አስገብተዋል መልካም ስራቸዉን አሏህ ይዉደድላቸዉና ምንዳቸዉን አሏህ እጥፍ ድርብ ያድርግላቸ ዱአ አድርጉላቸዉ

ሌሎቻቹሁም ተሳተፉ እኛ እያለን ሙስሊም ወንድም እህቶቻችን አይሬቡም አይጠሙም ሚያፈጥሩበትም አያጡም

https://t.me/ALHidayaTv/20022?single
https://t.me/ALHidayaTv/20022?single
752 viewsإذلم تتعلم التو حيد والعقيدت الصحيحت ستخيفك البو مت ويغير مزاجك, edited  19:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-24 22:46:11
#ኑ_ረመዷንን_ከመሳኪኖች_ጋር

አል ሂዳያ የየቲሞች መርጃና በጎ አድራጎት ጀማአ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል እንደተለመደዉ  በየ አመቱ የምናዘጋጀዉ ለመሳኪኖች ለረመዷን ወርሀዊ አስቤዛ ሰደቃ ለማድረግ ዝግጅት ካሁኑ ጀምረናል።

ረመዷን ሲመጣ ባለሀብቱ በተለያዩ ምግብ ባይነቱ ሲያማርጥ ሲቀያይርና ሲመገብ ሲበላና ሲጠጣ   ረመዷንን ሲያሳልፍ።

ሚስኪን ደካማዋ እናቴግን ረመዷንን በረሀብና በችግር  አንድ ጊዜ ማፍጠሪያ አታ አንድ ጊዜ ደሞ ምትጠጣዉ አታ አንድ ጊዜ ደሞ የምትበላዉ አታ ታሳልፋለች።

ታዳ እኛ ያለን ለምን ትራባለች ለምን ምታፈጥርበትስ ምግብ ታጣለች ኑ ተባብረን በአንድነት ለነዚ አቅመደካማ የቲም ለሚያሳድጉ አቅመ ደካማ እናቶችን ለረመዷን ምግብ እናስገባላቸዉ።

ለአንድ ቤተሰብ የረመዷን አስቤዛ 3000ሺብር

የሚገባላቸዉ የአስብዛ አይነት

ሩዝ 5ኪሎ ፓስታ 5እሽግ

ዱቄት 10ኪሎ ቴምር 5ኪሎ

ዘይት 5ሊትር የሾርባ እህል 10 ኪሎ

ንያቹሁን ማስገባት ለምፈልጉ
ንግድ ባንክ
1000375043298
ሪድዋን ሙሀመድ

ለበለጠ መረጃ 0993632424
/0975537107/0703136300

አል ሂዳያ የየቲሞች መርጃና በጎ አድራጎት ጀማአ
ቴሌግራም ቻናላችን ላይ በዛዉም ረመዷንን የሚመለከቱ ተከታታይ ኢስላማዊ ትምርቶችም ይሰጡበታል

https://t.me/ALHidayaTv/19970
https://t.me/ALHidayaTv/19970
205 viewsإذلم تتعلم التو حيد والعقيدت الصحيحت ستخيفك البو مت ويغير مزاجك, 19:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-21 22:51:38 የወላጅ  ሀቅ 
------------------------------
★አላህ ፍጡራንን ከፈጠረ በኃላ አንዱ በአንዱ ላይ ሀቅ እንዲኖረው አደረገ። ባል ሚስቱ ላይ ፣ ሚስት ባልዋ ላይ፣ ጎረቤት በጎረቤትለ ላይ ፣ ብሎም ሙስሊም በሌላው ሙስሊም ላይ ሀቅ እንዲኖረው አደረገ።

•ነገር ግን ከራሱ ሀቅ ቀጥሎ ትልቁ ሀቅ የወላጆች ሀቅ አደረገ

➩የአሏህ መልክተኛ ﷺ እንዲ አሉ አንድ ሰው በአፍንጫው አፈር ላይ ይደፋ ብለው ዱዓ አደረጉ፤ ማነው እሱ ተብለው ሲጠየቁ ወላጆችን አግኝቶ አንዳቸውን ወይም ሁለቱንም አግኝቶ ጀነት መግባት ያልቻለ ሰው ይደፋ ብለው ዱዓ አደረጉ የወላጅ በህይወት መኖር ላንተ ወደ ጀነት የተከፈተ በር ነውና እናት አባትህን ሳትሰላች ተንከባከብ ጥቅሙ ላንተ እንጂ ለነሱ አይደለም!!

