Get Mystery Box with random crypto!

AHADU RADIO FM 94.3

የቴሌግራም ቻናል አርማ ahaduradio — AHADU RADIO FM 94.3 A
የቴሌግራም ቻናል አርማ ahaduradio — AHADU RADIO FM 94.3
የሰርጥ አድራሻ: @ahaduradio
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.04K
የሰርጥ መግለጫ

አሐዱ ራድዮ 94.3
Your source for top local and international news and analysis.
"Voice of Ethiopian"
የአሐዱ የቴሌግራም ቻናል ቤተሰብ በመሆን ወቅታዊና እውነተኛ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 21

2023-01-09 14:53:59
በሶማሊያ ወታደራዊ ማዘዣ ጣቢያ ላይ በተፈጸመ ከባድ ጥቃት በርካታ የጦር ሀይሉ አባላት መገደላቸው ታውቋል፡፡

የሶማሊያ ባለስልጣናት በሰጡት ማብራሪያ በመካከለኛው የሸበሌ ግዛት በምትገኘው የሩኒር ጉድ መንደር በተፈጸመ ድንገተኛ ጥቃት ሰባት የሀገሪቱ ጦር ሀይል አባላት መገድላቸውን አስታውቀዋል፡፡

የዚያ የሩኒር ጉድ መንደር ቀድሞ በአልሸባብ አሸባሪ ሀይሎች እጅ እንደነበረ ሲገለፅ በቅርቡ የሶማሊያ መንግስት ሀይሎች በካሄዱት ደም አፋሳሽ ውጊያ ስፍራውን ሙሉ በሙሉ መቆጣጠራቸው ይታወቃል፡፡

የአልቃይዳው አሸባሪ ቡድን ክንፍ የሆነው አልሸባብ ሀይሎች በመንግስት ሀይሎች የተቃማባቸውን ይዞታዎች ሁሉ በማስመለስ የሞትሺረት ትግል እያደረጉ ስለ መሆኑ የዓለም የመገናኛ ብዙሃን ይዘግቡታል፡፡

በዚም የተነሳ የአልሸባብ ሀይሎች በመንግስት ጦር ሀይል የጦር ማዛዥ ላይ በከፈቱት ድንገተኛ ጥቃ ሰባት ወታደሮችን መግደላቸውን የዞገበው የአሜሪካ ድምጽ ነው፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24 #Ahadu_News_24 #News_24
1.4K views11:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-09 14:28:10
የትግራይ ክልል ሰላም ከዚህ በላይ እየተረጋጋ ሲሄድ በክልሉ በሚገኙ 4 ዩንቨርስቲዎች ቅርንጫፍ ፅኅፈት ቤቶች እንደሚከፍት የሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ አስታወቀ፡፡

የሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ በየክልሉ ባሉ ዩንቨርስቲዎች አማካኝነት ቅርንጫፍ የአስተዳደር ፅህፈት ቤቶች በመክፈት ሰራተኞችን ለመላክ ዝግጅት እያደረገ መሆኑን የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር እና የህዝብ ግንኙነት ሃላፊዉ ዶክተር ዮናስ አዳዬ ለአሀዱ ተናግረዋል፡፡

የትግራይ ክልል ሰላም ከዚህ በላይ እየተረጋጋ ሲሄድ በክልሉ በሚገኙ 4 ዩንቨርስቲዎች ፅህፈት ቤቶች እንደሚከፈቱ አስታዉቀዋል፡፡
ከታሪክ ምሁራን ጋር ቀጥተኛ ግኑኙነት በማድረግ እና ከመነጋገር የመግባቢያ ሰነድ ወደ መፈራረም እየተሸጋገረን ነው ብለዋል፡፡

