Get Mystery Box with random crypto!

AHADU RADIO FM 94.3

የቴሌግራም ቻናል አርማ ahaduradio — AHADU RADIO FM 94.3 A
የቴሌግራም ቻናል አርማ ahaduradio — AHADU RADIO FM 94.3
የሰርጥ አድራሻ: @ahaduradio
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.04K
የሰርጥ መግለጫ

አሐዱ ራድዮ 94.3
Your source for top local and international news and analysis.
"Voice of Ethiopian"
የአሐዱ የቴሌግራም ቻናል ቤተሰብ በመሆን ወቅታዊና እውነተኛ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 20

2023-01-13 14:59:14
እየተካሄደ ያለዉ ቤት የማፍረስ ዘመቻ የሀገሪቱን እና የዜጎችን ወቅታ ሁኔታ ግምት ዉስጥ ያላስገባ ነዉ ተባለ፡፡

በአዲስ አበባ ዙሪያ ህገ-ወጥ ናቸዉ የተባሉ ቤቶች በዘመቻ መልክ እየፈረሱ መሆኑ ይታወቃል፡፡
የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም ዋና እንባ ጠባቂ ዶክተር እንዳለ ሀይሌ በአዲስ አበባ ዙሪያ እና ቡራዩ አካባቢ ቤት እየፈረሰባቸዉ ያሉ በርካታ ዜጎች ወደ ተቋሙ እየመጡ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
ተቋማችን ህገ-ወጥነትን አያበረታታም ያሉት ዶክተር እናዳለ አሁን እየተካሄደ ያለዉ ቤት የማፍረስ ዘመቻ ወቅታዊ ሁኔታን ታሳቢ ያደረገ አይደለም ሲሉ ገልጸዋል፡፡
ጉዳዩን በህገ-ወጥነት መነጽር ብቻ መመልከት አግባብ አይደለም ያሉት ዋና እንባ ጠባቂዉ የበአል ወቅት እንደመሆኑ፤ በርካታ ተፈናቃዮች በተለያዩ ክልሎች እንደመኖራቸዉ እና ወቅታዊ የሀገራችን ሁኔታ በዘመቻ መልክ ይህን ለመፈጸም አስቻይ አይደለም ሲሉ ነዉ አጽኖት የሰጡበት፡፡
አክለዉም የመንግስት አስፈጻሚ አካላት ቤት የማፍረስ ዘመቻዉን ከማካሄዳቸዉ በፊት ጊዜዉ አስቻይ ነዉ ወይ የሚለዉን ማየት ነበረባቸዉ ነዉ ያሉት፡፡
ሰዎች ህገ-ወጥ አሊያም ህግን ባልተከተለ መንገድ ቤት ከገበሬ ላይ የሚገዙበትን ምክንያት የመንገስት አካላት ሊያጤኑት ይገባል ያሉት ዋና ዳሬክተሩ የመሬት ፖሊስን ፤በቂ የቤት አቅርቦት እና ተደራሽነት መኖር እና የቤት ሽያጭ ስረአቶች በህግ መእቀፍ ዉስጥ ያሉ ናቸዉ ወይ የሚለዉን ከግምት በማስገባት ማስተካከያዎችን መዉሰድ አለባቸዉ ሲሉ አጽኖት ሰጥተዋል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
1.1K views11:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-12 11:36:10
የጉራጌ ዞን በኮማንድ ፖስት ስር እንዲመራ መደረጉ ህዝቡ ጥያቄውን እንዳያሰማ የሚያደርግ ነው ሲሉ የዞኑ ወጣቶች ገለፁ፡፡
የጉራጌ ዞን ከህዳር 16 ጀምሮ በኮማንድ ፖስት ስር እንዲመራ የደቡብ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ መወሰኑ አይዘነጋም፡፡
በዚህ ጉዳይ ላይ ሃሳባቸውን ለአሐዱ የሰጡ እነዚሁ ወጣቶች አስቀድሞም ቢሆን ዞኑ በኮማንድ ፖስት ስር እንዲተዳደር የሚያደርግ ሁኔታ አልነበረም ነው ያሉት፡፡
በአሁን ወቅትም ዞኑ በኮማንድ ፖስት ስር መሆኑ ወጣቶች ህገ-መንግስቱን አክብረው እንዳይንቀሳቀሱ እያደረገ ነው ሲሉም ከሰዋል፡፡ ወጣቶቹ አያይዘውም ዞኑን በመደበኛው የህግ ማስከበር ስርዓት ማስተዳደር ይቻል ነበር ነው የሚሉት፡፡
