Get Mystery Box with random crypto!

AHADU RADIO FM 94.3

የቴሌግራም ቻናል አርማ ahaduradio — AHADU RADIO FM 94.3 A
የቴሌግራም ቻናል አርማ ahaduradio — AHADU RADIO FM 94.3
የሰርጥ አድራሻ: @ahaduradio
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.04K
የሰርጥ መግለጫ

አሐዱ ራድዮ 94.3
Your source for top local and international news and analysis.
"Voice of Ethiopian"
የአሐዱ የቴሌግራም ቻናል ቤተሰብ በመሆን ወቅታዊና እውነተኛ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 22

2023-01-04 14:39:32
ቱርክ በሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት ውስጥ ያላት አባልነት ጥያቄ ውስጥ መግባቱ ተነግሯል፡፡

የቀድሞው የአሜሪካ ብሔራዊ የፀጥታ አማካሪ ጆን ቦልተን እንደተናገሩት ቱርክ በሩሲያ ላይ ስለያዘችው አቋም በግልጽ ለመለየት ያለመቻሉን እናውቃለን በዚያም የተነሳ ቱርክ በሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት ውስጥ ያላት የአባልነት ሚና ጥያቄ ውስጥ ገብቷል ሲሉ ገልጸዋል፡፡

ሩሲያ በዩክሬን በገባችበት ጦርነት የተነሳ ቱርክ አመዛኝ በህርይዋና አቋሟ ከሩሲያ ጎን የተሰለፈች እንጂ እንደ የኔቶ አባልነቷ ያሳየችው ብርቱ ተቃውሞና ውግዘት እምበዛም አይደለም ነው ያሉት፡፡

በመጪዎቹ ወራት የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት አባል ሀገራት በቱርክ የአባልነት ጉዳይ ብርቱ ፈተና ይደቀንባቸዋል ሲሉ አስታውቀዋል፡፡
ዘገባው፡- የመኸር ኒውስ ነው፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን
#አሐዱ_24 #Ahadu_News_24 #News_24
3.0K views11:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-04 14:36:31
የምስራቅ አፍሪካ በይነ መንግስታት ወይም /ኢጋድ/ በደቡብ ሱዳን የተነሳ ስብሰባ መጥራቱ ተነገሯል፡፡

የኬንያው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ትናንት በሰጡት ማብራሪያ የምስራቅ አፍሪካ በይነ መንግስታት ወይም /ኢጋድ/ በደቡብ ሱዳን የሰላምና አጠቃላይ ጉዳይ የተያዘው የአውሮፓውያኑ ጥር ወር ከመጠናቀቁ በፊት ስብሰባ እንደሚቀመጥ አስታውቀዋል፡፡

የኬንያው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ እንደገለፁት የኢጋድ አባል ሀገራት ጉባኤ የሚቀመጡት የሱዳን መሪ ጀነራል አብዲል ፈታ አልቡርሃን ባስተላለፉት ጥሪ መሰረት እንደሆነም ነው የተናገሩት፡፡
የኬንያና የሱዳን መሪዎች በምስራቅ አፍሪካ ቀጣና ስላለው አጠቃላይ የፀጥታና የሰላም ሁኔታ መምከራቸውም ነው የተሰማው፡፡

በዚህ ወቅት የሱዳኑ ወታደራዊ መሪ ጀነራል አልቡርሃን የደቡብ ሱዳን የፀጥታ ጉዳይ እንደሳሰባቸውም ነው የተገለፀው፡፡
ዘገባው፡-የሬዲዮ ታማጁዝ ነው፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን
#አሐዱ_24 #Ahadu_News_24 #News_24
2.6K views11:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-04 14:31:58
የጸጥታ ሃይሎች ህብረተሰቡን በትህትና ማገልገል እንደሚገባቸው ተገልጿል፡፡

ትህትና በተሞላው መልኩ ለዜጎች አገልግሎት ከመስጠት ባለፈ ከለላ የመሆን ሃላፊነት የተጣለባቸው እንደ ፖሊስ ያሉ የጸጥታ ሃይሎች ህብረተሰቡን በሚያገለግሉበት ወቅት ትህትናን በተላበሰ መልኩ ሊሆን እንደሚገባው የገለጸው የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ነው፡፡

በኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊው ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ እንዳሉት ምንም እንኳን ፖሊስ ህብረተሰቡን በወታደራዊ ዲሲፕሊን ፣ በግብረ-ገብ እና ትህትና ማገልገል እንዳለበት እሙን ቢሆንም ይህንን አካሄድ በሚያፋልስ መልኩ የሚንቀሳቀሱ የፖሊስ አባላትም አሉ፡፡ በመሆኑም ይህ ፍጹም ተቀባይነት የሌለውና የፖሊስ ስነ-ምግባርን የሚጻረር በመሆኑ አባላቱ ቀደም ሲል በተገለጸው መንገድ ህብረተሰቡን ማገልገል አለባቸው ሲሉም ተናግረዋል፡፡