ከ53 የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር አብሮ ለመስረት የስምምነት ፊርማ መፈራማቸዉን ገልፀዉ በሁሉም ረገድ ለመቀራረብ ዝግጅት እያደረጉ መሆናቸዉን አስታዉቀዋል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24 #Ahadu_News_24 #News_24
1.6K views11:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-09 14:26:10
በሌሎቹ የሃገሪቱ አካባቢዎችም የሽግግር ፍትህን መተግበር እንደሚገባ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ገለጸ፡፡

ባለፉት ጥቂት አመታት ግጭትና አለመረጋጋት ሰፍኖባቸው በቆዩ የሃገሪቱ አካባቢዎች በርካታ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች መፈጸማቸውን ያስታወሰው ተቋሙ በሌሎቹ የሃገሪቱ አካባቢዎችም የሽግግር ፍትህን መተግበር እንደሚገባ ገልጿል፡፡

የሰሜኑን ጦርነት ተከትሎ የተፈጸሙ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ሰለባ የሆኑ ዜጎች ፍትህ እንዲያገኙ ለማስቻል የሽግግር ፍትህ ተግባራዊ እንደሚደረግ የተገለጸ ሲሆን ነገር ግን ትግበራው በሌሎቹም ግጭትና አለመረጋጋት ሰፍኖባቸው በቆዩና አሁንም ባልተረጋጉ አካባቢዎች ላይ መሆን እንዳለበት የኢትዮጲያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ዶክተር ዳንኤል በቀለ ለአሃዱ ገልጸዋል፡፡

ከነዚህም አካባቢዎች መካከል የኦሮምያ፣ ቤንሻንጉልና ደቡብ ክልሎች የሚገኙበት ሲሆን ይህም ሃገር አቀፍና ሙሉእ እንዲሁም ዘላቂ ሰላምን ለማምጣት ያስችላል ነው ያሉት፡፡
ባለፉት ጥቂት አመታት ከሰሜኑ የሃገሪቱ ክፍል ጦርነት ባሻገር በኦሮምያ፣ በቤንሻንጉል፣ ደቡብ እንዲሁም የጋምቤላ ውስን አካባቢዎች ግጭትን ተከትለው የተፈጸሙ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች በተለያዩ ጊዜያት ለህዝብ ይፋ መደረጋቸው ይታወሳል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24 #Ahadu_News_24 #News_24
1.5K viewsedited  11:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-09 14:23:30
ከህገወጥ የቤቶች ግንባታ ጋር ተያይዞ የሚስተዋለውን ያልተረጋጋ ሁኔታ ስርአት ለማስያዝ የህግ ማእቀፉን ቀድሞ መረዳት እንደሚገባ ተገለጸ፡፡

ከከተማ መሬት አስተዳደር ጋር ተያይዞ የወጣ ህግ መኖሩን እና በህጉ ላይ ያለውን የግንባታ ፍቃድ አሰጣጥ በየደረጃው ያሉ የመንግስት ሀላፊዎች ሊረዱት እንደሚገባ በከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተ አቶ ኢትዮጵያ በዴቻ ገልጸዋል፡፡
እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ ከሆነ ከዚህ ጉዳይ ጋር ተያይዞ ለሚሰራው ስራ እጃቸው የሚያርፍበት በርካታ የመንግስት ሀላፊዎች በመኖራቸው ከግንባታ ፍቃድ አስጣጥ አንሰቶ የሚስተዋለው ችግር አንዱና ዋንኛው ምክንያት እንደሆነ ነው የሚጠቅሱት፡፡

በመሰረታዊነት በህግ ማዕቀፉ ላይ ያለውን አሰራር በሚገባ በመረዳት ግንባታ ከመከናወኑ አስቀድሞ ሊጤን የሚገባው ጉዳይ እንደሆነም ነው የሚጠቅሱት፡፡
ከህገወጥ የቤቶች ግንባታ ጋር ተያይዞ የሚመጡ ችግሮች በዛን ረገድ የሰዎችን ህይወት ያልተገባ ሁኔታ ውስጥ ከማስገባታቸው አስቀድሞ አሰራሩን በመረዳት ተገቢው ውሳኔ ተግባራዊ ማድረግ ቅድሚያ ሊሰጠው እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24 #Ahadu_News_24 #News_24
1.7K viewsedited  11:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-05 14:29:25
ሁሉንም ሃይማኖቶች በእኩል ዐይን መመልከት እንደሚገባ የሃይማኖት መምህራን ገለጹ፡፡