እንደ መከራከሪያም የትኛው አመጽ ተነስቶ ነው፤ ለዚህስ የሚዳርግ ምንም አይነት አዝማሚያ ታይቶ ነው ሲሉም ጠይቀዋል፡፡ በጥቅሉ ኮማንድፖስቱ አፈና ውስጥ ነው ያስገባን ብለዋል፡፡
ምንም እንኳን ወጣቶቹ ይህን ቢሉም የክልሉ ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ዞኑ በኮማንድ ፖስት እንዲመራ ውሳኔ ሲያሳልፍ ዞኑ ከክልል አደረጃጀት ጥያቄ ጋር በተያያዘ በአካባቢው የተፈጠረውን የጸጥታ ችግር “በመደበኛ አሰራር ለማስተዳደር” ባለመቻሉ መሆኑን መግለጹ አይዘነጋም፡፡
የሃድያ ዞን ፤ የጉራጌ፤ የስልጤ፤ የሃላባ ፤ የከንባታ እና የም ልዩ ወረዳ የፊታችን ጥር 29 በሚደረገው ህዝበ ውሳኔ የማይሳተፉ ሲሆን ከነባሩ የደቡብ ክልል ጋር አብረው ይቀጥላሉ ነው የተባሉት፡፡
ጣቢያችን በዚህ ጉዳይ ላይ ስለተነሳው ክስ ማብራሪያ ለመጠየቅ ኮማንድ ፖስቱን ወደ ሚመሩት የስራ ኃላፊዎች የስልክ ሙከራ ቢያደርግም ሊያገኛቸው አልቻለም፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
3.4K views08:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-12 11:25:22
እስካሁን በዚህ የማጭበርበር ስራ ተሰማለጋራ መኖሪያ ቤቶች በሚል የጋብቻ ሁኔታን ለማስቀየር የሚመጡ ነዋሪዎች መበራከታቸው ተገለፀ፡፡
የአዲስ አበባ ወሳኝ ኩነት ምዝገባ እና መረጃ ኤጀንሲ ከሚያከናውናቸው ተግባራት መካካል ጋብቻን መመዝገብ እና ያላገባ ምስክር ወረቀት መስጠት እንደሆነ የሚታወቅ ሲሆን ጥንዶች በጋራ እየኖሩ የመኖሪያ ቤት እንዲሁም መሰል እድል ሲያጋጥማቻው ያላገባ የምስክር ወረቀት የመጠየቅ ተግባር እጅጉን ከፍተኛ በመሆኑ ይህንን ለማስቀረት ሲባል በቴክኖሎጂ የተደገፈ ስራ በከፍተኛ ሁኔታ እየተሰራ እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ወሳኝ ኩነት ምዝገባ እና መረጃ ኤጀንሲ የኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ዮሴፍ ንጉሴ ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡
አሁን ላይ ግን ማንኛውም የጋብቻ ሁኔታ ማስተካካያ ቢያስፈልግ በማዕከል ደረጃ እንዲሆን የተደረገ ሲሆን ሆኖም ግን በርካቶች የጋብቻ ሁኔታቸውን ለማስተካከል ወደ ማእከል እየመጡ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ጥንዶች ሆነው በአንድ ቤት ውስጥ እየኖሩ የጋራ መኖሪያ እጣ ተመዝግበው ከሆነ የተለያዩ ሰዎች ተብለው ስለሚቆጠሩ እና ጋብቻ አለ ተብሎ ሰለማይታሰብ ለሁለቱም በአንድ ጊዜ እጣው ሊደርስ የሚችልበት ሁኔታ ስላለ የቤት ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ላይ ጥያቄ ሊያስነሳ እንደሚችል ገልፀዋል፡፡
ያገቡ ሆነዉ የተመዘገቡ ሰዎችን ያላጋባ በማድረግ የጋብቻ ሁኔታቸዉን የመቀየር አገልግሎት በጊዜያዊነት መቆሙን ገልፀው ለዚህም በቴክኖሎጂ የተደገፈው አሰራር ትግበራ ይህንን ለማስቀረት አንደሚያስችል አስታዉቀዋል፡፡
በኤጀንሲው የተያዙ ባይኖሩም ከዚህ በኋላ የተጠናከረ ስራ እንደሚሰራ አቶ ዮሴፍ አክለዉ ተናግረዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
3.1K viewsedited  08:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-12 11:17:38
በአዲስ አበባ ዙሪያ እየተካሄደ ያለዉን ቤት የማፍረስ ዘመቻን ለማጣራት በሄዱበት የታሰሩት የሰብዓዊ መብት ባለሙያዎች ፍርድ ቤት በዋስ እንዲፈቱ መወሰኑ ተገለፀ፡፡