መልካም ስነ-ምግባር ያላቸው የፖሊስ አባላት እንዳሉ ሁሉ ግብረ-ገብና ትህትና የጎደላቸው አባላትም እንዳሉ ያነሱት ሃላፊው ይህ ሊታረም እንደሚገባውና አባላቱም በጎ ምግባር ያላቸውን ፖሊሶች አርአያ በማድረግ ያንኑ መከተል እንዳለባቸው አስገንዝበዋል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን
#አሐዱ_24 #Ahadu_News_24 #News_24
2.3K viewsedited  11:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-04 14:27:32
በበዓላት ወቅት በሀሰተኛ መንጃ ፍቃድ የሚያሽከረክሩ ግለሰቦች በብዛት እንደመታየታቸው ማህበረሰቡ ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለበት የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮምሽን አሳሰበ፡፡

በበዓል ግብይት ወቅት ወንጀል እንዳይፈጸም አደጋ እንዳይከሰት ምን ዝግጅት ተደርጓል ሲል አሀዱ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮምሽን የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰን ጠይቋል፡፡

በምላሻቸውም በበዓላት ወቅት ወንጀል ሊፈጸም ፤ የትራፊክ አደጋም ሊከሰት የሚችል በመሆኑ ማህበረሰቡ በብዙ ዘርፉ ጥንቃቄ ሊያድረግ እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡
በዚህ ረገድ የሚፈጸሙ ወንጀሎችን እና የትራፊክ አደጋዎችን ለመከላከል የቅድመ ዝግጅት ስራ መሰራቱን ተናግረዋል፡፡
በዓላትን ብቻ መነሻ በማድረግ የሚፈጸሙ ወንጀሎች መኖራቸውን የተናገሩት የህዝብ ግንኙነት ሀላፊው ስርቆት፤ዝርፊያ፤ንጥቂያ ሌሎችም ወንጀሎች ሊፈጸሙ እንደሚችሉ ገልጸዋል፡፡

የበዓል ሰሞን ድንገተኛ አደጋዎች ጭምር ሊከሰት እንደሚችል የተናገሩት ኮማንደር ማርቆስ ሀሰተኛ መንጃ ፍቃድ ወይም ያለመንጃ ፍቀድ ሚየሽከርክሩ ሰዎች ጎልተው የሚታዩበት ነው ብለዋል፡፡
ለመዝናናት ነው በሚል ህጋዊ ባልሆነ መንገድ ማሽከርከር ተገቢ እንዳልሆነ እና የሚያደርሰው አደረጋም የከፋ ነው ባይ ናቸው፡፡
ኮምሽኑም በዚህ ረገድ ዝግጅት በማድረግ ህገ-ወጥናትን በመካለከል ቀድሞ የሚሰራውን ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ጠቁመዋል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን
#አሐዱ_24 #Ahadu
1.9K views11:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-04 14:16:46
ከራስ ጥቅም ይልቅ ማህበረሰብን በማስቀደም የሲቪክ ማህበራት በትህትና አገልጋይ መሆን እንዳለባቸው ተገለጸ፡፡

አሀዱ ለሳምንቱ ቀናት በሰጠው ስያሜ መሰረት የዛሬው እለት የትህትና ቀን ብሎ እንደመሰየሙ በዚህ ረገድ የሲቪክ ማህበራት ማህበረሰቡን በማገልገል ረገድ ሚናቸው ምን ሊሆን ይገባል እንዴትስ ምሳሌ መሆን አለባቸው ሲል ጠይቋል፡፡

ምላሽ የሰጡት የሲቪክ ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ጂማ ዲልቦ ሲቪክ ማህበራት ማህበረሰቡን መሰረት አድረገው የተቋቋሙ እንደመሆናቸው ሌሎች በብዙ መንገድ አርያ መሆን አለባቸው ብለዋል፡፡

