Get Mystery Box with random crypto!

አል ሂዳያ የየቲሞች መርጃና በጎ አድራጎት ጀማአ 0993632424//0703136300አዲስ አበባ

የቴሌግራም ቻናል አርማ alhidayatv — አል ሂዳያ የየቲሞች መርጃና በጎ አድራጎት ጀማአ 0993632424//0703136300አዲስ አበባ
የቴሌግራም ቻናል አርማ alhidayatv — አል ሂዳያ የየቲሞች መርጃና በጎ አድራጎት ጀማአ 0993632424//0703136300አዲስ አበባ
የሰርጥ አድራሻ: @alhidayatv
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 15.07K
የሰርጥ መግለጫ

ኑ ተባብረን ባለን አቅም የቲሞችንና የተቸገሩ ሙስሊም ወገኖቻችንን እንርዳ
በልብስ👕👖 በገዘብ በአስዜዛ በጉልበት በሀሳብና
በተለያዩ በቤት ቁሳቁሶች መርዳት ትችላላቹ
ንግድ ባንክ
1000375043298
ሪድዋን ሙሀመድ
አባል መሆን ለምትፈልጉ
ለበለጠ መረጃ
251993632424
ወይም የቢሮ ቁጥር
251703136300
ወይም በኢቦክስ
@RidAmirsab
ሰደቃ ወጀልን ታብሳለች ረሱል (ﷺ)

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2022-12-05 21:32:18
274 viewsRidwan Muhamed, 18:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-05 21:32:16
213 viewsRidwan Muhamed, 18:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-05 21:31:52
በአሏህ ፈቃድ ሆኖ ዛሬ መንገድ ላይ በተለያዩ ምክኒያት ከቤታቸዉ ተፈናቅለዉ ለመጡ ወገኖቻችን ሩዝ መኮረኒ ፓስታና ለወጥ የሚሆን ምስር አምስት አምስት ኪሎ በማድረግ ለመስጠት ችለናል

ብዙም ባይዳረስልንም አልሀምዱ ሊላህ ለጊዜዉ ራሀባቸዉን የምታስታግስላቸዉ ትንሽ ነገር ሰተናቸዋል


ኢንሻ አሏህ በቀጣይ አሏህ ካሳካዉና በአፊያና በጤና አሏህ ካቆየን በጦርነቱ ምክኒያት ለተሰደዱ ወገኖቻችንን ቦታዉ ድረስ በመሄድ እርዳታ ለመስጠት ዝግጅት ላይ እንገኛለን

ተሳተፉ ያጀማአ የተራበን አብሉ የተጠማን አጠጡ የታረዘን አልብሱ የተሰደደን መጠለያ ስጡ

አል ሂዳያዎች ቀጥሉበት
https://t.me/ALhidayawoch
162 viewsRidwan Muhamed, 18:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-05 21:31:52
99 viewsRidwan Muhamed, 18:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-03 21:35:57
አሰላሙዓለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱ

በምስሉ ላይ ምትመለከቱትን ወረቀት ከአንድ ወጣት ወንድማችን ነው ለሶስተኛ ግዜ  ኮፒ አድርጎ የሰጠኝ

አንዳንድ እህትና ወንድሞች ባስገቡልኝ ብር ከ2,000 በላይ ወረቀቶችን ለመበተን ሞክሪያለሁ ይሄ ማለት የእቅዳችንን 1% ላይ ነው ያለነው።
ምክንያቱም እቅዳችን በየ ሀገሮች ማዳረስ ነው ግን እስካሁን ከ3 በላይ ትምህርት ቤት አልበተንም።

ፁሁፉ ደግሞ ለሙስሊሞች ብቻ አይደለም ካፊሮችም እየተማሩበት ነው። አይታወቅም የሂዳያ ሰበብም ሊሆናቸው ይችላል ምክንያቱም ይሄ ፁሁፍ እስልምና ምን ያክል ለሰው ሂወት እንደሚጨነቅ ማሳያ ነው።