በአዲስ አበባ ዙሪያ እየተካሄደ ባለው ቤት የማፍረስ ዘመቻ ምክንያት ቤታቸው የፈረሰባቸው ግለሰቦች ባቀረቡት አቤቱታ መሰረት የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ ሶስት የሰብዓዊ መብት ባለሙያዎች እና አንድ ሹፌር ታህሳስ 27 ዓለም ባንክ አካባቢ ጥቆማውን ለማጣራት በሄዱበት ወቅት በፖሊስ ተይዘው አራቱም ሰራተኞች መታሰራቸዉ ይታወሳል፤
ሠራተኞቹ ፍርድ ቤት ቀርበው ከተጠየቀባቸው 14 ቀናት የምርመራ ጊዜ ውስጥ አምስት ቀናት ተፈቅዶ በትላንትናዉ ዕለት ለሁለተኛ ጊዜ በሰበታ ወረዳ ፍርድ ቤት የቀረቡ ሲሆን ፍርድ ቤቱም በዋስ እንዲወጡ መፍቀዱን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ ምክትል ስራ አስፈፃሚ አቶ ዘየደ ገብረፃዲቅ ለአሀዱ ተናግረዋል፡፡

ፍርድ ቤቱ አቃቤ ህግ የጠየቀዉን የ7 ቀን ቀነ ቀጠሮ ዉድቅ በማድረግ የዋስትና መብታቸዉ እንዲከበር ለፖሊስ ትዕዛዝ ማስተላለፉን ገልፀዉ በዛሬዉ እለት ይፈታሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ አስታዉቀዋል፡፡
ኢሰመጉ የታሰሩት ሰራተኞቹ እንዲፈቱ ለፌደራል መንግስት፤ ለኦሮሚያ ክልል እና ለተለያዩ ተቋማት ደብደቤ ማስገባቱ ይታወሳል፡፡
የኢሰመጉ ሰራተኞች በተፈቀደላቸዉ የዋስ መብት መሰረት ዛሬ ይፈታሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
2.7K views08:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-12 11:12:38
የነዳጅ ዋጋ ጭማሬውን ተከትሎ የታሪፍ ጭማሪ ዋጋ ይፋ እስኪሆን ድረስ በራሳቸው ፍቃድ ዋጋ የሚጨምሩ የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች ህገ ወጥ እንደሆኑ ተገለጸ፡፡

የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደቱን ህጋዊ ለማድረግ እና ህብረተሰቡ ተገቢ ያልሆነ ክፍያ እንዳይጠየቅ ከዚህ ቀደም የታሪፍ ዋጋዎች በትራንስፖርት ተሸከርካሪዎች ውስጥ እንዲለጠፉ መደረጉን በማስታወስ ከተለጠፈው ዋጋ ውጪ የሚያስከፍሉ አካላት ተጠያቂ እንደሚሆኑ የገለጹት የአዲሰ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮ ኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተር ወ/ሮ እጸገነት አበበ በአሁን ወቅት የነዳጅ ዋጋ ጭማሪውን ተከትሎ ቢሮው ታሪፍ ሳያወጣ በገዛ ፍቃዳቸው የዋጋ ጭማሪ የሚያደርጉ አካላት ህጋዊ እንዳልሆኑ ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

