Get Mystery Box with random crypto!

ሐበሻ ጣዕም/Habesha Taem

የቴሌግራም ቻናል አርማ habshataem — ሐበሻ ጣዕም/Habesha Taem
የቴሌግራም ቻናል አርማ habshataem — ሐበሻ ጣዕም/Habesha Taem
የሰርጥ አድራሻ: @habshataem
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 163
የሰርጥ መግለጫ

ሐበሻ ጣዕም ስለ ሁሉም የሚያወራ ስለ ሁሉም የሚያነሳሳ የመዝናኛ ዝግጅት ነው።
የfacebook አድራሻችን👇👇👇
https://www.facebook.com/habeshatae?mibextid=ZbWKwL
በቀጥታ ለማድመጥ👇👇👇
http://www.aradafm.com
@DjFortink
@Daniyenatu

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-07-09 12:35:58
#ዜማ_ቢት
በ አባይ ቲቪ
ቅዳሜ በ12ሰአት ልዩ የበአል ቁይታ ከሙነሺድ አሊአሚን ጋር
24 views09:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 19:51:18
ለመላው እስልምናን ተከታዮች እንኳን ኢድ አል አድሀ/አረፋ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ለማለት እንወዳለን::

( የሐበሻ ጣዕም አዘጋጆች ዲጄ ፎርቲን ኬ እና ዳኒ )
30 views16:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 23:28:48
29 views20:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 23:25:10 አሐዱ ባንክ

'አንድ ቅርንጫፍ ለአንድ ልጅ' የበጎ ድጋፍ ፕሮግራም ይዞ መጥቷል

አሐዱ ባንክ ሐምሌ 9 ቀን 2014 ዓ.ም በይፋ ስራ የሚጀምር መሆኑን ገለፀ

አሐዱ ባንክ በ7 አደራጅ ኮሚቴ አባላት ታህሳስ 30 ቀን 2012 ዓ.ም. የተጠነሰሰውንና 10 ሺህ
የሚደርሱ ባለአክሲዮኖችን ያሰባሰበውን በ564 ሚሊዮን የተከፈለ ካፒታል እና በ702 ሚሊዮን የተፈረመ
ካፒታል በታላቅ ዉጥን የተዋቀረዉን የአሐዱ ባንክ ስራ መጀመሩን አስመልክቶ ዛሬ በማሪዮት ኤክስኪዩቲቭ
አፖርትመንት ሆቴል ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጠ

***
የመግለጫው ሙሉ ቃል

አሐዱ ባንክ ክፍተቶች በማስተዋል በዘመኑ
ቴክኖሎጂ የተደራጀና በተደራሽነት በኩል በአገልግሎት
አሰጣጥ፥ በቴክኖሎጂ አጠቃቀም፥ የተሻለ የፋይናንስ አገልግሎት ለመስጠት ዝግጅቱን በማጠናቀቅ ሐምሌ 9
2014 ዓ.ም. በይፋ ስራ የሚጀምር መሆኑን ስንገልጽ በታላቅ ደስታ ነው።

አሐዱ ባንክ እንደ ስሙ፤ ባለዉ የስራ መርሕ መሰረት “ምስጢሩ አንድ ብሎ መጀመሩ' የሚለዉን ለማሳየት
በዋናዉ መስሪያ ቤት ባደራጀዉ ዘመናዊ ቅርንጫፍ ስራዉን በይፋ የሚጀምር ሲሆን ከምርቃቱ እለት አንስቶ
በተከታታይ ቀናት በአዲስ አበባ እና ክልል ከተሞች ዝግጁ የሚያደርጋቸዉን ቅርንጫፎች በመክፈት አጠቃላይ
የቅርንጫፍ ብዛቱን እስከ መስከረም 30 2015 ድረስ 50 የሚያደርስ ይሆናል።