በተቃራኒው ደግሞ ብዙ ሚባሉ እህት ወንድሞቻችን እምነታቸውን እየቀየሩ ይገኛሉ በዚህ ሃራም ፍቅር ሰበብ። ቀላል የሆነ መዘዝ ያለው እንዳይመስላችሁ።

እና ለማገዝ ሃቅሙ ያላችሁ እህት ወንድሞች ዝም አንበል የሁላችንም ግዴታ ነው።
በገንዘባችን እንጠየቅበታለን።

ለአንድ ትምህርት ቤት ከ450 በላይ ወረቀት ነው ሚያስፈልገው።

የስልካችን ስክሪን ቢሰበር በምን ያክል ፍጥነት ከ5ሺ በላይ አውጥተን እንደምናሰራው ግልፅ ነው።
ግን የአላህ ዲን ለመርዳት ሲሆን ለምን ይሆን የሚከብደን።?

የኔም ሀላፊነት ነው ማገዝ እፈልጋለሁ የምትሉ በውስጥ መስመር አናግሩኝ
@jezakellah

ስልክ 0910509090

የቴሌግራም ቻናል

https://t.me/latekrebu_zina
https://t.me/latekrebu_zina
https://t.me/latekrebu_zina
300 viewsእንደ አበባ ፈክተሽ ወንድ ከምታፈዢ ሂጃብሽን(ኒቃብሽን) ለብሰሽ ጌታሽን ተገዢ!!!, 18:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-03 20:38:06 ​​​​╔═══❖•ೋ° °ೋ•❖═══╗
                     "ሶብር"
╚═══❖•ೋ° °ೋ•❖═══╝

ኻሊቁ ተናግሯል በቅዱስ ቁርአኑ፤
ሰዎች እስካመኑ እንደሚፈተኑ።

ይህንን ያወቀ ሙእሚን የሆነማ፤
ችግር ሲደርስበት ሲያገኘው ነዳማ፤
ዛፏን ተንጠልጥሎ የሶብርን ማማ፤
ስኬትን ያተርፋል በየውመል ቂያማ።