ቢሮው በጥናት የተደገፈ ህጋዊ ጭማሪ አድርጎ እስኪያሳውቅ ድረስ ከዚህ ቀደም በነበረው የታሪፍ መጠን አገልግሎቱ እንደሚቀጥል እና የነዳጅ ጭማሪውን ባገናዘበ መልኩ በቅርቡ አዲሱ የታሪፍ ማሻሻያ ይፋ እንደሚደረግ ተናግረዋል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24 #Ahadu_News_24
2.8K views08:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-10 12:11:34
የሙርሌ ታጣቂዎችና ኦነግ ሸኔ የፀጥታ ስጋት እንደሆኑበት ክልሉ ገልጿል፡፡
የጋምቤላ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሰናይ አኮር ለአሀዱ እንደገለፁት በጋምቤላ ክልል ደቡብ ሱዳን ድንበር ላይ እየተካሄደ ባለዉ ጥቃት ሳቢያ የክልሉ የፀጥታ ሀይል በሙሉ አቅሙ ወደዚያ እንዲሆን በመደረጉ ምክንያት ሌላ ጥቃት ለመከላከል አቅም አንሶናል ነዉ ያሉት፡፡
ነገር ግን በደቡብ ሱዳን አዋሳኝ ድንበር ላይ እየተፈጸመ ያለዉን ጥቃት ለመመከት በየ አቅጣጫዉ የፀጥታ ሀይል ተሰማርቷን ብለዋል፡፡
አሁን ላይ የሸኔ ቡድን በቀጥታ በጋምቤላ ክልል ገብቶ ጥቃት እየፈፀመ ባይሆንም በቄለም ወለጋ እየተደረገ ያለዉ እንቅስቃሴ በጋምቤላ ክልል ላይ ጫናና ስጋትን ፈጥሯል ሲሉም ገልጸዋል፡፡
በተለይ በአሁኑ ወቅት ክልሉ ሀይሉን ወደ ደቡብ ሱዳን በማድረጉ ቄለም ወለጋ ከጋምቤላ ጋር የሚዋሰን በመሆኑ ከፍተኛ አለብን ብለዉ ያ ቢሆንም የክልሉ መንግስት በተቻለዉ አቅሙ ሁሉ የመከላከል ስራዎችን እየሰራ እንዳለ አመላክተዋል፡፡
በሌላ በኩል የሙርሌ ታጣቂዎችና በጋምቤላ ክልል ያሉ አንዳንድ ህገ-ወጥ እንቅስቃሴ የሚያደርጉ አካላት እርስ በርስ ሽርክና በመፍጠር መሳሪያ እንደሚሸጡ እና እንደሚገዙም ገልፀዉ ይህንን ለመከላከል በሚዛን ከተማ ዉይይት መደረጉንም አብራርተዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24 #Ahadu_News_24
2.7K views09:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-10 12:08:21
በሀገር ውስጥ የሚበለጽጉ ማህበራዊ ትስስር ገፆች ፈቃድ አሰጣት እና ቁጥጥር ፖሊሲ እተዘጋጀ እንደሚገኝ ተገለጸ፡፡
በኢትዮጵያውያን የበለፀጉ ማህበራዊ ድረ ገፆች የፍቃድ አሰጣጥ እና ቁጥጥር ስራዉ በምን መልኩ ነው የሚካሄደው ሲል አሀዱ የመረጃ መረብ ደህንነት ኤጀንሲ የኮሚኒኬሽን ባለሙያ አቶ ሃብታሙ ተሾመ አነጋግሯል፡፡
በርካታ የማህበራዊ ትስስር ገፆች የሚጠቀሙ ግለሰቦች ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ መረጃዎቹ የሚቀመጡበት እና ቁጥጥር የሚካሄደው በሌሎች አገራት በሚገኙ ትላልቅ የማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ እንደሆነ ገልፀው በሀገር ወስጥ የመረጃ ማከማቻ የሌላቸውን ፍቃድ መስጠትም ሆነ መቆጣጠር እንማይቻል ገልጸዋል፡፡
እነዚህ ገጾች በሚያስተላልፏቸው መረጃዎች ዙሪያ ግን እንደ አገር ከመረጃ መረብ ደህንነት ጋር በተገናኘ ተገቢውን ክትትል እንደሚደረግባቸው ገልጸው ከፍትህ ሚንስቴር እንዲሁም ሌሎች ከሚመለከታቸው መንግስታዊ አካላት ጋር በመሆን መሰል የማህበራዊ ትስስር ገጾች ፊቃድ አሰጣጥ እና ቁጥጥር ዙሪያ የተለያዩ ፖሊሲዎችን እና ህጎች እየተዘጋጁ እንደሚገኝም ጠቁመዋል፡፡
አክለውም እንደ ሀገር በራሳችን ዜጎች የተሰሩ ኢትዮጵያዊ የማህበራዊ ትስስር ገፆች የማበልፀግ ፍላጎት እና ሙከራዎች እየጨመሩ መምጣታቸውን ገልፀው ሊበረታታ የሚገባው እንደሆነም አመላክተዋል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24 #Ahadu_News_24 #News_24