ኢትዮጵያ የተለያዩ ሃይማኖቶች መኖሪያ ብትሆንም ህዝቦቿ በመከባበር ውስጥ የሚኖሩባት እንደሆነች የሚነገርላት ሲሆን ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ግን በተለያዩ ሃይማኖቶች መካከል ቅራኔ እንዲፈጠር የሚሰሩ ሃይሎች መበራከታቸውን ተከትሎ ክፉ አመለካከትን ወደ ጎን በመተው ሁሉንም ሃይማኖቶች እኩል ማየት እንደሚገባ ለአሐዱ አስተያየታቸውን የሰጡ የሃይማኖት መምህራን ገልጸዋል፡፡

በቅድስት ስላሴ ዩኒቨርሲቲ መምህር ፍቅረማሪያም ባዘዘው የፈጣሪን ትእዛዝ ተከትሎ ፍቅርን ማስበለጥ መከባበርን ፣ በመከባበር ውስጥ እኩልነትን ማስፈን ያስችላል ይላሉ፡፡

ሌላኛው አሐዱ ያነጋገራቸው የእስልምና ሃይማኖት መምህሩ ሼህ አህመድ አወሉ በበኩላቸው በተለይም ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በሃይማኖቶች መካከል ግጭትን በመቀስቀስ ቅራኔ እንዲፈጠርና ሃይማኖቶቹ በማህበረሰቡ ዘንድ በእኩሌታ እንዳይታዩ የሚያደርጉ አካላትን ማስቆም እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡
በመሆኑም በሃይማኖቶች ዘንድ እኩልነት እንዲኖርና መከባበር እንዲሰርጽ ለማድረግ ታላላቅ የሃይማኖት መምህራን ከመሃከላችን እንዲፈልቁ ማድረግ እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን
#አሐዱ_24 #Ahadu_News_24 #News_24
2.7K views11:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-05 14:25:51
በሶማሊ ላንድ በተከሰተ ግጭት በርካታ ሰዎች ህይወታቸውን ማጣታቸውና መጎዳታቸው ታውቋል፡
በሶማሊ ላንድ የፀጥታ ሀይሎችና በተቃውሞ አራማጆቹ መካከል ባጋጠመ ግጭት በትንሹ ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ 20 ሰዎች መሞታቸውና ከ30 በላይ ሰዎች ክፉኛ መቁሰላቸውን ዘገባው ያመላክታል፡፡
የሆስፒታል ምንጮች እንዳስታወቁት በሶማሌ ላንድ ከፀጥታ ሀይሎች ጋር በተደረገው ግጭት ህይወታቸውን ያጡት ሰዎች በሙሉ ንጹሃን ዜጎች መሆናቸውም ነው የተሰማው፡፡
በሶማሊ ላንድ ይሄ ሁሉ ሞት ያጋጠመው ላሳኖድ ተብሎ በሚጠራው ስፍራ ነው፡፡
ላሳኖድ የሚባለው ስፍራ በሶማሊ ላንድ እና በፑንት ላንድ ፖለቲካ ሀይሎች መካከል ከፍተኛ የሆነ ግጭት የሚቀሰቀስበት ስፍራ መሆኑን የዘገበው አናዶሉ ዜና ተቋም ነው፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን
#አሐዱ_24 #Ahadu_News_24 #News_24
2.3K views11:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-05 14:24:10
ግብጽ ከሱዳን ጋር ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር ፍላጎት እንዳላት ዳግም ገልጻለች፡፡
የግብጽ ባለስልጣናት ከሱዳን ጋር ያላቸውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር ብርቱ ፍላጎት እንዳላቸውና ትብብራቸውን ከበፊቱ የበለጠ ለማስፋፋት መፈለጋቸውን ነው ያስታወቁት፡፡
የሱዳኑ የሉዓላዊ ምክር ቤት መሪ ሌፍተናንት ጀነራል አብዱል ፈታህ አልቡርሃን ትናንት ከግብጽ ፕሬዝዳንት አብዱል ፈታ አልሲሲ የተላከ መልዕክት መቀበላቸው ነው የተሰማው፡፡
አናዶሉ የዜና ተቋም ባሰራጨው ዘገባው በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ግንኙነት በተሻለ ስሌት ወደ ተሻለ አቅጣጫ ለማምራት በሚያስችላቸው መንገድ ላይ መሆናቸውን ገልጿል፡፡
ቡርሃን ከደህንነት መስሪያ ቤታቸው ዳይሬክተር አህመድ አብራሂም ጋር ሆነው የግብጹ ፕሬዝዳንት አብዱል ፈታ አልሲሲ የደህንነት መስሪያ ቤት ዋና ኃላፊን አባሶ ከማልን ተቀብለው ማነጋገራቸውን የዘገበው ሚድል ኢስት ሞኒተር ነው፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን
#አሐዱ_24 #Ahadu_News_24 #News_24
2.0K views11:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-05 14:16:23
በሀይማኖት ተቋማት መካከል ተከባብሮ በእኩልነት የመኖር አስተሳሰብን ማራመድ እንደሚገባ ተገልጿል፡፡