ትዕግስት በብዙ ስለተቸራቸው፤
ስለ ሶብርማ መረዳት ሚያመቸው፤
ድንቅ ምሳሌያችን አዩብኮ ናቸው።

ሲራቸው ሲሰማ እጅግ ያስገርማል፤
የአዩብን ትዕግስት ማን ችሎ ይደግማል።

ይኖር ነበር አዩብ በፀጋ ተከቦ፤
በቤተሰብ ብዛት ደምቆና ተውቦ።

ይታወቅ ነበረ በለጋስነቱ፤
ጎልቶ የወጣ ነው የሱ ደግነቱ።

በአንድ ለሊት ውስጥ ፈተናው ጀመረ፤
የድሎቱ ህይወት አቅጣጫ ቀየረ።

መላ ልጆቹና ያፈራው ንብረቱ፤
ሁሉ ነገር ጠፋ ስትቀር ባለቤቱ።

ፈተናው አልቆመም በልጅ በንብረቱ፤
በሽታ ላይ ወድቆ ቆስሎ ሰውነቱ፤
መራገፍ ጀመረ ስጋው ከአካላቱ።

ሰውነቱ ላይም ያብጥበት ጀመረ፤
አብጦ ሲፈነዳም ይመግል ነበረ።

ሽታው ከባድ ነበር ለተጠጋው ሁሉ፤
ተላላፊ በሽታ ይሆናል እያሉ፤
ያገላቸው ጀመር ሰውም እንዳመሉ።

የከተማው ህዝብም አስቦ አሰላስሎ፤
ውሳኔን ወሰነ እንዲሆን በቶሎ፤
እሩቅ ተራራ ላይ አዩብ ይጣል ብሎ።

ይሄ ሁሉ ሲሆን ሁሉም ሲሆን መና፤
ትከታተል ነበር ሚስቱ በጥሞና።

ልታገለው ቀርቶ ታመመኮ ብላ፤
ውላ እንኳን አታውቅም ከሱ ተነጥላ።

አላህ ሰጠውኮ ይቺን ሷሊህ ጀግና፤
ጥሩ ዘዋጅ ሁሉ ለጥሩ ነውና።

ቀን በየከተማው ወርዳ በየቦታው፤
ተቀጥራ ሰርታ ነው ሁሌ ምታበላው።

ሲመሽም ለአዩብ ምግብ ትገዛና፤
ታበላው ነበረ ምንም ሳታቅማማ።

የበሽታው ዘመን ስቃዩም በረታ፤
አዩብም ሰልችቶት በማማረር ፋንታ፤
ለጌታው ያደርሳል የሀምድ ጋጋታ።

አመታት ነጎደ እንዲሁ ከነፈ፤
ሰባት አመታትን በስቃይ አለፈ፤
ይሄኔ ግን ሚስቱ ስቃይዋ ሲበዛ፤
ትለውም ጀመረች እባክህ ዱዓ አብዛ።

ምነው ምን ሆነሽ ነው ብሎ ሲጠይቃት፤
አለችው አዩብን አይን አይኗን እያያት፤
አለፈኮ አዩብ 7ቱ አመታት፤
እንዲሁ በስቃይ ሆነን በእንግልታት።

አዩብም በቶሎ ቀበል አረገና፤
በጥያቄዋ ላይ ጠየቀ እንደገና።

ሁቢ እስቲ አስታውሺ ስንት አመት ኖርንበት፤
የአላህን ድሎት እያጣጣምንበት።

አለችው አዩብን 70 አመት ደላን፤
በምትኩ ደግሞ 7አመት ለፋን።

አዩብም መለሰ ምንም ሳያዘግም፤
70አመት ደልቶኝ ኖርያለው በአለም፤
7አመት ቢያመኝ እንዴት አልሶብርም?

አቤት ትዕግስታቸው የነአዩብማ፤
እንጨርሰው ብንል ይጠባል ከሊማ።

ከዕለታት አንድ ቀን እንዲህ እየኖረ፤
የራህማን አፊያ ቤቱን ቆረቆረ።

ከዛ ሁሉ ጭንቀት መከራ ቡኋላ፤
የነ አዩቤ ቤት በደስታ ተሞላ።

ልጆቹ ንብረቱ መልሰው መጡለት፤
የትዕግስቱ ውጤት ደምቆ አበራለት።

እስቲ ቆይ ንገሩኝ አሏህ የፈተነው፤
ስለጨከነበት ወይ ስለጠላው ነው?

አይደለም ሀቂቃ ስለወደደው ነው፤
አማኝ የሆነ ሰው ይፈተናል ያለው።

እንዳይረዝምባቹ ቋጭቼው ነው እንጂ፤
የአዩብ ሶብርማ አያልቅም በእጂ።

ችግር ሲደርስበት ሶብሮ ያለፈ፤
በዱንያም በአኼራም እሱ አተረፈ።

እኛም ተቸግረን ዛሬ ብንፈተን፤
ወይም አፊያ አተን ደስታችን ቢበተን፤
ዛሬ አመስግነን በሶብር ካለፍን፤
በጀነት ተክሰን ነገ ድሎት አለን።
            ‘ኢንሻአሏህ’
              
454 viewsእንደ አበባ ፈክተሽ ወንድ ከምታፈዢ ሂጃብሽን(ኒቃብሽን) ለብሰሽ ጌታሽን ተገዢ!!!, 17:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-03 20:00:00 ግራ እንዳትጋባ፦ የዲን ባለቤቷን አግባ