የሚሰጡት አገልግሎትም ከትህትና እንዲሁም ሰውን ከማክበር ጋር ሊሆን እንደሚገባ የተናገሩት አቶ ጂማ በዚህ ረገድ ሀላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡ አንድ ሰው በትህትና ሌሎችን ማገልገል ሲችል ለራሱ ያለው ክብር የሚታይበት ማንነቱ የሚገልጸበት ነው ባይ ናቸው፡፡
ማህበራቱ ከራሳቸው ጥቅም ይልቅ ማህበረሰቡን በትህትና ማገልገል ላይ ማተኮር እንዳለባቸው አቶ ጂማ ጠቁመዋል፡፡
ትህትና የፈጣሪ መገለጫ እንደ መሆኑ በዚህ ረገድ ማህበረሰቡን አገልጋይ መሆን የሚደገፍ የሚያበረታታ ለሚሰራው ስራም ውጤት የሚያስገኝ ነው ሲሉም አመላክተዋል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን
#አሐዱ_24 #Ahadu_News_24 #News_24
2.3K viewsedited  11:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-03 16:11:46
እርቀ ሰላምን ለማውረድ እና ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት ውስጥ ማህበረሰቡ ከታሪክ ሊማር እንደሚገባው ተገለጸ፡፡

አሁን የተጀመረውን የሰላም ሂደት በዘላቂነት ለማስቀጠል እና በየ አካባቢው የሚፈጠሩ የጸጥታ ችግሮችን ለመቅረፍ ማህበረሰቡ ከታሪክ ተምሮ የበኩሉን አስተዋጽኦ ሊያበረክት እንደሚገባ ተመላክቷል፡፡

ያለፉ ታሪኮቻችንን መለስ ብሎ መመልከቱ ለጀመርነው የሰላም ሂደት ከፍተኛ አስተዋጾ እንዳለው ለአሃዱ የገለጹት የታሪከ ምሁሩ ፕሮፍሰር አህመድ ዘኸርያ ባለፉት ታሪኮቻችን ላይ ያሉት እውነታዎች ሰላምን በማምጣት ረገድ፤ ይቅርታን አማራጭ አድርጎ በመመልከት ለሃገር ሁለንተናዊ ሰላም እና ልማት መረጋገጥ ጉልህ አበርክቶ ያላቸዉ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ባለፉ ታሪኮቻችን ላይ የነበሩ እውነቶችን በምሳሌነት አንስተው ለዛሬው ትውልድ በማሳያነት ያቀረቡት ሌላኛው የታሪክ ምሁር አቶ ደረጄ ተክሌ በሃገሪቱ ውሰጥ በአሁኑ ጊዜ በአንጻራዊነት እየሰፈነ ያለውን ሰላም በዘላቂነት ለማስቀጠል ማህበረሰቡ ካለፉት መልካም ተሪኮቹ መማር እንዳለበት እና ለሀገር ሰላም ብሎም ልማት በጋራ በመቆም የበኩሉን አስተዋጽኦ ሊያበረከት እንደሚገባም አስገንዝበዋል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
2.2K viewsedited  13:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-03 15:17:51
የሰሜን ኮሪያው መሪ የሀገራቸው የጦር መሳሪያ ጠበብቶች ተጨማሪ የጅምላ ጨራሽ የኑክሌር ጦር መሳሪያና የረዥም ርቀት ተምዘግዛጊ መሳሪያዎችን ያመርቱ ዘንድ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

በዚህ ወቅት ለመላው ዓለም ጭንቀትና ስጋት በጋጠመው የሰሜን ኮሪያና የባላንጦቿ በተለይም በአሜሪካ በደቡብ ኮሪያና በጃፓን ጉዳይ ላይ ሰሜን ኮሪያ አንዳች እርምጃ ለመውሰድ ጊዜ እየጠበቀች መሆኑ ይነገራል፡፡

የደቡብ ኮሪያ ጦር ሀይል ባወጣው መግለጫ የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን ለሀገሪቱ ጦር መሳሪያ ጠበብቶች ጥሪ ማቅረባቸውን ገልፀዋል፡፡
የሰሜን ኮሪያ መንግስት የአህጉር አቋራጭ የባላስቲክ ሚሳይሎች ግዙፍ መጠን ያለው የኑክሌር ጦር መሳሪያ እንዲመረትና በባላንጦቻቸው ሀገራት ላይ የማያዳግም እርምጃ ለመውሰድ ቆርጦ መነሳቱን አስታውቋል፡፡

በቅርቡ በተካሄው የሰሜን ኮሪያው የሰራተኞች ፓርቲ ጉባኤ ላይ የሀገሪቱ መሪ ኪም ጆንግ ኡን እንደተናገሩት በእስያ ቀጣና ሀያል የጦር ሀይል መገንባት አለብን ነው ያሉት፡፡