በተጨማሪም ብዛት ያላቸዉ
የባንክ አገልግሎት ወኪሎችንም ይዞ ወደ ገበያ የሚገባ ይሆናል።

ባንካችንን ልዩ ከሚያደርጉት መገለጫዎች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፤

● በየዓመቱ ከሚያቀርበዉ ብድር እስከ 15% ያህሉን የፋይናንስ አቅርቦት ለሥራ ፈጣሪዎችና ለአነስተኛ
ኢንተርፕራይዞች የሚያመቻች ሲሆን ለተመረጡ ሥራ ፈጣሪዎች በየቅርንጫፎቻችን የምርት ማሳያ
ቦታ ለማጋራት የሚያስችል ሁኔታም እናዘጋጃለን፤

● አጠቃላይ አገልግሎቱን ተደራሽ ለማድረግ በስፋት በአገሪቱ ዉስጥ ህዝባችን የወኪል ባንh
አገልግሎትን በተለያዩ የዲጂታል አማራጮች ተደራሽ ማድረግ የሚያስችል አጋርነትና ኢደረጃጀትፈጥረናል፤

● ከተለመደዉ በሠራተኛ ከታገዘ የቅርንጫፍ አገልግሎት በተጓዳኝ ደንበኞች በራሳቸዉ የዲጂታል
አገልግሎት የሚያገኙበት የቅርንጫፍ ዉስጥ አገልግሎት አደረጃጀት (experience area)
አመቻችተናል፤

● የገጠር የባንክ አገልግሎትን ለአርሶና አርብቶ አደሮች፣ የገበሬ ማህበራት እንዲሁም በግብርና እሴት
ሰነሰለት ለሚሳተፉ ተዋናዮች በስፋት ለማዳረስ ተዘጋጅተናል፤

● የብድር፥ የአለም አቀፍ ባንክ አገልግሎት፥ እና ማንኛዉም የአገር ዉስጥና የዉጭ ሀዋላ እና ክፍያዎች
ወረቀት አልባ (ዲጂታል) በሆነ መልኩ እንዲከናወን አስቻይ የሆነ መተግበርያ (ፕላትፎረም)
ተዘጋጅቷል፤

● የባንኩ ደንበኞች ካሉበትና ባሉበት ቦታዎች ሆነዉ ራሳቸዉን የባንኩ ደንበኛ ማድረግ የሚችሉበትን
አሰራር ይዘን መጥተናል፤

● የዉስጥ አሰራሩን ሙሉ በሙሉ ወረቀት አልባና ዘመናዊ አድርገናል፤
እንዲሁም
ሁሉም የባንኩን አሰራሮች በቴክኖሎጂ ላይ የተመሠረቱ እና የተሳለጡ እንዲሆኑ ማድረጋችን
ተጠቃሾች ናቸዉ።

ማህበራዊ ግዴታችንን ከመወጣት አንፃር፤
ባንካችን ከተቋቋመት ተልዕኮ ጋር የተጣጣሙ ዕሴቶችን ከመኖር አኳያ ከምስረታው ጀምሮ በተለያዩ ማኅበራዊ
ግዴታን ለመወጣት የሚጋብዙ ዝግጅቶች ላይ ተሳትፎ እያደረገ መምጣቱ ይታወሳል።

በቀጣይም ባንኩ
በቋሚነት ወላጅ አልባ የሆኑ ህጻናትን በማደጎ በመረከብ ለማሳደግ፥ አልባሽ አጉራሽ ለሌላቸዉን
ቤተሰቦች የስራ እድል ለመፍጠር፥ እንዲሁም በአገር ታሪክ፥ ባህል እና ቅርስ ጥበቃ ላይ የሚሰሩ አካላት
ጋር በትብብር የሚሰራ ይሆናል።

ሙሉ ዝግጅቱን አጠናቆ አገልግሎት ወደ መስጠት ለመግባት በተዘጋጀበት ዋዜማም ይህንኑ አጠናክሮ
በመቀጠልና ከወዲሁ የተለያዩ ቅድመ ዝግጅቶችን በማድረግ

1ኛ. ሐምሌ 2 ቀን 2014 ዓ.ም. የአሐዱ ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት፥ የማኔጅመንት አባላት እና መላው
ሠራተኞቹ የሰዉ ልጅን ክቡር ህይወት ለማስቀጠል ይረዳ ዘንድ ዉድ ከሆነዉን ስጦታ ለመጀመር
በማሰብ የደም ልገሳ መርሐ ግብር ያካሂዳሉ።