ታዋቂው የዲን ሊቅ፣ የታሪክ ምሁርና የኢልም፣ የሲድቅ፣ የፊቅህ ባለቤት የሆነው ኢስሀቅ ቢን ራሀወይህ፦ አንዲት ባሏ የሞተባት ሴት አገባ። የዚህች ሴት ባል ከመሞቱ በፊት የኢማሙ ሻፍእይና የሌሎች ኡለማዎች የኪታብ ክምች ነበረው። ሰዎች ለኢስሀቅ ሌሎችን ትተህ ይህችን ሴት እንዴት መረጥክ ብለው ጠየቁት። እሱም፦ ለኪታቦቹ ብዬ ነው። ሴት ልጅ ለኪታቧ ሲባል ትገባለች አላቸው።

(السير للذهبي ص 70/ج 10)

የኢልምና የዲን ጥፍጥና ያወቀ ሰው ከምንም በላይ ዲን ያላትን ይመርጣል። በተለይ በዚህ ዘመን በኢማን በተቅዋ የተገነባች ሴት ከምንም በላይ ወሳኝ ነው። የአብዘሀኛው የትዳር ችግር መንስኤው መሰረቱ ዲን ባማከለ መልኩ ባለመገንባቱ የሚፈጠር ነው።

➲ አንዳንዱ ግን ያሳዝናል። የትዳር አጋር ሳይሆን በግ ይመርጥ ይመስል የሌለ።መስፈርት በማስቀመጥ ወፍራም ቀጭን፣ ጥቁር ነጭ፣ አጭር ረጅም እያለ የዲን ባለቤቷን ትቶ አስተምራታለሁ፣ እቀይራታለሁ በሚል ሂሳብ መልክ፣ ገፅታ፣ ሀብትና ዘር በማየት ዲን የሌላትን ሚመርጥ በዝቷል። እቀይራለሁ ብለው አግብተው ተቀየረው የቀሩ ስንቶች እንዳሉ አላወቀም።

እውነተኛ ደስታ፣ የማያልቅ ሀብት፣ ዘላቂ እፎይታና በረካ ያለው ከዲን ባለቤቷ ጋር ሲሆን ብቻ ነው። የፈለገ መልክ ቢትረፈረፈ፣ ሀብት ቢሞላ ዲን ከሌለ ሁሌም ስቃይ፣ ጭቅጭና መከራ ነው። እንዲህ አይነት ትዳር እድሜውም አጭር ነው።

ሀብት አይተህ ካገባህ አላቂና ጠፊ ነውና ሀብቱ ሲያልቅ የትዳርህ ጉዳይ ያበቃል። መልክ አይተህም ካገባህ ሁለት ሶስት ስትወልድ ይረግፋልና የዛኔ የትዳርህ ማገር ይፈርሳል። ተቅዋ፣ ሀያእ፣ ኢማንና ዲኗን አይተህ ካገባህ ግን የማይጠፋና የማይፈርስ፣ ሁሌም ከሷ ጋር የሚቀር ነውና ትዳርህ ያማረና የሰመረ ሆኖ ይቀጥላል።
467 viewsእንደ አበባ ፈክተሽ ወንድ ከምታፈዢ ሂጃብሽን(ኒቃብሽን) ለብሰሽ ጌታሽን ተገዢ!!!, 17:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-03 19:51:41
ሰዉ አሏህ የሰጠዉን የተለያየ አቅም ተጠቅሞ የስሜት ህዋሀሶችን በማፅዳት አሏህ ወደሚፈልገዉ አቅጣጫ በመጓዝ ሲተጋ የነፍሱን አጥር መሻገር ይችላል። አምስቱ የስሜት ህዋሀሳት አሏህ ወደሚፈልገዉ አቅጣጫ ሲገቡ በሂደቱ ቀልብ ትነፃለች ነፍስ ትጠራለች። ቀልብ እዉነታዎችን ሁሉ ወደ መገለጥ ደረጃ ትደርሳለች። አሏህ ሱብሀነሁ ወታአላ እንዲህ በማለት የጠቀሳትን ሩህ ከሁነተ አለም የወጣች አል ነፍስ አል ሱልጣንያ ናት።