አሏህ ሱ,ዐ ስለ ወላጅ ሀቅ ስናገር እንዲህ ይላል:

۞ وَقَضَىٰ رَبُّكَ أَلَّا تَعْبُدُوا إِلَّا إِيَّاهُ وَبِالْوَالِدَيْنِ إِحْسَانًا ۚ إِمَّا يَبْلُغَنَّ عِندَكَ الْكِبَرَ أَحَدُهُمَا أَوْ كِلَاهُمَا فَلَا تَقُل لَّهُمَا أُفٍّ وَلَا تَنْهَرْهُمَا وَقُل لَّهُمَا قَوْلًا كَرِيمًا

➩ጌታህም (እንዲህ ሲል) አዘዘ፡- እርሱን እንጂ ሌላን አትገዙ፡፡ በወላጆቻችሁም መልካምን ሥሩ፡፡ በአንተ ዘንድ ኾነው አንዳቸው ወይም ሁለታቸው እርጅናን ቢደርሱ ፎህ አትበላቸው፡፡ አትገላምጣቸውም፡፡ ለእነርሱም መልካምን ቃል ተናገራቸው፡፡

وَاخْفِضْ لَهُمَا جَنَاحَ الذُّلِّ مِنَ الرَّحْمَةِ وَقُل رَّبِّ ارْحَمْهُمَا كَمَا رَبَّيَانِي صَغِيرًا

➩ለሁለቱም ከእዝነትህ የመዋረድን ክንፍ ዝቅ አድርግላቸው፡፡ «ጌታዬ ሆይ! በሕፃንነቴ (በርኅራኄ) እንዳሳደጉኝ እዘንልላቸውም» በል፡፡

(ሱረቱል ኢስራዕ 23__24)

★ታዲያ የእናት ትርጉም የሁላችንም ቤት ነው ያለው ፣ለምን በእናት ያልተውለደ የለምና።

★ እናታችን ወይም እህታችን ነፍሰጡር በሆነች ጊዜ የምታየው ስቃይ ማየት ብቻ በቂ ነው የእናትን ትልቅነት ለመረዳት ።
አንድ ፀሐፊ ምን ይላል « እኔ ስለ እናት አንብቤም አዳምጬም አውቃለሁ ።ነገር ግን በጣም የተረዳሁት ባለቤቴ ነፍሰጡር ሆና ታየው የነበረው ስቃይ ደረጃ በደረጃ እከታተል ነበር ።የባለ ቤቴ ስቃይ 8 ኛው ወር ላይ እየከፋ ሄደ እንደፈለኩ ልተኛ፣ልብላ፣ ልጠጣ አትችልም ። አሟት ሀኪም ቤት ብወስዳት የሚያስታግስ እንጂ የሚያሽል መድሀኒት  አይሰጧትም ለምን ፅንሱ እንዳይጎዳ።
#የርግዝናው ስቃይ ያለ ሆኖ የቤትም ውጣውረድ እሷንም ይመለከታል ።

★ ይህ ሁሉ ግን ለሷ ምንም አይደለም፣ እንኳን ልትበሳጭ/ ኡፍ ልትል ይቅርና ልጄን መች ይሆን የማቅፈው ብላ ያለየችው ትናፍቃለች ። ይህም ላይሆንም ይችላል  ። ይህ ናት እናት ። ታድያ ለዚች እናት ትልቅ ሀቅ አላት ።

