2022-06-28 07:20:24
ከቀናቶች ሁሉ በላጭ በሆኑት ቀናቶች
በላጭ የሆነ ዒባዳ!
ዙልሒጃ ወር አስሩ የመጀመሪያ ቀናት ከቀናቶች ሁሉ በላጭ ናቸው፡፡
በነዚሁ ቀናት የሚሰሩ የአምልኮ ተግባራት (ዒባዳዎች) በሌሎች ቀናት
ከሚሰሩት ሁሉ በላጭ መሆናቸውን ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) ተናግረዋል፡፡ አቅሙ
ለቻለ ሰው ሐጅና ዑምራ ማድረግ በነዚህ ቀናት ውስጥ ሊሰሩ ከሚችሉ
የአምልኮ ተግባራት ሁሉ በላጩ ነው፡፡ ጾም መጾም፣ አላህን በብዛት
ማወደስ፣ ተክቢራ ማለት፣ ቁርአንን ማንበብ፣ በጥቅሉ መልካም የተባሉ
ተግባራትን ሁሉ በነዚህ ቀናት መፈጸም እጥፍ ድርብ ምንዳ ያስገኛል፡፡
ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) ዘጠነኛውን ቀን መጾምን
አስመልክተው ‹‹ያለፈውንና የሚመጣውን አመት ወንጀል ያብሳል››
ብለዋል፡፡ በላጭ የሆኑ ዒባዳዎችን መርጦ በነዚህ በላጭ በሆኑ ቀናት
መፈጸም ብልህነት ነው፡፡
‹‹ከአምልኮ ተግባራት ሁሉ የትኛው ይበልጣል?›› የሚለውን ጥያቄ
አስመልክቶ የተለያዩ አመለካከቶች ቢኖሩም አብዛኛዎቹ ዑለማዎች
ወቅቱ የሚጠይቀውን አምልኮ ከመፈጸም የላቀ በላጭ የአምልኮ
ተግባር እንደሌለ ይስማማሉ፡፡ አዛን ሲል በላጩ አምልኮ ሰላት መስገድ
ነው፡፡ ቁርአን እያነበበ ለነበረ ሰው ወላጆቹ ቢጠሩት ቁርአኑን ከመቀጠል
ይልቅ ለወላጆቹ ምላሽ መስጠት በላጭ የአምልኮ ተግባር ነው፡፡ አላህን
እያወደሰ ለነበረ ሰው ተጣልተው የነበሩ ሰዎችን እንዲያስታርቅ
ቢጠየቅ ማስታረቅ ለሱ በላጭ ኢባዳ ነው፡፡ ‹‹ይበልጥ አንገብጋቢ የሆኑ
አላህ የሚወዳቸው ተግባራትን መፈጸም ከአምልኮ ተግባራት ሁሉ
በላጭ አምልኮ ነው››
ታዲያ ለነዚህ መልካም ቀናቶች ማነው ዝግጅት ያደረገው?
ይህ አሁን ያለንበት ወር ሙሉ ሚሆን ከሆነ የዙል ሒጃ ወር ሀሙስ ይጀምራል
ሌሎችም ቀናቶችን በፆም...በተለያየ ኢባዳ እንዲያሳልፉ ሼር በማድረግ አስታውሷቸው።
እዚህ ይቀላቀሉ
https://t.me/tghamzs
445 viewsedited 04:20