فَإِذَا سَوَّيْتُهُ وَنَفَخْتُ فِيهِ مِن رُّوحِي فَقَعُوا لَهُ سَاجِدِينَ

(ፍጥረቱን) ባስተካከልኩትና በውስጡ ከመንፈሴ በነፋሁበትም ጊዜ ለእርሱ ሰጋጆች ኾናችሁ ውደቁ፡፡ (አል ሂጅር 29)

ይች ሩህ ወደ ጠፊዉ አካል እንድትካተት ሆነ ። የተወሳዉን ክስተት አሏህ ሱብሀነሁ ወታአላ ያነሳልን ነፍስ አስ ሱልጣንያህ አካልን እንድትመራና እንድትቆጣጥር እንጅ ከስጋ ብርታት ፊት እንድትልፈሰፈስ አለመሆኑን ሊገልፅልን ሽቶ ነዉ። ሩህ በአካል ዉስጥ ሁኔታዋ ልክ ወተት ዉስጥ እንደሚገኝ ቅቤ ነዉ። ቅቤዉ ተደብቋል አይታይም ሩህም በአካል ዉስጥ እንዲሁ ናት። ቅቤዉ ከወተቱ እዲወጣ ወተቱ በሀይል መገፋትና መንቀሳቀስ አለበት ። የሩህ መሪነት እንዲረጋገጥ ደሞ መንፈሳዊ ትግልና እንቅስቃሴ እንዲሁም ከክልክላዎች ሁሉ የመራቅ ትእግስት ያስፈልጋል። መዳንና ለዘላአለማዊ ስኬት መብቃት ነፍስን ሳያጠሩ ሊሆን እንደማይችል ጌታችን አሏህ በአንቀፁ አብራርቶልናል።

قَدْ أَفْلَحَ مَن تَزَكَّىٰ
وَذَكَرَ اسْمَ رَبِّهِ فَصَلَّىٰ

የተጥራራ ሰው በእርግጥ ዳነ፡፡
የጌታውንም ስም ያወሳና የሰገደ፡ አል አእላ 14;15
قَدْ أَفْلَحَ مَن زَكَّاهَا
وَقَدْ خَابَ مَن دَسَّاهَا
(ከኀጢኣት) ያጠራት ሰው ፍላጎቱን በእርግጥ አገኘ፡፡
(በኀጢኣት) የሸፈናትም ሰው በእውነት አፈረ፡፡
አል ሸምስ 9-10

የሀይማኖት አላማዉ የሀሳብና የዉበት ቋት የሆነዉን የሰዉ ልጅ ማለዘብና ማግራት ነዉ።ከልብ የሆነ አምልኮ ቀልብ ያለዝባል። ባህሪን ያገራል ጥልቅ ማስተዋልና ማስተንተን ሲታከልበት ደሞ የበለጠ ይጎመራል። በኢባዳ የተገራ ባሀሪ በማስተዋልና በዚክር የፀዳ ቀልብ በእዉቀትና በማስተንተን የሰላ አእምሮ ያለዉ ሰዉ ትልቅ ደረጃ ላይ ደርሷል።

إِنَّمَا الْمُؤْمِنُونَ الَّذِينَ إِذَا ذُكِرَ اللَّهُ وَجِلَتْ قُلُوبُهُمْ وَإِذَا تُلِيَتْ عَلَيْهِمْ آيَاتُهُ زَادَتْهُمْ إِيمَانًا وَعَلَىٰ رَبِّهِمْ يَتَوَكَّلُونَ

ፍጹም ምእምናን እነዚያ አላህ በተወሳ ጊዜ ልቦቻቸው የሚፈሩት፣ በነሱም ላይ አንቀጾቻችን በተነበቡ ጊዜ እምነትን የሚጨምሩላቸው፣ በጌታቸውም ላይ ብቻ የሚመኩት ናቸው፡፡ (አል አንፉል 2)