ዘገባው፡-የኤዥያን ዋን ነው፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
2.3K views12:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-03 15:14:54
የናይጄሪያ ጦር በዛምፋራ ግዛት በፈጸመው ጥቃት በርካታ ሽፍቶችን መግደሉ ታውቋል፡፡
የናይጄሪያ ጦር ሀይል በአየር ሀይሉ እየታገዘና በምድር ጦሩ ባደረገው ጥልቅ አሰሳ ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ በትንሹ 16 ሽፍቶችን መግደሉን አስታውቋል፡፡
በናይጄሪያ ከምደርና ከሰማይ የተቀናጀና የተጠናከረ አሰሳ ለረዥም ጊዜ ሲፈለግ የነበረው የሽፍቶቹና የአሸባሪዎቹ ዋና መሪና አስተባባሪ ኪንግፒን ማምለጡም ነው የተነገረው፡፡
በዛምፋራ ግዛት የናይጄሪያ ጦር ሀይል በፈፀመው ጥልቅ አሰሳ ያመለጠው የሽፍቶቹና የአሸባሪዎቹ ዋና መሪና አስተባባሪ ክፉኛ ቆስሎ መሆኑም ተሰምቷል፡፡
የናይጄሪያ ጦር ሀይል አሰሳውንና ጥቃቱን የፈጸመው በአዲሱ የአውሮፓውያኑ 2023 አዲስ ዓመት ዋዜማ መሆኑን ዘገባው ያብራራል፡፡
የአሸባሪዎቹ ሀይሎች በመሪያቸው ላይ ስለተቃጣው የግድያ ሙከራ እጅጉን ማዘናቸውን የዘገበው ፐንች ነው፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
2.0K views12:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-03 15:00:10
በፖለቲካዉ ዘርፍ የማያግባቡ ጉዳዮችን በመለየት እርቅ ማዉረድ እንደሚገባ ተገልጿል፡፡

የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ዋና ሰብሳቢ ዶክተር መብራቱ አለሙ እርቀ ሰላም ላይ ሁሉም ዜጋ ድርሻ አለዉ ያሉ ሲሆን እንደ ሀገራችን ኢትዮጲያ ባህል እሴት ግን ሰፊዉን ድርሻ የሀገር ሽማግሌዎችና የሀይማኖት አባቶች ይይዛሉ ሲሉ ተናግረዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት ለሰላም እጦት እና አለመግባባት ዋና ተፅእኖ እያደረጉ ያሉትና ለግጭት መንስኤ እየሆነ ያለዉ የፖለቲካ አለመግባባት በመሆኑ የፖለቲካ ተዋንያኖች ችግሩን ሊፈቱና እርቅ ሰላም ሊፈጥሩ ይገባል ነዉ ያሉት፡፡

ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት እርቅ ሰላምን የምትሻበትና ህዝብ እየናፈቀዉ ያለዉ ዋነኛ ጉዳይ በመሆኑ በተለይ በፖለቲካዉ ዘርፍ የማያግባቡ ጉዳዮችን በመለየት እርቅ ማዉረድ እንደሚገባ ዶክተር መብርሀቱ ለአሀዱ ገልፀዋል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
2.0K views12:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-03 14:48:02
አሁን ላይ ሀገራችን ከገባችበት ቀውስ ወጥታ የተሻለ ሰላማዊ ሁኔታ ወስጥ እንድትገባ ሁሉም ሰው ሰላምን እንደ ስጦታ ሊሰጥ ይገባል ተባለ።

በሀገራች ውስጥ ያለውን ሁኔታ ለማስተካከል ሁላችንም የየራሳችንን ድርሻ በመውሰድ ሰላማዊ መስተጋብር እንዲፈጠር መትጋት አለብን ያሉት የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ዶክተር ዳንኤል በቀለ ናቸው።
መተሳሰብን፤ መቻቻልን እንዲሁም ሰላማዊ መስተጋብርን ማስፋት በሀገር አቀፍ ደረጃ የተሻለ ሁኔታ ለማስፈን መሰረታዊ ጉዳዮች በመሆናቸው ትኩረት ልናደርግባቸው ይገባል ብለዋል።

ይህ የሰላም እጦትን የመለዋወጥ እና የመቻቻል መሰረትን መጣል የሁሉም ዜጋ ሀላፊነት በመሆኑ በአንድ መንፈስ ለዚህ ተግባራዊነት መትጋት ተገቢ ነው ሲሉም አመላክተዋል።

እንደ ሀገር ወደ ፊት ለመራመድ ሰላም ያስፈልገናል ይህንን ሰላም ደግሞ የምናመጣው እኛው በመሆናችን ለዚህ የበኩላችንን ልንወጣ ይገባል ነው ያሉት።
በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የነበረውን ችግር በሰላማዊ ሁኔታ በመፍታት አሁን ላይ እየታየ ያለውን ተስፋ ሰጪ ሁኔታ እንድናይ ያስቻለን የሁላችን ጥረት ነው ሲሉም ገልጸዋል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
2.3K viewsedited  11:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