2.4K views09:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-10 12:05:22
በአዲስ አበባ ዙሪያ እየተካሄደ ያለዉን ቤት የማፍረስ ሂደት ለማጣራት በሄዱበት የታሰሩት የሰብአዊ መብት ባለሙያዎች እስካሁን ድረስ አለመፈታታቸዉ ተገለፀ፡፡
በአዲስ አበባ ዙሪያ እየተካሄደ ባለው ቤት የማፍረስ ሂደት ምክንያት ቤታቸው የፈረሰባቸው ግለሰቦች ባቀረቡት አቤቱታ መሰረት የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ ሶስት የሰብዓዊ መብት ባለሙያዎች እና አንድ አሽከርካሪ ታህሳስ 27 2015 ጥቆማውን ለማጣራት መላኩ ይታወቃል፡፡
ጉዳዩን ለማጣራት በሄዱበት ወቅት በፖሊስ ተይዘው አራቱም ባለሙያዎች የድርጅቱንም ተሽከርካሪ ጨምሮ ዓለምገና ሁለተኛ ፖሊስ ጣቢያ ታስረው እንደሚገኙ እና እስካሁን ድረስ አለመፈታታቸዉን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤ ምክትል ስራ አስፈፃሚ አቶ ዘየደ ገብረፃዲቅ ለአሀዱ ተናግረዋል፡፡
ኢሰመጉ በባለሙያዎች ላይ የተለያዩ ጫናዎች እና ዛቻ ጨምሮ ማስፈራራት እየደረሰበት እንደሚገኝ አስታዉቀዋል፡፡
ይህ ድርጊት ከህግ አግባብ ውጪ የሆነና የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ ለሰብዓዊ መብት መከበር የሚሰራ ተቋም እንደመሆኑ የተቋቋመበትን አላማ እንዳይፈጽም እንቅፋት የሚሆን፤ ባለሙያዎቹ በነጻነት ተንቀሳቅሰው እንዳይሰሩ ለማድረግ እና ለማሸማቀቅ የተደረገ ድርጊት መሆኑን ገልፀዋል፡፡
ጉዳዩ ለሚመለከታቸዉ ለፌደራል መንግስትም ለኦሮሚያ ክልልም ደብዳቤ ቢያስገቡም ምላሽ አለማግኘታቸዉን አቶ ዘየደ አስታዉቀዋል፡፡
መንግስት በኢሰመጉ ላይ የተለያየ አይነት እስር እና ጫናዎችን ከመፈጸም እንዲቆጠብ ብሎም እስካሁን ድረስ በእስር ላይ የሚገኙት ሰራተኞችን ፖሊስ በአስቸኳይ ከእስር እንዲፈታ ጠይቀዋል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
2.1K views09:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-10 12:00:02
የጋምቤላ ክልል በወባ በሽታ ስርጭት በቀዳሚነት መቀመጡ ተገለጸ፡፡
በኢትዮጲያ የተለያዩ አካባቢዎች የወባ በሽታ በከፍተኛ መጠን እየተሰራጨ የሚገኝ ሲሆን ካለፈው ሐምሌ ወር 2014 ዓ.ም አንስቶ እስከ ህዳር ወር 2015 ዓ.ም ድረስ ባሉት ጊዜያት በተደረገው ምርመራ የጋምቤላ ክልል ከሌሎቹ የሃገሪቱ አካባቢዎች ይልቅ ከፍተኛው ቁጥር የተመዘገበበት መሆኑን የገለጸው የኢትዮጲያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲቲዩት ነው፡፡
በተቋሙ የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ቅኝት እና ምላሽ ዳይሬክተር አቶ መስፍን ወሰን እንደገለጹት አሁን ባለው ሁኔታ በኢትዮጵያ ባለፉት አምስት ወራት ውስጥ የወባ በሽታ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር፤ ባለፉት አምስት ዓመታት ከነበረው ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ ሆኖ መመዝገቡን ነዉ፡፡
በዚህም ባለፉት 5 ወራት ምርመራ ከተደረገላቸው 6.3 ሚሊዮን ሰዎች ውስጥ 1.3 ሚሊዮን ገደማ የሚሆኑት በሽታው እንደተገኘባቸውም ነው የገለጹት፡፡

