Get Mystery Box with random crypto!

AHADU RADIO FM 94.3

የቴሌግራም ቻናል አርማ ahaduradio — AHADU RADIO FM 94.3 A
የቴሌግራም ቻናል አርማ ahaduradio — AHADU RADIO FM 94.3
የሰርጥ አድራሻ: @ahaduradio
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.04K
የሰርጥ መግለጫ

አሐዱ ራድዮ 94.3
Your source for top local and international news and analysis.
"Voice of Ethiopian"
የአሐዱ የቴሌግራም ቻናል ቤተሰብ በመሆን ወቅታዊና እውነተኛ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 23

2022-12-30 11:52:29
ሶሪያ ሩሲያና ቱርክ ከአውሮፓውያኑ 2011 ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ መስብሰባቸው ተነግሯል፡፡

የቱርኩ ፕሬዝዳንት ረሲፕ ጣይብ ኤርዶሃን ከሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲንና ከሶሪያው ፕሬዝዳንት ባሺር አልአሳድ ጋር ተቀምጠው ለመምከር የሚያስችላቸውን ሀሳብ ያመጡ መሆናቸው ተገልጻል፡፡

በዚያ መሰረትም የሶሪያ የቱርክና የሩሲያ የመከላከያ ሚንስትሮች በሩሲያዋ ዋና ከተማ ሞስኮው ውስጥ ተገናኝተው መምከራቸው ነው የተሰማው፡፡
በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ ኤርዶሃን በሰጡት መግለጫ በሶስቱ ሀገራት ሚንስትሮች ደረጃ የተጠራው ስብሰባ በስተመጨረሻው በሶስቱ ሀገራት መሪዎችም እንደሚደረግም መናገራቸው ይታወቃል፡፡
ቱርክና ሶሪያ በሶሪያ ጦርነቱ ከተጀመረ ወዲህ ለ11ዓመት ይፋዊ የሆነ የዲፕሎማሲ ግንኙነት እንደሌላቸው ይታወቃል፡፡

የቱርኩ የዜና ማሰራጫ አናዶሉ በሰራው ዘገባ የቱርኩ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ሁሉሲ አካር የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ሰርጌይ ላቭሮቭና የሶሪያው የውጭ ጉዳይ ሚንስትር አሊ ሙሐመድ በሞስኮው ያደረጉት ውይይት ገንቢና ውጤታማ መሆኑን ገልጿል፡፡
ዘገባው፡-የዘ ናሽናል ነው፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
2.6K views08:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-30 11:49:32
ኬንያው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ በደቡብ ሱዳን የላይኛው ናይል ጆንግሌ ግዛት የሚደረገው ጦርነት ያበቃ ዘንድ የሀገሪቱን ፕሬዘዳንት ሳልቫ ኪርን ጠይቀዋቸዋል፡፡

በደቡብ ሱዳን የላይኛው ናይልና የጆንግሌ ግዛቶች የሚደረገው ከባድ ጦርነት ፈፅሞ መቋጫ ያጣ ይመስላል፡፡
የሀገሪቱ አጎራባች ሀገራት በዚያች ሀገር ያለው የንፁሃት ሰቆቃ ተውግዶ ሰላም ይሰፍን ዘንድ አብዝተው መሻታቸውን ቢገልጹም የተለወጠና በደቡብ ሱዳን የመጣ የሰላም አዝማሚያ እስካሁን የለም፡፡
ይህንን ተከትሎም የጎረቤት ሀገር ኬንያ ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ በደቡብ ሱዳን ሁለት ግዛቶች ማባሪያ ያጣው ጦርነት ተወግዶ ለሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦት የተመቻቸ መንገድ እንዲፈጠር ለደቡብ ሱዳኑ ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪር ጥያቄ ማቅረባቸው ነው የተሰማው፡፡

የኬንያው ፕሬዝዳንት እንደተናገሩት በሀገሪቱ ያለው የጠላትነት ስሌት ሁሉም ቢሆን በአውሮፓውያኑ 2018 የተደረሰውን የሰላም ስምምነት የሚፃረርና የሚንድ መሆኑንም ነው ያሰመሩበት ሲል የዘገበው ዘ ኢስት አፍሪካን ነው፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
2.3K views08:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-30 11:43:06
የፌደራል መንግስቱ ከፍተኛ ባለስልጣኖች ወደ ትግራይ ክልል ያደረጉት ጉዞ አበረታች እና ተስፋ ሰጪ መሆኑ ተገለጸ፡፡

በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የነበረውን ሁኔታ በማርገብ እና በሰላማዊ መንገድ ችግሮች እንዲፈቱ በሁለቱም አካላት በኩል የተወሰደው እርምጃ በመልካም ጎኑ የሚታይ እንደሆነ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ዶክተር ዳንኤል በቀል ለአሀዱ ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ከተባበሩት መንግስታት ኮሚሽን ጋር በመተባበር ባደረገው ጥናት መሰረት በጦርነቱ ወቅት በርካታ የሰብአዊ መብት ጥሶች መፈጠራቸውን በመግለጽ ሰላማዊ ሁኔታ እንዲፈጠር ምክረ ሀሳብ ማቅረቡን ጠቁመዋል፡፡
በዚህም በፌደራል መንግስቱ እንዲሁም በህዋሀት መካከል ሰላማዊ ሁኔታዎች እንዲፈጠሩና በሰከነ መንፈስ ለመወያየት መወሰናቸው ወደ ፊት ተስፋ ሰጪ የሰላም ሁኔታዎች እንዲፈጠር መንገድ ከፋች ነውም ብለዋል፡፡

ይህ የሰላም ስምምነት ኢትዮጵያዊያን በራሳቸው ያለ ማንም ጣልቃ ገብነት ወደ ቀጣይ ትግበራዎች ለመግባት መወሰናቸው ትልቅና ተስፋ ሰጪ ጉዳይ እንደሆነም ነው ያነሱት፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
2.0K views08:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-30 11:40:58
በጦርነት እና በድርቅ አደጋዎች ምክንያት የኮቪድ 19 ክትባት ያላገኙ አካባቢዎችን ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝ ተገለጸ፡፡

በሀገር አቀፍ ደረጃ የኮቪድ 19 ክትባት ስርጭት በሚደረግበት ወቅት በተለያዩ ምክንቶች ይህንን እድል ላላገኙና ለሚያስፈልጋቸው ዜጎች ክትባቱን ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝ በጤና ሚኒስቴር የብሄራዊ ኮቪድ ምላሽ ግብረ ሀይል አስተባባሪ ዶክተር መብራቱ ማንሴቦ ለአሀዱ ተናግረዋል፡፡

በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በነበረው ጦርነት በርካታ ሰዎች ክትባት ባለማግኘታቸው ይህንን ተደራሽ ለማድረግ በስፋት እየተንቀሳቀሱ እንደሚገኙም ገልጸዋል፡፡
በዚህ እንቅስቃሴ ከ1 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ተጨማሪ ሰዎች ተደራሽ ለማድረግ አልመው እየሰሩ እንደሚገኙም ዶክተር መብራቱ ጠቅሰዋል፡፡
በተለይ በድርቅ እና በጦርነት አማካኝነት ክትባቱን ላልወሰዱ ዜጎች በተለየ ሁኔታ ክትባቱን እንዲያገኙ ለማስቻል እየሰሩ እንደሚገኙ ነው አክለው የተናገሩት፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
1.8K viewsedited  08:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-30 11:31:06
በህዝብ ንብረት ላይ ከፍተኛ ብክነት እያስከተሉ ያሉ ተቋማትና ሹማምንቶች በህግ ሊጠየቁ እንደሚገባ ተገለጸ፡፡

ተቋማት ከቢሮ ሳይወጡ ከ2 ነጥብ 9 ሚሊዮን ብር በላይ አላግባብ አበል እንደተከፈለና ይህም ከፍተኛ የሆነ ወንጀል ስለመሆኑ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መገለጹ ይታወሳል፡፡
አሀዱም ይህንን መነሻ በማድረግ ሌሎች በርካታ ተቋማትና ባለስልጣናትም በመሰል አይነት ድርጊቶች ዉስጥ የሚሳተፉ እና ስልጣናቸዉን ያለ አግባብ የሚጠቀሙ እንደመኖራቸዉ በምን ልክ በህግ አግባብ ተጠያቂ ሊሆኑ ይገባል ሲል የህግ ባለሙያዎችን ጠይቋል ፡፡
የህግ ባለሙያዉ አቶ ካሳሁን ሙላቱ እንደገለፁት ይህ ከፍተኛ የሆነ ወንጀል በመሆኑ አስተዳደራዊ እርምጃ የሚያስወስድና በወንጀል የሚያስጠይቅ ነዉ ብለዋል፡፡

ሌላኛዉ የህግ ባለሙያ አቶ ይልቃል ሀሳቤ በበኩላቸዉ የፀረ ሙስና አዋጅና የህግ ማእቀፍ ያለ በመሆኑ እነዚህን ህጎች መሰረት አድርጎ ማየት እና እርምጃ መዉሰድ ያስፈልጋል ነዉ ያሉት፡፡
በተጨማሪም ከተፈፀመ በኋላ መቅጣትን ብቻ ሳይሆን ወንጀሉ እንዳይፈፀም የፋይናንስ ስርአትን ማስተካከል በስልጣን ላይ የሚሰየሙ ግለሰቦችም ስነ-ምግባራቸዉ እና ቀድሞ የነበራቸዉ ስብእና ተለይቶ መሆን እንዳለበት አመላክተዋል፡፡
ይህንን ለመከላከልም ቀድሞ ጥቆማ መቅረብ ስላለበት በተለያየ እርከን ያለ አካል ያገኘዉን ሪፖርት ለፀጥታና ፍትህ ተቋማት እንዲደርስ ማድረግ አለባቸዉ ብለዋል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
?lang=en
2.1K views08:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-29 16:22:41
የመፅሀፍ ምረቃ ፕሮግራም የፊታችን ታህሳስ 22, 2015 ዓ ም በብሔራዊ ትያትር