በኢትዮጵያ በርካታ የእምነት ተቋማት እና አማኞች ቢኖሩም ሁሉም የሚከተለው እምነት እንዲከበርለትና እምነት ተቋሞቻችንና ቤተ እምነቶች እንዲጠበቁ እንደሚፈለገዉ ሁሉ የየትኛዉንም እምነት ተቋም ማክበርና ማስከበር ያስፈልጋል ተብሏል፡፡
ይህንን ለመተግበር የሁሉም ድርሻና ሀላፊነት ነዉ ሲሉ የኢትዮጵያ ሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ ዋና ፀሀፊ ቀሲስ ታጋይ ታደለ ለአሐዱ ገልፀዋል፡፡

ሌሎች የሚያከብሩትን እምነት ለማክበር የራስን እምነት አስቀድሞ የሚያከብር ዜጋ መሆን ስለሚገባ በየቤተ እምነቶቻችን ስር ያሉ አማንያንን በስነ ምግባር አንፆ ቤተ እምነቶችን አክባሪና አስከባሪ ትዉልድ ማፍራት ይገባል ብለዋል፡፡

ይህንን እንዳይደረግ ግን ዋና እንቅፋት የሆነውን እና እዚህ ደረጃ ያደረሰን የኔ ሀይማኖት ካልበለጠ የኔ የበላይ ካልሆነ የሚል እሳቤ ገኖ በመዉጣቱ በመሆኑ ይህንን አስተሳሰብ ማስወገድ ያሻል ብለዋል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን
#አሐዱ_24 #Ahadu_News_24 #News_24
2.0K views11:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-05 14:09:28
እኩልነት የሰዉ ልጆችን በአንድ ሊያኖር የሚችል ትልቅ መርህ በመሆኑ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ይህንን አስበዉ መስራት እንደሚገባቸዉ ተገለፀ፡፡
የእኩልነት ጉዳይ የሰብአዊ መብት ጉዳይ ሲሆን በህገ መንግስቱ በአንቀፅ 25 ላይም በግልፅ መቀመጡን በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ማህበር ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ባለሙያ አቶ በፍቃዱ ድሪባ ተናግረዋል፡፡
እኩልነት ማለት አንድ ሰዉ ያለ አድሎ ከማንኛዉም ሰዉ እኩል እንዲታይ የሚጠይቅ የሰዉ ልጆችን በአንድ ሊያኖር የሚችል ትልቅ መርህ በመሆኑ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ይህንን አስበዉ መስራት እንደሚገባቸዉ ገልፀዋል፡፡
ሰዎች በባህል በሀይማኖት በፆታ አድሎ ሳይደረግባቸዉ ያለ አድሎ እንዲኖሩ የሚያደርግ መርህ እክልነት መሆኑን ገልፀዉ ዜጎች በእኩልነት እንዲዳኙ እና እኩል የሆነ የሀብት ክፍፍል እንዲኖር ስርዓት ማበጀት ይገባል ብለዋል፡፡
በህገ መንግስቱ የተቀመጠዉን መርህ በመተግበር አድሏዊ አሰራርን ማስቀረት እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን
#አሐዱ_24 #Ahadu_News_24 #News_24
2.4K views11:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-04 16:31:01
የኤርትራ ሰራዊት በኦሮሚያ እና በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እንደሚገኝ እንደሚያውቅ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረንስ(ኦፌኮ) ገልጿል፡፡

የኤርትራ ስራዊት ከትግራይ ክልል አልፎ በኦሮሚያና በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች መኖራቸውን እንደሚያውቅ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረንስ ባሳለፍነው አርብ የፌደራል መንግስቱና የህወሃት ሀይሎች ስለደረሱበት የሰላም ስምምነት በተመለከተ በመንግስት በኩል ለፖለቲካ ፓርቲዎች ገለጻ በተሰጠበት ወቅት መግለጹ ይታወሳል፡፡
አሑዱም ከምን ተነስታችሁ ነው ይህን ያላቻሁት ሲል የፓርቲውን ምክትል ሊቀመንበር አቶ ሙላት ገመቹን ጠይቋል፡፡
በሁለቱም ክልሎች ከመንግስት ጋር እየተዋጉ ያሉ ሃይሎች በተደጋጋሚ የኤርትራ ሠራዊት አባላት ከፌደራል መንግስቱ ሃይሎች ጋር በመሆን እየወጉን ነው ሲሉ ይገልጻሉ፤እነርሱም የሰሙት ከእነዚሁ ሃይሎች ነው ብለዋል፡፡
በመሆኑም እነርሱ ይህንን እያሉ ያሉት ሰምተው መሆኑን እና ፤መንግስት ደግሞ አለ ወይንም የለም ማለት ድርሻው የእሱ ነው ብለዋል፡፡
እኛ ግን በተደጋጋሚ በእነዚህ አካባቢዎች እነዚሁ ሃይሎች እንዳሉ ነው መረጃው ያለን ሲሉ አክለዋል፡፡ ስለሆነም መንግስት በይፋ ወጥቶ አለ ወይንም የለም የሚለውን መግለጽ ይጠበቅበታል ብለዋል፡፡
ባሳለፍነው አርብ በፌደራል መንግስት እና በህወሃት መካከል እየተደረገ ስላለው የሰላም ስምምነት ጉዳይ በተመለከተ የብሔራዊ የደህንነት አማካሪውና ተደራዳሪው አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ለፖለቲካ ፓርቲዎች ማብራሪያ መስጠታቸው የሚታወስ ነው፡፡
ጣቢያችን ዘገባውን የተሟላ ለማድረግ ወደ ኦሮሚያ ክልል መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ የስልክ ሙከራ ቢያደርግም ሊሳካለት አልቻለም፡፡
በተመሳሳይ ወደ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የጸጥታ ቢሮ ኃላፊ የእጅ ስልክም ተመሳሳይ የስልክ ሙከራ አድርጎ ኃላፊው ስብሰባ ላይ በመሆናቸው ምላሻቸውን ማግኘት አልቻለም፡፡
2.7K views13:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