الَّذِينَ إِذَا ذُكِرَ اللَّهُ وَجِلَتْ قُلُوبُهُمْ وَالصَّابِرِينَ عَلَىٰ مَا أَصَابَهُمْ وَالْمُقِيمِي الصَّلَاةِ وَمِمَّا رَزَقْنَاهُمْ يُنفِقُونَ

እነዚያን አላህ በተወሳ ጊዜ ልቦቻቸው የሚጨነቁትን፣ በደረሰባቸውም (መከራ) ላይ ታጋሾችን፣ ሶላትንም አስተካክለው ሰጋጆችን፣ ከሰጠናቸውም ሲሳይ የሚለግሱትን (አብስር)፡፡ አል ሀጅ 35


وَاذْكُر رَّبَّكَ فِي نَفْسِكَ تَضَرُّعًا وَخِيفَةً وَدُونَ الْجَهْرِ مِنَ الْقَوْلِ بِالْغُدُوِّ وَالْآصَالِ وَلَا تَكُن مِّنَ الْغَافِلِينَ

ጌታህንም በምስጢር ተዋድቀህና ፈርተህ ከጩኸት በታችም በኾነ ቃል በጧትም በማታም አውሳው፡፡ ከዘንጊዎቹም አትኹን፡፡ (አል አእራፍ 205)


وَاذْكُرِ اسْمَ رَبِّكَ وَتَبَتَّلْ إِلَيْهِ تَبْتِيلًا

የጌታህንም ስም አውሳ፤ ወደእርሱም (መግገዛት) መቋረጥን ተቋረጥ ፡፡ (አል ሙዘሚል 8


اللَّهُ الَّذِي رَفَعَ السَّمَاوَاتِ بِغَيْرِ عَمَدٍ تَرَوْنَهَا ۖ ثُمَّ اسْتَوَىٰ عَلَى الْعَرْشِ ۖ وَسَخَّرَ الشَّمْسَ وَالْقَمَرَ ۖ كُلٌّ يَجْرِي لِأَجَلٍ مُّسَمًّى ۚ يُدَبِّرُ الْأَمْرَ يُفَصِّلُ الْآيَاتِ لَعَلَّكُم بِلِقَاءِ رَبِّكُمْ تُوقِنُونَ

አላህ ያ ሰማያትን የምታዩዋት አዕማድ ሳትኖር ያነሳት ከዚያም በዐርሹ (ዙፋኑ) ላይ (ስልጣኑ) የተደላደለ ፀሐይንና ጨረቃንም የገራ ነው፡፡ ሁሉም ለተወሰነ ጊዜ ይሮጣሉ፡፡ ነገሩን ሁሉ ያስተናብራል፡፡ በጌታችሁ መገናኘት ታረጋግጡ ዘንድ ተዓምራቶችን ይዘረዝራል፡፡ (አል ረእድ 2)

ይቀጥላል'''''''''ቻናሉን ተቀላቀሉ።

https://t.me/HiDAYATV
https://t.me/HiDAYATV
429 viewsAllah is great, 16:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-03 16:37:46 ሙሐደራ ቁጥር ⓷⓪
547 viewsእንደ አበባ ፈክተሽ ወንድ ከምታፈዢ ሂጃብሽን(ኒቃብሽን) ለብሰሽ ጌታሽን ተገዢ!!!, 13:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-03 15:37:07 ወንድሜዋ ፂምህን አሣድግ!!