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
3.2K viewsedited  13:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-29 11:56:53
በአዲስ አበባ ከተማ አንድ የወጣት ስብእና ማእከል እንዲፈርስ ተደርጎ ቦታው ለግል ባለሃብት እንዲሰጥ መደረጉ ተገለፀ፡፡

በአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ሚሊኒየም አዳራሽ ጀርባ ይገኝ የነበረው የወጣት ስብእና ግንባታ ማእከል እንዲፈርስ ተደርጎ ቦታው ለግል ባለሃብት ተላልፎ መሰጠቱን የአዲስ አበባ ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ ጥናት እና አቅም ግንባታ ባለሙያ አቶ ሙላቱ አበበ ለአሐዱ ገልጸዋል፡

በአዲስ አበባ ከተማ ያሉት ወጣት ማእከላት በቁጥርም ሆነ በሚሰጧቸው አገልግሎቶች ከፍተኛ ችግር እንዳለባቸው የሚታወቅ ሲሆን የአዲስ አበባ ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ ችግሮቹን ለመፍታት የተለያዩ ጥረቶችን እያደረገ የሚገኝ ቢሆንም በዚህ መልኩ ያሉትንም እንዲፈርሱ መደረጉ ችግሩን እንደሚያባብሰው አመላክተዋል፡፡

ይህን አስመልክቶ አሐዱ መረጃውን ለማግኘት ባደረገው ጥረት ማዕከሉ መፍረሱን እውነት እንደሆነ እንዲሁም በምትኩ ሌላ ለመገንባት የሚያስችል ቦታ እንደተሰጠ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የወጣቶች ስብእና ማእከላት ልማት ኤጀንሲ አረጋግጧል፡፡
አሁን በተለዋጭ የተረከቡት ቦታ ከዚህ በፊትም የወጣት ስብእና ማእከል እንዲገነባ ተደጋጋሚ ጥያቄ ሲቀርብበት የነበረ እንደሆነ እና ግንባታውም በቅርቡ እንደሚጀመር ከተቋሙ ያገኘነው መረጃ ያሳያል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
1.6K views08:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-29 11:50:43
የመንግስት ተቋማት የመስተንግዶ ወጪ በግለሰቦች እጅ መውደቁ አሳሳቢ መሆኑ ተገለጸ፡፡

ይህንን ያለው በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሲሆን የመንግስት ተቋማት ስልጠናዎችን ጨምሮ ለተለያዩ ዝግጅቶች እንዲያውሉት የሚፈቀደው የመስተንግዶ ወጪ አጠቃቀምን በተመለከተ መመሪያ የተዘጋጀ ቢሆንም ወጪው በግለሰቦች እጅ ስለመውደቁ ተጠቁሟል፡፡

መመሪያው የተዘጋጀው ውጤታማ የበጀት አጠቃቀም እንዲኖር በማለም ቢሆንም ተፈጻሚነቱ ግን በእጅጉ ደካማ እንደሆነና የወጪው በግለሰቦች እጅ መውደቅ አሳሳቢ መሆኑንም ነው የቋሚ ኮሚቴው አባላት የገለጹት፡፡
ምንም እንኳን የፌደራል ኦዲተር መስሪያ ቤት ስለጉዳዩ ጥልቅ ምርመራና ዳሰሳ እንዳደረገ ቢገልጽም በሚፈለገው መጠን ፍተሻ ተደርጎበታል የሚል እምነት የለንም ያሉት የቋሚ ኮሚቴው አባላት ስለሆነም ጉዳዩ አሁንም ትኩረት የሚሻ ነው ሲሉ አስምረዋል፡፡

ከዚህም በተጨማሪ ከመስተንግዶ ጋር በተያያዘ የሚፈጸሙ ግዢዎች የተጋነኑ የሚሆኑበት አጋጣሚ በርካታ እንደሆነ ገልጸው ይህም ሃገሪቱን አሁናዊ የምጣኔ ሃብት ሁኔታ ከግምት ባስገባና መመሪያን መሰረት ባደረገ መልኩ እርምጃ ሊወሰድ እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
1.5K viewsedited  08:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-29 11:46:20
በድርቅ ለተጎዱ ህጻናት ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ተገለጸ፡፡

በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች ካለፈው አመት አጋማሽ አንስቶ የተከሰተውን ድርቅ ተከትሎ ወደ 2 ሚሊዮን የሚጠጉ ህጻናት አስቸኳይ የምግብ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው የተባበሩት መንግስታት የህጻናት መርጃ ድርጅት ዩኒሴፍ በኢትዮጲያ ለአሐዱ ባጋራው ሪፖርት የገለጸ ሲሆን ከነዚህም መካከል 8 መቶ ሺህ የሚሆኑት አስቸኳይ የህክምና ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው ገልጿል፡፡

አሐዱም ሪፖርቱን መነሻ በማድረግ የጤና ሚኒስቴርን ያነጋገረ ሲሆን በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የእናቶች ጤናና የብሄራዊ ክትባት ማስተባበሪያ ዳይሬክተር አቶ ዮሃንስ ላቀውም በበኩላቸው ዩኒሴፍ ባወጣው የቁጥር መረጃ ላይ እርግጠኛ መሆን ባይቻልም በድርቅ የተጎዱ በርካታ ህጻናት እንዳሉና ድጋፍም እንደሚያስፈልጋቸው እናምናለን ብለዋል፡፡

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሚያስፈልጉ አስቸኳይ ድጋፎችን ለማድረግ እየሰራ እንደሆነ ገልጸው የቁጥር መረጃውን ጥናት በዋነኝነት እያካሄደ ያለው ተቋም ግን የኢትዮጲያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲቲዩት እንደሆነ ገልጸዋል፡፡
አሐዱም የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲቲዩትን ያነጋገረ ሲሆን ተቋሙም ጥናቱን እያካሄደ እንደሚገኝና ዝርዝር መረጃውን በቅርቡ ግልጽ እንደሚያደርግ ጠቁሟል፡፡
እንደ ዩኒሴፍ መረጃ በምስራቅ አፍሪካ ቀንድ በሚገኙት በኢትዮጲያ ፣ ሶማሊያና ኬንያ ወደ 20 ነጥብ 2 ሚሊየን የሚጠጉ ህጻናት በአስከፊ ርሃብ ውስጥ ይገኛሉ፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
1.4K views08:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-29 11:43:36
ከአንድ መቶ በላይ የስነ ምግባር ችግር ያለባቸው የጸጥታ አካላት ላይ ርምጃ መወሰዱ ተገለጸ፡፡
የሲዳማ ክልል በክልልነት ሲደራጅ የሁሉንም ብሄር ብሄረሰቦችን ሰላም ለማስጠበቅ ህግን ለማክበር እና ለማስከበር በሚል ለመስራት እቅድ መያዙን የተናገሩት የሲዳማ ክልል የሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ሀላፊ አቶ አለማየሁ ጢሞቲዎስ ፤በተሰራው ስራ ህግ ለሁሉም ሰው እኩል እንደሆነ ማሳያ የሆኑ ስራዎች ተሰርተዋል ብለው አሁን ላይ ከሌሎች ክልሎች በአንጻራዊነት ብቻ ሳይሆን በተሻለ መልኩ ሰላም ማረጋጋጥ እንደተቻለ ነው የገለጹት፡፡
በዘላቂነት ሰላምን ለማስጠበቅ የተጀመረው ስራ እንዲቀጥል የአመራሮችን ብቃት በማዳበር እና ከማህበረሰቡ ጋር ተቀራርቦ በመስራት የተገኘ ውጤት ነው ብለዋል፡፡
ሀላፊነት ከተጠያቂነት ጋር እንደመሆኑ ፖሊስ ኮምሽነሮችን ጨምሮ ከአንድ መቶ በላይ የስነ ምግባር ችግር ያለባቸውን የጸጥታ አካላት ላይ ርምጃ እንደተወሰደባቸው ተናግረዋል፡፡
የአመራሮችን አቅም ማጎልበት እና ተጠያቂነትን የማረጋጋጥ ስራ በየጊዜው እንደሚሰራ የተናገሩት አቶ አለማየሁ ከህግ እና ከስነ ምግባር ውጪ ማህበረሰቡ ቅሬታ እንዲያነሳ ምክንያት የሆኑ አካላት ላይ ከደረጃ ዝቅ ማድረግ፤ ከስራ ማሰናበት፤ እርከን መቀነስን ዓይነት ርምጃ እንደተወሰደባቸውም ተናግረዋል፡፡
ሰላምን ለማስጠበቅ ጠንካራ የጸጥታ መዋቅር ሊኖር እንደሚገባ ያነሱት አቶ አለማየሁ ሀገርም በተናጥል የሚገነባ ባለመሆኑ የጋራ ስራ እንደሚያስፈልግም ጠቁመዋል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
1.2K views08:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