2ኛ. ሐምሌ 4 ቀን 2014 ዓ.ም. በተስፋ አዲስ የካንሰር ሕሙማን መርጃ ማዕከል በመገኘት ከተለያዩ የሀገሪቱ
ክፍሎች በመምጣትና ዉድ የሆነች ህይወታቸዉን ለማትረፍ የህክምና ወረፋ በመጠባበቅ ላይ ላሉ
የካንሰር ህሙማን የገንዘብ ስጦታ ይበረከታል።

3ኛ በመቀጠልም ሐምሌ 5 ቀን 2014 ዓ.ም. በጌርጌሴኖን የአዕምሮ ሕሙማን መርጃ ማዕከል እና በአሥመሮም
ጎዳና ሻወር በመገኘት የምሣ ማብላት መርሐ ግብር ያካሄዳል።

4ኛ. ባንካችን የአገር ቅርስ እና እሴቶችን ተንከባክቦና ጠብቆ ማስቀጠል የሁሉም የሕብረተሰብ ክፍል ኃላፊነት
ነዉ ብሎ ያምናል።

ይህንንም ታሳቢ በማድረግ ሐምሌ 6 ቀን 2014 ዓ.ም. የአገራችን ትልቅ ሃብት
የሆነውን የቅዱስ ላሊበላ ገዳም የእድሳት ስራ ለመደገፍ የብር 500,000.00 ድጋፍ የሚከናወን ይሆናል።

5ኛ. በመጨረሻም ሐምሌ 7 ቀን 2014 ዓ.ም. በስለእናት የበጎ አድራጎት ድርጅት በመገኘት በማዕከሉ ላሉና
እገዛ እየተደረገላቸዉ የሚገኙ ሕጻናትን የመጎብኘትና የገንዘብ ስጦታ የማበርከት መርሐ ግብር
የሚከናወን ይሆናል።

ባንካችን በዚህ ድጋፍ ሳይገደብም 'አንድ ቅርንጫፍ ለአንድ ልጅ' በሚል እሳቤ
ባንኩ በሚከፍታቸዉ ቅርንጫፎች ቁጥር ልክ ድጋፍ እና እገዛ ለሚያስፈልጋቸዉ ልጆች ዓመታዊ
ወጪያቸዉን ለመሸፈን መወሰኑን ስንገልጽ ከታላቅ ደስታ ጋር ነዉ ።

በዚህም የማኅበረሰብ አጋርነቱንና "ከብዙዎች ለብዙዎች" ብሎ የተነሳበትን ዓላማ በተግባር ለማሳየት
እንቅስቃሴውን መጀመሩን ያበስራል።

ሐበሻ ጣዕም
29 views20:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 18:08:30
"አንባቢዎች መሪዎች ናቸው!!!!!"

ሰኔ 30 የንባብ ቀን እየተከበረ ነው።

የኢትዮጵያ ደራስያን ማህበር በየአመቱ ሰኔ 30 ቀን በኢትዮጵያ የንባብ ቀን እንዲሆን በማቀድ የጀመረው እንቅስቃሴ አመታዊ መርሀ ግብር እየተካሄደ ነው።

በአብርሆት ቤተ መጻህፍት እየተካሄደ ባለው በዚህ መርሀ ግብር ላይ ከአራት አመቱ ታዳጊ አንባቢ ናኦል ጀምሮ የተለያዩ ደራስያን እና ጠንካራ የንባብ ልማድ ያላቸው እንግዶች ስለ ንባብ ጥቅም ልምዳቸውን እያካፈሉ ይገኛሉ።

"አንባቢዎች መሪዎች ናቸው!!!" በሚል ሀይለ መልእክት ስር እየተከበረ በሚገኘው በዚህ ዝግጅት ላይ እንደተነገረው የኢትዮጵያ ደራስያን ማህበር ሀገር አቀፍ ንባብ ተገቢው ትኩረት እንዲያገኝ በዚህ ክረምት ሰፊ ስራዎች ይሰራሉ ተብሏል።
37 views15:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-05 15:18:31
ሞዴልና ተዋናይ ሀናን ታሪክ ይታሽ ሞቢሊያ የተሰኘ የቱርክ ኩባንያ ወኪል ከሆነው ቡሩል ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግል ኩባንያ የብራንድ አምባሳደር በመሆን በዛሬው ዕለት ፊርማዋን አኖረች።