ጺምን (ጢም ) ማሳደግ የነብያት፣ የሶሃቦችና የቀደምት የኢስላም አባቶች የዲናቸው (የእምነታቸው) አንዱ አካል ነው፡፡ ፂም ማሳደግ ዋጂብ ለመሆኑ መረጃ ከቁራን፤ከሐዲስ እና የኡለማዎች ስምምነት (ኢጅማዕ) አለ፡፡

1) ቁራናዊ መረጃ

قال الله تعالى (( قال يبنؤم لا تأخذ بلحيتي ولا برأسي ))
قال العلامة الشنقيطي في أضواء البيان ( ج 4 ص 506 ) عند تفسير هذه الآية
(( فهي دليل قرآني على إعفاء اللحية وعدم حلقها ) اهـ .

"የእናቴ ልጅ ሆይ ጢሜንም ራሴንም አትያዝ" ኢማም ሙሐመድ አሚን አሽ-ሺንቂጢ በዚህ አያ ማብራሪያቸው ከሱረቱ-ጣሃ ‹አድዋዑል በያን› ላይ እንዲህ ይላል:-
"ይህ አያ ጺምን ማሳደግ ባለበት መተውና አለመላጨት ዋጂብ ለመሆኑ ቁራናዊ መረጃ ነው አለ"

2) ከሐዲስ መረጃ

"عن نافع عن ابن عمر عن النبي صلى الله عليه وسلم قال «خالفوا المشركين وفروا اللحى وأحفوا الشوارب » متفق عليه

“ አጋሪዎችን ተቃረኗቸው፤ ጺማችሁን አወፍሩት (ባለመላጨት አብዙት)፣ ከአፍንጫ ስር ያለውን (ቀድሞቀመስ) ደግሞ አሳጥሩት፡፡

عن زيد بن أرقم رضي الله عنه قال: قال رسول الله صلى الله عليه وسلم: «من لم يأخذ من شاربه فليس منا» خرجه الترمذي في سننه وصححه الشيخ الألباني

ኢማም ቲርሚዚ በዘገቡት ሀዲስ ደግሞ የአላህ መልክተኛ እንዲህ ይላሉ፡
“ ከአፍንጫው ስር ያለውን ጸጉር ያላሳጠረ ከእኛ አይደለም፡፡ ”

3) በኡለማዎች ስምምነት (ኢጅማዕ) ደግሞ

قال العلامة الكبير والحافظ الشهير أبو محمد ابن حزم: (اتفق العلماء على أن قص الشارب وإعفاء اللحية فرض) ا.هـ.مراتب الإجماع
ታላቁ ኢማም አቡ ሙሐመድ ቢን ሐዝም- ኢብኑ ሐዝም በመባል የሚታወቁት ረሂመሁላህ እንዲህ ይላሉ -"የቀደምት ኡለማዎች ተስማምቷል ፂም ማሳደግና ዋጂብ በሞሆኑና ከአፍንጫው ስር ያለውን ጸጉር ማሳጠር ግዴታ በመሆኑ ላይ።"

አሁን ደግሞ ፂም ማሳደግን በተመለከተ ታላላቅ የሱና ኡለማዎች ከነበሩት የስጧቸው ፈተዋዎች እንመልከት

ሸይኽ አብዱል ዓዚዝ ኢብኑ ባዝ ረሒመሁላህ
https://t.me/tewihd/4780
ሼኽ ሙሐመድ ናሲሩዲን አልባኒ ረሒመሁላህ
https://t.me/tewihd/4777

ሸይኽ ሙቅቢል ኢብኑ ሃዲ አልዋዲዒ ረሒመሁላህ
https://t.me/tewihd/4781

ሸይኽ መሀመድ ኢብኑ ሷሊህ አል‐ዑሰይሚን ረሒመሁላህ
https://t.me/tewihd/4782

ሸይኽ ሷሊህ ፈውዛን አልፈውዛን

https://t.me/tewihd/4779

ሸይኽ ሉሀይዳን
https://t.me/tewihd/4782


https://telegram.me/tewihd
598 viewsእንደ አበባ ፈክተሽ ወንድ ከምታፈዢ ሂጃብሽን(ኒቃብሽን) ለብሰሽ ጌታሽን ተገዢ!!!, 12:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