★ አንድ ሰው ዑመር رضى الله عنه  ዘንድ መጣና « እኔ እናቴ በጣም ከማርጀቷ የተነሳ ሽንት ቤት የምወስዳት ተሸክሜያት ነው ድሮ እኔ በጀርባዋ እሸና እንደነበረወ አሁን እሷ ትሸናብኛለችና ሀቋ ተወጥቻለሁኝ»  ብሎ ጠየቃቸው  { አልተወጣህም} { አልተወጣህም}  {አተውጣምም} አሉት ።ምክንኛቱም ያኔ እሷ ያ! ሁሉ ታደርግልህ የነበረው ማደግህን የተመኘች ነበር ። አንተ ይህ ብታደርግም ሞቷን የተመኘህ ነው አሉት ይባላል።


☞ ስለዚህ ይህ ትልቅ ሀቅ በቻልነው አቅም ልንውጣው እንሞክር

☞ በሀያት ካሉ ተውሂድን በማስተማር ከሽርክ እንዲሪቁና ዱንያ አኼራች እንዲያስተካክሉ እንርዳችው

☞ ከሞቱ ዱዓ እናድርግላቸው።

:የወላጅ ሐቅ እና እናት አባትን የማክበር ሲባል …

:ድምፅህን ከድምፃቸዉ በላይ ከፍ አታድርግ፣
:አጉል ክርክር አትከራከራቸው፣
:እነሱ ሣይጨርሱ አትናገር፣
:በሥማቸው አትጥራቸው፣
:እንቅልፋቸዉን ሣይጨርሱ አትቀስቅሣቸው፣
:ለምክኒያት ካልሆነ በስተቀር (አደጋ እንዳያገኛቸዉን ለመሣሠሉት) ከፊት ለፊታቸው አትቅደም፣
:እነርሱ ሣይቀመጡ ቀድመህ አትቀመጥ ፣
:ባሪያ ለጌታዉ እንደሚተናነሰው ሁሉ ተናነስላቸው፣
:ጠርተዉህ ሣይጨርሱ ‘ አቤት ’ በላቸው፣
:ከቤት ወጥተህ በመዘግየት እንዲያስቡ አታድርጋቸው፣
:በሀሳብ ተጨንቀህ አታስጨንቃቸው፣
:በእይታህ አታፍጥባቸው፣
:በንግግርህ አትዳፈራቸው፣
:በቁጣቸው መልሰህ አትቆጣ፣
:በንግግራቸው አትሣቅ, ሙድ አትያዝ፣
:መላና ሀሣባቸዉን አታናንቅ፣
:ሲጨንቃቸዉ አማክራቸው፣
:ሲቸግራቸው እርዳቸው፣
:ሲታመሙ አሣክማቸው፣
:ሲታረዙ አልብሣቸው፣
:ጉዳይቸዉን ሁሉ ጉዳዬ በል፣
:እቅድ ሀሣባቸዉን ተካፈል፣
:ዓላማህን አትደብቃቸው፣
:የሥጋ ዘመዶቻቸዉን ቀጥል፣
:ወዳጆቻቸን አክብርላቸው፣
:ጉዞ ስትወጣ ንገራቸው፣
:የሚወዱትን ዉደድላቸው፣
:እርግማናቸዉን ተጠንቀቅ፣
:እነርሱን ከማስከፋት ፈፅሞ እራቅ፣
:ነገሮችን ቀስ ብለህ አስረዳቸው፣
:በሚገባቸዉ ሁኔታና ቋንቋ ንገራቸው፣
:ዱዓኣቸዉን ፈልግ፣
:ከምርቃታቸው ተሽቀዳደም፣
:ለወላጆችህ  ‘ ጌታዬ ሆይ ! በህፃንነቴ እንዳሳደጉኝ ሁሉ እዘንላቸው ’ የዘወትር ዱዓእህ ይሁን ።

★ አላህ ሆይ ! ጀነት በእግሮቿ ስር እንዳደረከው መኖሪያዋም ጀነት አድርገው ። 

አሚንንን  አላሁመ አሚንንን

ولله أعلم
https://t.me/ALHidayaTv
322 viewsatwehid dawet arsul!!!, 19:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