ቡሩል ትሬዲንግ እ.ኤ.አ በ2016 የተመሰረተ አስመጪና ላኪ ኩባንያ ሲሆን በአሁኑ ጊዜ ለሶስት የቱርክ ኩባንያዎች የምስራቅ አፍሪካ ገበያ ወኪል በመሆን በመስራት ላይ ይገኛል።

ኩባንያው "ኢንጂ ፈርኒቸር" የሚል የብራንድ ስም በመያዝ ከተለመደው ወጣ ያሉ ፣ ቅንጡ፣ ውብና ማራኪ ፈርኒቸሮችን በልዩ ትዕዛዝ እንደሚያስመጣ ወ/ሮ እንቁጣጣሽ ሀይሌ በዛሬው ዕለት በሀያት ሬጀንሲ ሆቴል በተሰጠው መግለጫ ጠቅሰዋል።

ኩባንያው በደንበኞቹ ጥያቄ መሰረት የሆቴልና አፓርትመንት ቅንጡ ፈርኒቸሮችን በማስመጣት በኬንያ፣ በደቡብ ሱዳን፣ በናይጄሪያ፣ በታንዛኒያ ለሚገኙ ደንበኞቹ ሲያቀርብ መቆየቱን ጠቅሰው በመስከረም 2022 በናይሮቢ የመጀመሪያውን ሾው ሩም እንደሚከፍት ወ/ሮ እንቁጣጣሽ ጠቅሰዋል።

አርቲስት ሀናን ኩባንያው በሀገር ውስጥና በሌሎች ሀገራት ለሚያደርጋቸው እንቅስቃሴዎች በብራንድ አምባሳድነት ለመስራት የፈረመች ሲሆን ክፍያውን በተመለከተ ከፍተኛ ነው በሚል ቁጥሩን ከመጥቀስ ተቆጥበዋል።
አርቲስት ሀናን በብራንድ አምባሳደርነት በመመረጥዋ መደስቷን ገልፃለች።
54 views12:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 22:08:45
ድምጻዊ አብርሐም በላይነህ (ሻላዬ) ከእስር ተፈታ!

ከ3ኛ ፎቅ ላይ ወድቃ ህይወቷ ካለፈው ዶ/ር ቤዛ ተዋበ ጋር ተያይዞ ከአንድ ወር በላይ ምርመራ ሲደረግበት የቆየው ድምጻዊ አብርሐም በላይነህ (ሻላዬ) በዛሬው ዕለት ከእስር ተፈቷል።

የፖሊስ የምርመራ መዝገብን ሲመለከት የቆየው የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት አራዳ ምድብ 2ኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ባሳለፍነው ሀሙስ በነበረ ቀጠሮ የፖሊስ የምርመራ መዝገብ በመጠናቀቁ የጊዜ ቀጠሮ መዝገቡ እንዲዘጋ ትዕዛዝ መስጠቱ ይታወሳል።

በዕለቱ ከሰዓት በኋላ ጠበቃው ገመቹ መረራ ለፍርድ ቤቱ 1ኛ የፍትሐብሄር ልዩ ልዩ ችሎት አካልን ነጻ የማውጣት መብት ጥያቄ አቅርበዋል። ነገር ግን 10:00 ላይ የችሎቱ ዳኛው ባለመኖራቸው ምክንያት ጥያቄው ሳይታይ አድሯል።