በሃገሪቱ ውስጥ የወባ ስርጭት በከፍተኛ መጠን እየተስፋፋ የሚገኝ ሲሆን አሁን ባለው ሁኔታም የበሽታው ስርጭት ካለፈው ሃምሌ ወር 2014 ዓ.ም አጋማሽ ወዲህ ሲታይ በ 2 እጥፍ ስለመጨመሩ የአለም ጤና ድርጅት መረጃ ያመላክታል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24 #Ahadu_News_24 #News_24
2.3K views09:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-09 14:55:00
ሳዑዲ አረቢያ ስታደርገው የነበረውን የባህር ሀይል የጦር ልምምድ ማጠናቀቋን አስታውቃለች፡፡

የሳዑዲ አረቢያ ጦር ሀይል የነዳጅ ማውጫና ማቀነባበሪያ ስፍራዎቹን ከየትኛውም ጥቃት ለመጠበቅ በሚል ለቀናት የዘለቀ የባሀር ላይ የጦር ልምምድ ማድረጉ ታውቋል፡፡

የሳዑዲ አረቢያ ጦር ሀይል የባህር ላይ የጦር ልምምዱን ያደረገው በአልጁቤይል ከሚገኘው የአብዱላዚዝ የባህር ማዘዣ መሆኑም ነው የተገለፀው፡፡

በሳዑዲ አረቢያ የታሳዲ የባህር ሀይል ዋና ዳይሬክተር አድሚራል ካሊድ አልሻሚኒ እንደተናገሩት የአሁኑ የሀገሪቱ የባህር ሀይል ግዙፍ የጦር ልምምድ የመላዋ ሳዑዲ አረቢያን ጦር ሀይሎች ያቀናጀና ከየትኛውም ጥቃት ለመጠበቅ የተቀላጠፈ የመረጃ ልውውጥና በጋራ ተከላክሎ በጋራ ለማጥቃት የሚያስችል ነው ሲሉ ገልጸውታል፡፡

ከዚያ ውጪም ለአምስት ቀናት የዘለቀው የሳዑዲ አረቢያ የባህር ሀይል የጦር ልምምድ የሀገሪቱን የውሃ ባህር መተላለፊያዎች ሁሉ በጥልቅ ለመቃኘት ያስቻለ መሆኑን የዘገበው መኸር ኒውስ ነው፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24 #Ahadu_News_24 #News_24
1.7K views11:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