በይደር አርብ ዕለት ለችሎቱ ማመልከቻው ቀርቦ የታየ ቢሆንም፤ ፍርድ ቤቱ መርምሮ ብይን ለመስጠት ለዛሬ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቶ ነበር። በዚህ መሰረት ዛሬ በነበረ ቀጠሮ ችሎቱ የድምጻዊ አብርሐም በላይነህን አካልን ነጻ የማውጣት አቤቱታ ተመልክቶ ድምጻዊ አብርሐም በላይነህ በነጻ ከእስር እንዲፈታ ትዕዛዝ መስጠቱን ጋዜጠኛ ታሪክ አዱኛ ዘግባለች። አብርሐም በላይነህ ከእስር ተፈቶ ከቤተሰቡ ጋር መቀላቀሉን ጠበቃው ገልጸዋል።

bbc
55 views19:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 19:32:48
#45 አንጋፋ እና ወጣት የኪነጥበብ ባለሞያዎች ሊሸለሙ ነው!

የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ክብር ለጥበብ! በሚል ርእስ ዘንድሮ ለሁለተኛ ጊዜ በሚያደረገው የእውቅና እና የሽልማት ፕሮግራም በስነ-ጽሁፍ፣ሙዚቃ፣ውዝዋዜ፣ሰርከስ፣ቴአትር፣ሲኒማና በሌሎች አራት ዘርፎች የሚሰጥ መሆኑን ገልጽዋል፡፡ ለሽልማቱ መስፈርቶቹን ያሟሉ 45 አንጋፋ እና ወጣት የኪነጥበብ ባለሞያዎችም እንደተመረጡም ተነግርዋል፡፡

የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ባለሞያዎችን በህይወት ሳሉ ማመስገንና የእውቅና ሽልማት መስጠት ተተኪ ወጣቶችን የሚያበረታታ ነው ብሎታል፡፡

ሽልማቱ የፊታችን ረቡዕ ሰኔ 29/2014 ዓ.ም የሚሰጥ ሲሆን የዘንድሮው ለየት የሚያደርገው የክልሎችን የኪነጥበብ ባለሞያዎች የሚያካትት መሆኑን ነው የባህልና ስፖርት ሚኒስትር በሰተው መግለጫው ያስታወቀው።
50 views16:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-30 10:58:41
እውቁ አሜሪካዊ ድምጻዊ አር ኬሊ በጾታዊ ጥቃት ወንጀል የ30 ዓመት እስር ተፈረደበት

ታዋቂው የአሜረካዊ የአር ኤንድ ቢ አቀንቃኝ አር ኬሊ በአሜሪካ ፍርድ ቤት የ30 ዓመት እስር እንደተፈረደበት ተነግሯል።

የ55 ዓመቱ ሙዚቀኛ ባሳለፍነው መስከረም ወር ላይ ነበር በወሲብ ንግድ፣ በህፃናት ላይ ጾታዊ ጥቃት፣ በአፈና እና ሌሎች ከወሲብ ጋር በተያያዙ ወንጀሎች ተከሶ ፍርድ ቤት የቀረበው።

በዚህም ፍርድ ቤቱ ትክክለኛ ስሙ ሮበርት ሲልቪስተር ኬሊ በተባለው ድምጻ ላይ የ30 ዓመት እስር የፈረ ሲሆን፤ ይግባኝ ማለት መብት እንዳለውም አስታውቋል።
57 views07:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-28 10:23:01
አንጋፋው ፀሐፌ ተውኔት፣ አዘጋጅ እና ተዋናይ ሰለሞን አለሙ ፈለቀ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።

በ"አብዬ ዘርጋው" የሬዲዮ ድራማ ይበልጥ የሚታወቀው ሰለሞን አለሙ በ5 ቋንቋዎች ከ500 በላይ የሬዲዮ ድራማዎችን፣ የመድረክ ቴአትሮችን እና መነባንቦችን ሰርቷል።ለአብነትም ከዳንኪራው ጀርባ፣ ፍራሽ ሜዳ፣ ገመዱ እና አዙሪትን የመሳሱሉ ተወዳጅ ሥራዎች አበርክቷል።

በኢትዮጵያ ሬዲዮ ታሪክ በተለይ ከ1975 እስከ 1980 ገናና ሥራዎችን ያበረከተበት ወርቃማ ዘመኑ ነበር።እንደኢብኮ ዘገባ ሰለሞን በቅርቡ ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ ሌሊቱን ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
55 views07:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